ማርቆስ 14 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 14:1-72

ኢየሱስን ሽቶ የቀባችው ሴት

14፥1-11 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥2-16

14፥121011 ተጓ ምብ – ሉቃ 22፥1-6

14፥3-8 ተጓ ምብ – ዮሐ 12፥1-8

1ፋሲካና የቂጣ በዓል ሊከበር ሁለት ቀን ሲቀረው፣ የካህናት አለቆችና ጸሐፍት ኢየሱስን የሚይዙበትና የሚገድሉበትን ዘዴ ይፈልጉ ነበር። 2ሆኖም፣ “ሕዝቡ ዐመፅ እንዳያነሣ በበዓሉ ሰሞን መሆን የለበትም” ይባባሉ ነበር።

3እርሱም በቢታንያ በለምጻሙ ስምዖን ቤት በማእድ ተቀምጦ ሳለ፣ አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ ውድ የሆነ ንጹሕ የናርዶስ ሽቱ የተሞላበት የአልባስጥሮስ ቢልቃጥ ይዛ መጣች፣ ቢልቃጡንም ሰብራ ሽቱውን በራሱ ላይ አፈሰሰችው።

4በዚያ ከነበሩት አንዳንዶቹ በድርጊቱ ተቈጥተው እንዲህ ይባባሉ ነበር፤ “ሽቱው ለምን በከንቱ ይባክናል? 5ከሦስት መቶ ዲናር በላይ ተሸጦ፣ ገንዘቡን ለድኾች መስጠት ይቻል ነበር።” ሴትዮዋንም ነቀፏት።

6ኢየሱስ ግን እንዲህ አላቸው፤ “ተዉአት፣ ለምን ታስቸግሯታላችሁ? መልካም ነገር አድርጋልኛለች። 7ድኾች ምንጊዜም ከእናንተ ጋር ናቸው፤ በፈለጋችሁ ጊዜ ልትረዷቸው ትችላላችሁ፤ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም፤ 8እርሷ ማድረግ የምትችለውን ያህል አድርጋለች፤ ለመቃብሬ እንዲሆን ሰውነቴን አስቀድማ ቀብታለች። 9እውነት እላችኋለሁ፤ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በሚሰበክበት በማንኛውም ስፍራ እርሷ ያደረገችው መታሰቢያ ሆኖ ይነገርላታል።”

10ከዚህ በኋላ ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ የሆነው የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ ሊሰጠው ወደ ካህናት አለቆች ሄደ። 11እነርሱም ይህን ሲሰሙ ደስ አላቸው፤ ገንዘብ ሊሰጡትም ቃል ገቡለት፤ ስለዚህ እርሱን አሳልፎ የሚሰጥበትን ምቹ ጊዜ ይጠባበቅ ነበር።

የጌታ እራት

14፥12-26 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥17-30ሉቃ 22፥7-23

14፥22-25 ተጓ ምብ – 1ቆሮ 11፥23-25

12የፋሲካ በግ በሚታረድበት በቂጣ በዓል የመጀመሪያው ቀን፣ ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሱስ ቀርበው፣ “የፋሲካ እራት የት እንድናዘጋጅልህ ትፈልጋለህ?” አሉት።

13እርሱም ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን እንዲህ ሲል ላካቸው፤ “ወደ ከተማ ሂዱ፤ እንስራ ውሃ የተሸከመ ሰው ይገናኛችኋል፤ 14ወደሚገባበት ቤትም ተከተሉት፤ የቤቱንም ጌታ፣ ‘መምህሩ፣ ከደቀ መዛሙርቴ ጋር የፋሲካን ራት የምበላበት የእንግዳ ማረፊያ የትኛው ነው?’ ብሏል በሉት፤ 15እርሱም በሰገነቱ ላይ የተሰናዳና የተነጠፈ ሰፊ አዳራሽ ያሳያችኋል፤ እዚያ አዘጋጁልን።”

16ደቀ መዛሙርቱም ወጥተው ወደ ከተማዪቱ ሄዱ፤ ማንኛውም ነገር ኢየሱስ እንዳላቸው ሆኖ አገኙት፤ ፋሲካውንም አሰናዱ።

17በመሸም ጊዜ ኢየሱስ ከዐሥራ ሁለቱ ጋር መጣ። 18በማእድ ላይ ሳሉም፣ “እውነት እላችኋለሁ፣ ከመካከላችሁ አንዱ፣ አብሮኝ የሚበላው እርሱ አሳልፎ ይሰጠኛል” አላቸው።

19እነርሱም ዐዘኑ፤ እያንዳንዳቸውም፣ “እኔ እሆንን?” ይሉት ጀመር።

20እርሱም እንዲህ አላቸው፤ “ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ፣ ከእኔ ጋር እጁን በወጭቱ ውስጥ የሚያጠልቀው ነው። 21የሰው ልጅስ ስለ እርሱ እንደ ተጻፈው ይሄዳል፤ የሰውን ልጅ አሳልፎ ለሚሰጥ ለዚያ ሰው ግን ወዮለት! ያ ሰው ባይወለድ ይሻለው ነበር።”

22ሲበሉም እንጀራ አንሥቶ ባረከ፤ ቈርሶም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸውና፣ “ዕንኩ፤ ይህ ሥጋዬ ነው” አላቸው።

23ጽዋውንም አነሣ፤ አመስግኖም ሰጣቸው፤ ሁሉም ከዚያ ጠጡ።

24ደግሞም እንዲህ አላቸው፤ “ይህ ስለ ብዙዎች የሚፈስስ የአዲስ14፥24 አንዳንድ ቅጆች “አዲስ” የሚለው ቃል የላቸውም። ኪዳን ደሜ ነው፤ 25እውነት እላችኋለሁ፤ በእግዚአብሔር መንግሥት አዲሱን የወይን ፍሬ እስከምጠጣበት እስከዚያች ቀን ድረስ ዳግም ይህን አልጠጣም።”

26ከዚህ በኋላ መዝሙር ዘምረው ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ወጡ።

ጴጥሮስ እንደሚክደው ኢየሱስ አስቀድሞ ተናገረ

14፥27-31 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥31-35

27ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “እንዲህ ተብሎ እንደ ተጻፈ፣ ሁላችሁ ትክዱኛላችሁ፤

“ ‘እረኛውን እመታለሁ በጎቹም ይበተናሉ’

28ከተነሣሁ በኋላ ግን፣ ቀድሜአችሁ ወደ ገሊላ እሄዳለሁ።”

29ጴጥሮስም፣ “ሁሉም ቢሰናከሉ እንኳ እኔ አላደርገውም” አለ።

30ኢየሱስም፣ “እውነት እልሃለሁ፤ በዚህች ሌሊት ዶሮ ሁለት14፥30 አንዳንድ የጥንት ቅጆች “ሁለት ጊዜ” የሚለው ሐረግ የላቸውም። ጊዜ ሳይጮኽ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ” አለው።

31ጴጥሮስም፣ “ከአንተ ጋር ብሞት እንኳ ከቶ አልክድህም” በማለት ይበልጥ አጽንቶ ተናገረ። ሁሉም ደግሞ እንደዚሁ አሉ።

ኢየሱስ በጌቴሴማኒ ጸለየ

14፥32-42 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥36-46ሉቃ 22፥40-46

32ከዚህ በኋላ ጌቴሴማኒ ወደሚባል ስፍራ ሄዱ፤ ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን፣ “እኔ ስጸልይ እናንተ እዚህ ቈዩ” አላቸው። 33ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስንም ይዞ ሄደ፤ እጅግ ያዝን ይጨነቅ ጀመር። 34ደግሞም፣ “ነፍሴ እስከ ሞት ድረስ እጅግ ዐዘነች፤ እዚሁ ሁኑና ነቅታችሁ ጠብቁ” አላቸው።

35ጥቂት ዕልፍ ብሎም በምድር ላይ በመውደቅ ቢቻል ሰዓቱ ከእርሱ እንዲያልፍ ጸለየና፣ 36“አባ14፥36 በአራማይክ ቋንቋ አባት የሚጠራበት ነው።፤ አባት ሆይ፤ ሁሉ ነገር ይቻልሃልና ይህን ጽዋ ከእኔ አርቀው፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ ሳይሆን የአንተ ፈቃድ ይሁን” አለ።

37ተመልሶም ሲመጣ ደቀ መዛሙርቱን ተኝተው አገኛቸው፤ ጴጥሮስንም እንዲህ አለው፣ “ስምዖን ሆይ፤ ተኝተሃልን? አንድ ሰዓት እንኳ ነቅተህ መጠበቅ አቃተህ? 38ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉ፤ ጸልዩም፤ መንፈስ ዝግጁ ነው፣ ሥጋ ግን ደካማ ነው።”

39እንደ ገናም ሄዶ መጀመሪያ የጸለየውን ደግሞ ጸለየ። 40ዳግመኛም ሲመለስ ዐይናቸውን እንቅልፍ ከብዶት ተኝተው አገኛቸው፤ የሚመልሱለትንም አያውቁም ነበር።

41ሦስተኛ ጊዜም መጥቶ እንዲህ አላቸው፤ “አሁንም እንደ ተኛችሁና እንዳረፋችሁ ናችሁ? ይበቃል! ሰዓቲቱ ደርሳለች፤ እነሆ፤ የሰው ልጅ ለኀጢአተኞች እጅ ዐልፎ ይሰጣል። 42ተነሡ፤ እንሂድ፤ አሳልፎ የሚሰጠኝ መጥቷል።”

ኢየሱስ ተያዘ

14፥43-50 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥47-56ሉቃ 22፥47-50ዮሐ 18፥3-11

43ወዲያው እየተናገረ ሳለ ከዐሥራ ሁለቱ አንዱ ይሁዳ መጣ፤ አብረውትም ሰይፍና ዱላ የያዙ፣ ከካህናት አለቆች፣ ከጸሓፍትና ከሽማግሌዎች የተላኩ ብዙ ሰዎች ነበሩ።

44አሳልፎ የሚሰጠውም፣ “እኔ የምስመው እርሱ ነውና ያዙት፤ ተጠንቅቃችሁም ውሰዱት” በማለት አስቀድሞ ምልክት ሰጥቷቸው ነበር። 45እንደ ደረሰም ወዲያው ወደ ኢየሱስ ቀርቦ፣ “መምህር ሆይ!” ብሎ ሳመው፤ 46ሰዎቹም ኢየሱስን ያዙት አሰሩትም። 47በአቅራቢያው ቆመው ከነበሩት አንዱ ሰይፉን መዝዞ የሊቀ ካህናቱን አገልጋይ ጆሮ ቈረጠ።

48ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፤ “እንደ ወንበዴ በሰይፍና በቈመጥ ልትይዙኝ መጣችሁን? 49በየዕለቱም በቤተ መቅደስ እያስተማርሁ ከእናንተ ጋር ስኖር አልያዛችሁኝም፤ መጻሕፍት ይፈጸሙ ዘንድ ይህ ሆነ።” 50በዚህ ጊዜ ሁሉም ትተውት ሸሹ።

51ዕርቃኑን ለመሸፈን በፍታ ያገለደመ አንድ ወጣት ኢየሱስን ይከተል ነበር። ሰዎቹም ይህን ወጣት በያዙት ጊዜ፣ 52ግልድሙን ጥሎ ዕራቍቱን ሸሸ።

ኢየሱስ በሸንጎ ፊት

14፥53-65 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥57-68ዮሐ 18፥121319-24

14፥61-63 ተጓ ምብ – ሉቃ 22፥67-71

53ኢየሱስንም ወደ ሊቀ ካህናቱ ወሰዱት፤ በዚያም የካህናት አለቆች፣ ሽማግሌዎችና ጸሐፍት ሁሉ ተሰበሰቡ። 54ጴጥሮስም ከሩቅ እየተከተለው፣ እስከ ሊቀ ካህናቱ ግቢ ዘለቀ፤ በዚያም ተቀምጦ ከሎሌዎቹ ጋር እሳት ይሞቅ ነበር።

55የካህናት አለቆችና ሸንጎው በሙሉ ኢየሱስን ለመግደል ምስክር ፈለጉ፤ ነገር ግን ማግኘት አልቻሉም። 56ብዙዎች በሐሰት ቢመሰክሩበትም፣ ቃላቸው አንድ ሊሆን አልቻለም። 57አንዳንዶቹም ተነሥተው እንዲህ ሲሉ በሐሰት መሰከሩበት፤ 58“ይህ፣ ‘የሰው እጅ የሠራውን ቤተ መቅደስ አፍርሼ፣ በሦስት ቀን ሌላ የሰው እጅ ያልሠራውን እሠራለሁ’ ሲል ሰምተነዋል።” 59ይህም ሆኖ፣ እንኳ ምስክርነታቸው አንድ አልሆነም።

60ሊቀ ካህናቱም ተነሥቶ በፊታቸው በመቆም፣ “እነዚህ በአንተ ላይ የሚመሰክሩት ምንድን ነው? ለምን አትመልስም?” በማለት ኢየሱስን ጠየቀው። 61ኢየሱስ ግን ዝም አለ፤ ምንም መልስ አልሰጠም።

ሊቀ ካህናቱም እንደ ገና፣ የቡሩኩ ልጅ፣ ክርስቶስ14፥61 ወይም መሲሑ አንተ ነህን? ሲል ጠየቀው።

62ኢየሱስም፣ “አዎን ነኝ፤ የሰው ልጅ በኀያሉ ቀኝ ሲቀመጥ፣ በሰማይ ደመናም ሲመጣ ታዩታላችሁ” አለ።

63ሊቀ ካህናቱም ልብሱን ቀደደና፣ እንዲህ አለ፤ “ሌላ ምን ምስክር ያስፈልገናል? 64ስድቡን ሰምታችኋል፤ ታዲያ ምን ይመስላችኋል?”

እነርሱም ሞት ይገባዋል በማለት በአንድ ቃል ፈረዱበት። 65በዚህ ጊዜ አንዳንዶቹ ይተፉበት ጀመር፤ ዐይኑንም ሸፍነው በጡጫ እየመቱት፣ “እስቲ ትንቢት ተናገር!” ይሉት ነበር። ሎሌዎችም በጥፊ እየመቱ ወሰዱት።

ጴጥሮስ ኢየሱስን አላውቀውም አለ

14፥66-72 ተጓ ምብ – ማቴ 26፥69-75ሉቃ 22፥56-62ዮሐ 18፥16-1825-27

66ጴጥሮስ በግቢው ውስጥ በታችኛው በኩል ሳለ፣ ከሊቀ ካህናቱ ገረዶች አንዲቱ መጣች፤ 67ጴጥሮስ እሳት ሲሞቅ አይታ ትኵር ብላ ተመለከተችውና፣ “አንተም ከናዝሬቱ ኢየሱስ ጋር ነበርህ” አለችው።

68እርሱ ግን፣ “የምትዪውን አላውቅም፤ አይገባኝምም” በማለት ካደ። ከዚያም ወደ መግቢያው በር ወጣ አለ፤ በዚህ ጊዜ ዶሮ ጮኸ።14፥68 አንዳድ ቅጆች “ዶሮ ጮኸ” የሚለው የላቸውም።

69ገረዲቱም ባየችው ጊዜ እዚያ ለቆሙት፣ “ይህ ሰው ከእነርሱ አንዱ ነው” ብላ እንደ ገና ተናገረች። 70እርሱ ግን አሁንም ካደ።

ከጥቂት ጊዜ በኋላ፣ በዚያ የቆሙት ሰዎች ጴጥሮስን፣ “የገሊላ ሰው እንደ መሆንህ መጠን፣ በርግጥ አንተ ከእነርሱ አንዱ ነህ” አሉት።

71እርሱ ግን፣ “እናንተ የምትሉትን ሰው እኔ አላውቀውም” እያለ ይምል ይገዘት ጀመር።

72ወዲያውም ዶሮ ሁለተኛ14፥72 አንዳንድ የጥንት ቅጆች “ሁለተኛ” የሚለው ቃል የላቸውም። ጮኸ። ጴጥሮስም፣ “ዶሮ ሁለት ጊዜ14፥72 አንዳንድ የጥንት ቅጆች “ሁለት ጊዜ” የሚለው ሐረግ የላቸውም። ከመጮኹ በፊት ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ” ያለው የኢየሱስ ቃል ትዝ አለው። ከዚያም ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי מרקוס 14:1-72

1יומיים לפני חג הפסח עדיין חיפשו ראשי הכוהנים וכמה ממנהיגי היהודים הזדמנות מתאימה לאסור את ישוע ולהוציאו להורג.

2”איננו יכולים לעצור אותו בפסח,“ אמרו לעצמם, ”מפני שהעם יעורר מהומות.“

3באותו זמן היה ישוע בבית־עניה, בביתו של שמעון המצורע. בשעת ארוחת הערב הופיעה אישה אחת עם פחית קטנה מלאה בשמן זך יקר מאוד. האישה הסירה את המכסה ויצקה את השמן על ראשו של ישוע.

4‏-5אחדים מן המסובים התמרמרו בינם לבין עצמם על ”הבזבוז“, כלשונם. ”מדוע את מבזבזת את השמן היקר הזה?“ התלוננו. ”יכולת למכור אותו ברווח, ואת הכסף לתת לעניים.“ 6”הניחו לה!“ נחלץ ישוע להגנתה.

”מדוע אתם מציקים לה? הלא היא עשתה מעשה טוב. 7העניים הנזקקים לעזרה נמצאים אתכם תמיד, ואתם יכולים לעזור להם בכל זמן שתרצו בכך, ואילו אני לא אשאר אתכם עוד זמן רב. 8היא עשתה מה שיכלה; היא משחה את גופי בשמן לפני קבורתי.

9”אני אומר לכם: בכל מקום שבו תוכרז הבשורה, תיזכר גם האישה הזאת, בזכות המעשה שעשתה.“

10לאחר מכן הלך יהודה איש־קריות, תלמידו של ישוע, אל ראשי הכוהנים כדי לתכנן את הסגרתו של ישוע.

11ראשי הכוהנים התלהבו ושמחו על כך שיהודה החליט להסגיר את ישוע, והבטיחו לתת לו כסף.

12ביום הראשון של חג הפסח, שבו הקריבו את זבח הפסח, שאלו התלמידים את ישוע היכן ברצונו לערוך את הסדר.

13ישוע שלח שניים מתלמידיו לירושלים, כדי לערוך את ההכנות הדרושות, ואמר: ”כשתלכו העירה יבוא לקראתכם אדם ובידו כד מים. לכו אחריו, 14היכנסו אל הבית שאליו ייכנס ואמרו לבעל הבית: ’רבנו שלח אותנו לראות את החדר שהכנת בשביל הסדר‘. 15הוא יוביל אתכם לחדר גדול שהכין למעננו בקומה השנייה, ושם תכינו את הסדר.“

16כשהגיעו השניים העירה הכול התרחש בדיוק כפי שאמר להם ישוע, והם הכינו את הסדר.

17ישוע ושאר התלמידים הגיעו לשם בערב. 18כשישבו לאכול בשולחן פתח ישוע ואמר: ”אמת אני אומר לכם, אחד מכם היושב עכשיו בינינו ואוכל איתנו יבגוד בי ויסגיר אותי.“

19התלמידים נמלאו צער רב, ושאלו: ”האם זה יהיה אני?“ 20”אחד מבין השנים־עשר שיטבול איתי את הלחם“, השיב ישוע. 21”בן־האדם הולך למות כפי שכתוב שצריך לקרות, אולם אני אומר לכם: אוי לו לאיש שיסגיר אותו; מוטב שלא היה נולד בכלל!“

22בעת הסעודה הוא לקח לחם (מצה), ברך עליו ופרס אותו לפרוסות. הוא הגיש את הפרוסות לתלמידיו ואמר: ”קחו, זהו גופי.“

23לאחר מכן לקח ישוע כוס יין, ברך, הגיש לתלמידיו וכולם שתו ממנה. 24”זהו דמי הנשפך למען רבים, דם הברית“, המשיך ישוע. 25”ואני אומר לכם שלא אשתה עוד יין עד היום שבו אשתה יין חדש במלכות האלוהים.“

26כל הנוכחים שרו מזמורי תהלים, ולאחר מכן הלכו להר הזיתים.

27”כולכם תעזבו אותי,“ אמר ישוע לתלמידיו, ”והרי כתוב: ’אכה את הרעה ותפוצין הצאן‘. 28אולם לאחר שאקום לתחייה אלך לגליל ואפגוש אתכם שם.“

29”יקרה מה שיקרה,“ קרא פטרוס, ”אני לעולם לא אעזוב אותך!“

30”דע לך, פטרוס,“ אמר ישוע, ”עד מחר בבוקר, לפני שיקרא התרנגול, אתה תתכחש לי שלוש פעמים.“

31”אני לעולם לא אתכחש לך, אפילו אם יהיה עלי למות יחד אתך!“ נשבע פטרוס, וכל האחרים גם אמרו כך.

32הם הגיעו לחורשת עצי־זית הנקראת ”גת־שמני“, וישוע אמר לתלמידיו: ”חכו לי כאן עד שאחזור. אני הולך להתפלל.“

33הוא לקח איתו את פטרוס, יעקב ויוחנן, ולפתע נמלא חרדה ומועקה מפני העומד לבוא עליו. 34”אני מתייסר עד מוות!“ אמר להם ישוע. ”חכו כאן… הישארו ערים….“

35הוא התרחק מהם מעט, כרע ברך על האדמה והתפלל שאלוהים יוותר לו על העומד לקרות לו, אם אכן אפשרי.

36”אבא,“ קרא ישוע, ”אתה כל יכול. אנא, הרחק ממני את כוס הייסורים. אולם לא כרצוני כי אם רצונך ייעשה!“

37לאחר מכן הוא חזר אל שלושת התלמידים ומצא אותם ישנים. ”שמעון,“ קרא ישוע לפטרוס, ”אתה ישן? האם לא יכולת להישאר ער שעה אחת בלבד? 38עמדו על המשמר והתפללו שלא תבואו לידי ניסיון. אני יודע שהרוח אכן רוצה, אבל גופכם חלש כל־כך!“

39ישוע הלך להתפלל שוב, וחזר על תחינתו לפני אלוהים. 40הוא חזר אל תלמידיו, וגם הפעם מצא אותם ישנים, כי עיניהם היו כבדות. הם לא ידעו כיצד לתרץ את הדבר.

41כשחזר אליהם ישוע בפעם השלישית הוא קרא: ”קומו! ישנתם מספיק? הגיעה השעה שבן־האדם יימסר לידי אנשים חוטאים. 42קומו, הבה נלך מכאן. הביטו, הנה מתקרב האיש שיסגיר אותי.“

43לפני שהספיק ישוע לסיים את דבריו הגיע למקום יהודה, אחד משנים־עשר התלמידים, ואיתו המון שנשלח מטעם ראשי הכוהנים והסופרים והזקנים. כולם היו מצוידים בחרבות ובמקלות.

44יהודה תיאם איתם מראש ואמר: ”אני אגש לישוע ואנשק אותו, כדי שתדעו מיהו ותוכלו לתפוס אותו ולהוביל אותו בלוית משמר.“ 45יהודה ניגש אליו. ”רבי!“ קרא יהודה כשהוא מחבק ומנשק אותו. 46ואז תפסו את ישוע ואסרו אותו. 47פטרוס שלף מיד את חרבו והכה באחד מהם שהתברר להיות משרתו של הכהן הגדול, וקיצץ את אוזנו.

48”מדוע אתם מתנפלים עלי בחרבות ובמקלות?“ שאל ישוע. ”האם אני פושע מסוכן? 49מדוע לא אסרתם אותי בבית־המקדש? הרי לימדתי שם בכל יום ויכולתם לתפוס אותי ללא התנגדות. אבל מה שכתוב צריך להתקיים.“

50בינתיים ברחו כל התלמידים. 51‏-52נער אחד שהתלווה לישוע לבש סדין בלבד. כשניסו לתפוס אותו, הנער השאיר את הסדין בידם וברח מפניהם ערום.

53ישוע נלקח אל בית הכוהן הגדול, ועד מהרה התאספו שם כל ראשי הכוהנים, הזקנים והסופרים. 54פטרוס הלך אחריהם במרחק מה ונכנס לחצר הכוהן הגדול. הוא התיישב בין המשרתים והתחמם ליד המדורה.

55ראשי הכוהנים וחברי הסנהדרין ניסו למצוא סיבה מספקת כדי להוציא את ישוע להורג, אך מאמציהם היו לשווא. 56עדי שקר רבים התנדבו להעיד נגדו, אולם עדויותיהם סתרו זו את זו.

57לבסוף קמו עדי שקר נוספים שהעידו: 58”שמענו אותו אומר: ’אני אהרוס את המקדש הזה שנבנה בידי אדם, ותוך שלושה ימים אקים מקדש אחר שאינו מעשה ידי אדם!‘ “ 59אולם עדות זאת גם לא הייתה מספקת.

60הכהן הגדול עמד באמצע החדר ושאל את ישוע: ”מה יש לך לומר להגנתך? מה יש לך לומר על כל ההאשמות נגדך?“ 61ישוע לא פצה את פיו, והכהן הגדול המשיך לשאול אותו: ”האם אתה המשיח בן־האלוהים?“

62”אני הוא,“ השיב ישוע, ”אתם עוד תראו את בן־האדם יושב לימין האלוהים, ובא בענני השמים.“

63הכהן הגדול התרגז מאוד וקרע את בגדיו מעליו. ”למה אנו זקוקים עוד?“ שאל בכעס. ”איננו זקוקים להוכחות נוספות! 64שמעתם את הגידופים שלו. מהו פסק־דינכם?“ הם הצביעו פה אחד בעד הוצאתו להורג.

65לאחר השמעת פסק־הדין החל קהל הנוכחים לירוק על ישוע ולהתעלל בו. הם קשרו את עיניו והכו אותו בכל גופו. ”נחש מי הכה אותך, נביא שכמותך?“ לעגו לו. גם השומרים שלקחו אותו משם הכו אותו באגרופים.

66‏-67כל אותו זמן היה פטרוס בחצר. אחת המשרתות בבית הכהן הגדול זיהתה את פטרוס שהתחמם ליד המדורה. היא הביטה בו בתשומת לב רבה והכריזה: ”אתה היית עם ישוע מנצרת!“ 68פטרוס הכחיש מיד את ההאשמה. ”אינני יודע כלל על מה את מדברת!“ אמר ועבר לקצה האחר של החצר.

לפתע נשמעה קריאת התרנגול.

69המשרתת ראתה אותו עומד שם ולא הרפתה ממנו. ”הנה אחד התלמידים של ישוע!“ קראה בקול.

70פטרוס שוב הכחיש את דבריה.

כעבור זמן מה קראו גם אלה שעמדו איתו ליד האש: ”הלא גם אתה אחד מהם? הרי יש לך מבטא גלילי!“

71פטרוס החל לקלל ונשבע: ”אני בכלל לא מכיר את האיש שעליו אתם מדברים!“

72באותו רגע קרא התרנגול בפעם השנייה.

לפתע נזכר פטרוס בדברי ישוע: ”לפני שיקרא התרנגול פעמיים, תתכחש לי שלוש פעמים.“ והוא פרץ בבכי.