ማርቆስ 15 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 15:1-47

ኢየሱስ በጲላጦስ ፊት

15፥2-15 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥11-26ሉቃ 23፥2318-25ዮሐ 18፥29–19፥16

1ጧት በማለዳ የካህናት አለቆች ከሽማግሌዎች፣ ከጸሓፍትና ከመላው የሸንጎ አባላት ጋር ወዲያው ከተማከሩ በኋላ፣ ኢየሱስን አስረው ወሰዱት፤ ለጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት።

2ጲላጦስም፣ “አንተ የአይሁድ ንጉሥ ነህን?”

ሲል ጠየቀው፤ ኢየሱስም፣ “አንተው አልኸው፣” በማለት መለሰለት።

3የካህናት አለቆችም በብዙ ነገር ከሰሱት። 4ጲላጦስም፣ “ለምን መልስ አትሰጥም? እነሆ፤ በብዙ ነገር ከስሰውሃል” ሲል እንደ ገና ጠየቀው።

5ኢየሱስ ግን ምንም አልመለሰም፤ ጲላጦስ ተገረመ።

6በበዓል ሕዝቡ እንዲፈታላቸው የሚጠይቁትን እስረኛ የመልቀቅ ልማድ ነበር። 7በዐመፃ ተነሣሥተው ነፍስ ከገደሉ ዐመፀኞች ጋር የታሰረ በርባን የሚባል አንድ ሰው ነበረ። 8ሕዝቡም መጥተው እንደተለመደው እንዲያደርግላቸው ጲላጦስን ለመኑት።

9ጲላጦስም፣ “የአይሁድን ንጉሥ እንድፈታላችሁ ትፈልጋላችሁን?” ሲል ጠየቃቸው፤ 10ምክንያቱም የካህናት አለቆች ኢየሱስን አሳልፈው የሰጡት በቅናት መሆኑን ያውቅ ነበር። 11የካህናት አለቆች ግን በርባንን በእርሱ ምትክ እንዲፈታላቸው እንዲጠይቁ ሕዝቡን አነሣሡ።

12ጲላጦስም እንደ ገና፣ “እንግዲያው የአይሁድ ንጉሥ የምትሉትን ምን እንዳደርገው ትፈልጋላችሁ?” አላቸው።

13እነርሱም እንደ ገና፣ “ስቀለው!” እያሉ ጮኹ።

14ጲላጦስም፣ “ለምን? ምን የፈጸመው ወንጀል አለ” አላቸው።

እነርሱ ግን፣ “ስቀለው!” እያሉ የባሰ ጮኹ።

15ጲላጦስም ሕዝቡን ደስ ለማሰኘት ሲል በርባንን ፈታላቸው፤ ኢየሱስን ግን ገርፎ እንዲሰቀል አሳልፎ ሰጠው።

ወታደሮች በኢየሱስ ላይ አፌዙ

15፥16-20 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥27-31

16ወታደሮቹ ፕራይቶሪዮን ወደ ተባለ ወደ ገዥው ግቢ ወሰዱት፤ ሰራዊቱንም ሁሉ በአንድነት ሰበሰቡ። 17ቀይ ልብስም አለበሱት፤ የእሾኽ አክሊል ጐንጕነው በራሱ ላይ ደፉበት። 18ከዚያም፣ “የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፤ ሰላም ለአንተ ይሁን!” እያሉ እጅ ነሡት፤ 19ራሱንም በበትር መቱት፤ ተፉበትም፤ ተንበርክከውም ሰገዱለት። 20ካፌዙበት በኋላም ቀዩን ልብስ ገፈፉት፤ የገዛ ልብሱን አለበሱት፤ ሊሰቅሉትም ወሰዱት።

የኢየሱስ ስቅለት

15፥22-32 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥33-44ሉቃ 23፥33-43ዮሐ 19፥17-24

21የአሌክሳንድሮስና የሩፎስ አባት ስምዖን የተባለ አንድ የቀሬና ሰው ከገጠር ሲመጣ መስቀሉን እንዲሸከም አስገደዱት። 22ከዚያም ኢየሱስን፣ ትርጕሙ “የራስ ቅል ስፍራ” ወደ ተባለ ወደ ጎልጎታ ወሰዱት። 23ከከርቤ ጋር የተቀላቀለ የወይን ጠጅም ሰጡት፤ እርሱ ግን አልተቀበለም። 24ከዚያም ሰቀሉት፤ እያንዳንዱም ምን እንደሚደርሰው ለማወቅ ዕጣ ተጣጥለው ልብሱን ተከፋፈሉ።

25ሲሰቅሉትም ጊዜው ከጧቱ ሦስት ሰዓት ነበረ። 26የክሱ ጽሑፍም፣ “የአይሁድ ንጉሥ” የሚል ነበር። 27ከእርሱም ጋር ሁለት ወንበዴዎችን አንዱን በቀኙ አንዱን በግራው ሰቀሉ። 28መጽሐፍ፣ “ከዐመፀኞች ጋር ተቈጠረ” ያለውም በዚሁ ተፈጸመ።15፥28 አንዳንድ ቅጆች 28 የላቸውም (ኢሳ 53፥12)። 29በመንገድ የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ የስድብ ናዳ በማውረድ እንዲህ ይሉት ነበር፤ “አዬ! ቤተ መቅደስን አፍርሰህ በሦስት ቀን የምትሠራ አንተ ነህ፤ 30እስቲ አሁን ከመስቀል ውረድና ራስህን አድን።”

31እንዲሁም የካህናት አለቆችና ጸሐፍት በማሾፍ እርስ በርሳቸው እንዲህ አሉ፤ “ሌሎችን አዳነ፤ ራሱን ግን ማዳን አልቻለም፤ 32አይተን እናምን ዘንድ ይህ ክርስቶስ15፥32 ወይም መሲሕ፣ ይህ የእስራኤል ንጉሥ እስቲ ከመስቀል ይውረድ።” ከእርሱ ጋር የተሰቀሉትም እንደዚሁ የስድብ ናዳ ያወርዱበት ነበር።

የኢየሱስ መሞት

15፥33-41 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥45-56ሉቃ 23፥44-49

33ከስድስት ሰዓት ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ። 34በዘጠኝም ሰዓት ኢየሱስ፣ “ኤሎሄ፣ ኤሎሄ፣ ላማ ሰበቅታኒ?” ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ፤ ትርጓሜውም “አምላኬ፣ አምላኬ፣ ለምን ተውኸኝ?” ማለት ነው።

35በዚያ ቆመው ከነበሩት አንዳንዶቹ ይህን ሲሰሙ፣ “ኤልያስን ይጣራል” አሉ።

36ከዚያም አንድ ሰው ፈጥኖ ሄዶ የሆመጠጠ የወይን ጠጅ በሰፍነግ ነከረ፤ በዘንግም ሰክቶ እንዲጠጣው ለኢየሱስ አቀረበለት፤ ከዚያም፣ “ተዉት፤ እስቲ ኤልያስ መጥቶ ሲያወርደው እናያለን” አለ።

37ኢየሱስም በታላቅ ድምፅ ጮኾ፤ ነፍሱን ሰጠ።

38የቤተ መቅደሱም መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ። 39በኢየሱስ ትይዩ ቆሞ የነበረውም የመቶ አለቃ እንደዚህ ጮኾ15፥39 አንዳንድ ቅጆች እንደዚህ ጮኾ የሚለው ሐረግ የላቸውም። ነፍሱን ሲሰጥ ባየ ጊዜ፣ “ይህ ሰው በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበር” አለ።

40በዚህ ጊዜ ሴቶች ከሩቅ ሆነው ይመለከቱ ነበር፤ ከእነርሱም መካከል መግደላዊት ማርያም፣ የታናሹ ያዕቆብና የዮሳ እናት ማርያም፣ እንዲሁም ሰሎሜ ነበሩ፤ 41እነዚህ ሴቶች በገሊላ ሲከተሉትና ሲያገለግሉት የነበሩ ናቸው፤ ደግሞም አብረውት ወደ ኢየሩሳሌም የመጡ ሌሎች ብዙ ሴቶች ነበሩ።

የኢየሱስ መቀበር

15፥42-47 ተጓ ምብ – ማቴ 27፥57-61ሉቃ 23፥50-56ዮሐ 19፥38-42

42ጊዜው እየመሸ መጥቶ የሰንበት ዋዜማ ይኸውም የመዘጋጀት ቀን ሆነ፤ 43የተከበረ የሸንጎ አባልና የእግዚአብሔርን መንግሥት ይጠባበቅ የነበረው የአርማትያሱ ዮሴፍ በድፍረት ወደ ጲላጦስ ሄዶ የኢየሱስን ሥጋ ለመነው። 44ጲላጦስም እንዲህ በቶሎ መሞቱን ሲሰማ ተደነቀ፤ የመቶ አለቃውንም ጠርቶ ከሞተ ምን ያህል ጊዜ እንደ ሆነ ጠየቀው፤ 45መሞቱንም ከመቶ አለቃው ካረጋገጠ በኋላ ሥጋውን ለዮሴፍ ሰጠው። 46ዮሴፍም በፍታ ገዛ፤ ሥጋውንም አውርዶ በበፍታው ከከፈነው በኋላ፣ ከዐለት በተወቀረ መቃብር አኖረው፤ የመቃብሩንም ደጃፍ በድንጋይ ገጠመው። 47ማርያም መግደላዊትና የዮሳ እናት ማርያም የት እንዳኖሩት ይመለከቱ ነበር።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

הבשורה על-פי מרקוס 15:1-47

1השכם בבוקר נפגשו ראשי הכוהנים, הזקנים, הסופרים וכל חברי הסנהדרין כדי להתייעץ על הצעד הבא. הם החליטו לשלוח את ישוע בליווי משמר מזוין אל פילטוס, המושל הרומאי.

2”האם אתה מלך היהודים?“ שאל פילטוס.

”אתה אומר“, השיב ישוע.

3‏-4ראשי הכוהנים האשימו אותו בפשעים רבים. ”מדוע אינך מגן על עצמך?“ שאל פילטוס בתמיהה. ”מה יש לך לומר?“ 5להפתעתו של פילטוס לא ענה ישוע דבר.

6כל שנה בחג הפסח נהג פילטוס להוציא לחופשי אסיר יהודי אחד, לפי בחירת העם. 7באותו זמן היה בכלא אסיר יהודי בשם בר־אבא, אשר הואשם ברצח (יחד עם אחרים) בעת אחת המרידות.

8בינתיים החל ההמון לבקש מפילטוס שישחרר אסיר אחד כמנהגו.

9”האם אתם רוצים שאוציא לחופשי את מלך היהודים?“ שאל פילטוס. 10הוא הציע לשחרר את ישוע, כי הבין שראשי הכוהנים אסרו אותו מתוך קנאה.

11אולם ראשי הכוהנים הסיתו את ההמון לדרוש את שחרורו של בר־אבא במקום שחרורו של ישוע.

12”אם אשחרר את בר־אבא, מה אעשה עם איש שאתם קוראים לו מלך היהודים?“ שאל פילטוס.

13”צלוב אותו!“ צעקו.

14”אבל מדוע?“ לא הבין פילטוס. ”מה עשה?“ הם לא ענו, ורק הגבירו את צעקותיהם: ”צלוב אותו!“

15פילטוס רצה למנוע מהומות אז נכנע לדרישת ההמון. על כן שחרר את בר־אבא מבית־הסוהר וציווה להלקות את ישוע בשוטים.

16‏-17לאחר מכן לקחו החיילים הרומאים את ישוע לחצר הארמון. הם קראו לכל חיילי המשמר, הלבישו את ישוע בגלימת ארגמן, הכינו לו זר מקוצים ארוכים ודוקרניים והניחו את הזר על ראשו. 18הם החלו ללעוג ולצחוק לו: ”יחי מלך היהודים!“ 19הם הכו אותו באכזריות, חבטו על ראשו במקלות, ירקו עליו, כרעו ברך לפניו והשתחוו לו בלעג.

20לאחר שסיימו החיילים להתלוצץ ולצחוק עליו, הפשיטו מעליו את הארגמן והלבישו אותו בבגדיו, והוציאו אותו החוצה לצליבה.

21החיילים פגשו בדרך את שמעון מקירניה (אביהם של אלכסנדר ורופוס), שחזר מהשדה, ואילצוהו לשאת את הצלב של ישוע למקום הצליבה.

22ישוע הובא למקום הנקרא ”גלגלתא“, כלומר ”מקום הגולגולת“. 23הם הגישו לו יין מסומם, אך הוא סרב לשתות. 24לאחר מכן הם צלבו אותו וערכו הגרלה על בגדיו.

25בשעה תשע בבוקר צלבו את ישוע.

26מעל ראשו היה תלוי שלט שאשמתו כתובה עליו: ”מלך היהודים“.

27באותו בוקר נצלבו איתו שני פושעים: אחד לימינו ואחד לשמאלו, 28וכך התקיים הפסוק:15‏.28 טו 28 ישעיהו נג 12 ”ואת פושעים נמנה.“

29העוברים והשבים קללו אותו, לעגו לו וקראו: ”נו, אתה יכול להרוס את בית המקדש ולבנותו מחדש בשלושה ימים? 30אם אתה גיבור כזה, מדוע אינך מציל את עצמך ויורד מהצלב?“ 31גם ראשי הכוהנים והסופרים עמדו סביבו ולעגו לו. ”הוא יכול להושיע את כולם חוץ מאשר את עצמו!“ צחקו.

32”משיח שכמוהו!“ קראו. ”מלך ישראל, הבה נראה אותו יורד מהצלב, ואז נאמין למה שהוא אומר!“ גם שני הפושעים שנצלבו איתו קיללו אותו.

33בשעה שתים־עשרה בצהריים כיסה חושך את כל הארץ למשך שלוש שעות.

34בשעה שלוש אחר־הצהריים זעק ישוע זעקת שבר: ”אלי, אלי, למה שבקתני?“ (כלומר, ”אלי, אלי, למה עזבתני?“15‏.34 טו 34 תהלים כב 2) 35אחדים מהאנשים שעמדו שם חשבו שהוא קורא לאליהו הנביא. 36איש אחד רץ והביא ספוג טבול בחומץ, שם אותו בקצה מוט ארוך והגיש אותו לישוע. ”הבה נראה אם אליהו באמת יבוא להוריד אותו!“ קרא האיש.

37באותו רגע זעק ישוע זעקת שבר נוספת ונפח את נשמתו.

38בבית־המקדש, הפרוכת התלויה לפני קודש הקודשים נקרעה לשניים מלמעלה למטה.

39קצין רומאי אחד, שעמד בין הצופים וראה כיצד נפח ישוע את נשמתו, קרא: ”האיש הזה באמת היה בן־אלוהים!“

40גם נשים עמדו במרחק מה וחזו בצליבה; ביניהן היו מרים המגדלית, מרים (אמם של יעקב ויוסי) ושלומית. 41כל אלה האמינו בישוע ואף שרתו אותו בהיותו בגליל. היו שם עוד נשים רבות אשר הלכו אחריו לירושלים.

42‏-43כל זה התרחש ביום שישי. עם רדת הערב, יהודי נכבד בשם יוסף מן הרמתיים ניגש לפילטוס וביקש את גופתו של ישוע. יוסף היה חבר בסנהדרין והאמין בביאת המשיח באותה עת. 44פילטוס לא האמין שישוע כבר מת, ולכן ביקש מאחד מקציניו שיוודא את הדבר. 45הקצין בדק ואישר שאכן ישוע כבר מת, ורק אז הרשה פילטוס ליוסף לקחת את הגופה.

46יוסף קנה סדין גדול, הוריד את גופת ישוע מהצלב, עטף אותה בסדין וקבר את ישוע בקבר חצוב בסלע. הוא סתם את פתח הקבר באבן גדולה. 47מרים המגדלית ומרים אמו של יוסי ראו את המקום שבו נקבר ישוע.