ማርቆስ 11 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 11:1-33

ኢየሱስ በታላቅ ክብር ወደ ኢየሩሳሌም ገባ

11፥1-10 ተጓ ምብ – ማቴ 21፥1-9ሉቃ 19፥29-38

11፥7-10 ተጓ ምብ – ዮሐ 12፥12-15

1ወደ ኢየሩሳሌም በደብረ ዘይት ተራራ አጠገብ ወዳሉት ወደ ቤተ ፋጌና ወደ ቢታንያ በቀረቡ ጊዜ፣ ኢየሱስ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን እንዲህ በማለት ላካቸው፤ 2“በፊታችሁ ወዳለው መንደር ሂዱ፣ ሰው ተቀምጦበት የማያውቅ የአህያ ውርንጫ እዚያ ታስሮ ታገኛላችሁ፤ ፈታችሁ አምጡት፤ 3ማንም፣ ‘ምን ማድረጋችሁ ነው?’ ቢላችሁ፣ ‘ለጌታ ያስፈልገዋል፤ በቶሎም መልሶ ይልከዋል’ ብላችሁ ንገሩት።”

4እነርሱም ሄዱ፤ በአንድ ቤት በራፍ መንገድ ላይ የአህያ ውርንጫ ታስሮ አገኙ፤ ፈቱትም። 5በዚያ ከቆሙት አንዳንድ ሰዎች፣ “ውርንጫውን የምትፈቱት ለምንድን ነው?” አሏቸው። 6ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስ ያላቸውን ለሰዎቹ በነገሯቸው ጊዜ ፈቀዱላቸው። 7ውርንጫውንም ወደ ኢየሱስ አምጥተው ልብሳቸውን በጀርባው ላይ አደረጉ፤ እርሱም ተቀመጠበት። 8ብዙ ሰዎች ልብሳቸውን በመንገድ ላይ አነጠፉ፤ ሌሎች ደግሞ ለምለም የዛፍ ቅርንጫፍ እየቈረጡ ያነጥፉ ነበር። 9ከፊቱ የቀደሙትና ከኋላው የተከተሉትም በታላቅ ድምፅ እንዲህ ይሉ ነበር፤

“ሆሣዕና!”11፥9 በዕብራይስጡ አድን! ማለት ሲሆን፣ ምስጋናን የሚገልጽ አባባል ነው፤ እንዲሁም 10 ይመ።

“በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው!”

10“የምትመጣው የአባታችን የዳዊት መንግሥት የተባረከች ናት!”

“ሆሣዕና በአርያም!”

11ኢየሱስም ኢየሩሳሌም ደረሰ፤ ከዚያም ወደ ቤተ መቅደስ ገባ፤ በዙሪያው ያለውንም ሁሉ ተመለከተ፤ ቀኑም ስለ መሸ ከዐሥራ ሁለቱ ጋር ወደ ቢታንያ ወጣ።

ኢየሱስ ቤተ መቅደስን አጸዳ

11፥12-14 ተጓ ምብ – ማቴ 21፥18-22

11፥15-18 ተጓ ምብ – ማቴ 21፥12-16ሉቃ 19፥45-47ዮሐ 2፥13-16

12በማግስቱም ከቢታንያ ሲወጡ ኢየሱስ ተራበ።

13እርሱም ቅጠል ያላት የበለስ ዛፍ ከሩቅ አየ፤ ምናልባት ፍሬ ይገኝባት እንደ ሆነ ብሎ ወደ እርሷ መጣ፤ ነገር ግን የበለስ ወራት አልነበረምና ከቅጠል በቀር ምንም አላገኘባትም። 14ከዚያም ዛፏን፣ “ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም ማንም ፍሬ ከአንቺ አይብላ” አላት። ደቀ መዛሙርቱም ይህን ሲናገር ሰሙ።

15ወደ ኢየሩሳሌምም መጡ፤ ከዚያም ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ፣ የሚሸጡትንና የሚገዙትን ያስወጣ ጀመር። የገንዘብ መንዛሪዎችን ጠረጴዛና የርግብ ሻጮችን መቀመጫ ገለባበጠ፤ 16ማንም ዕቃ ተሸክሞ በቤተ መቅደሱ ቅጥር ግቢ ውስጥ እንዳያልፍ ከለከለ። 17ሲያስተምራቸውም፣

“ ‘ቤቴ ለሕዝቦች ሁሉ የጸሎት ቤት ይባላል’

ተብሎ አልተጻፈምን? እናንተ ግን የሌቦች ዋሻ አደረጋችሁት!” አላቸው።

18የካህናት አለቆችና ጸሐፍትም፣ ይህን ሲሰሙ እንዴት እንደሚያጠፉት መንገድ ይፈልጉ ጀመር፤ ሕዝቡ ሁሉ በትምህርቱ በመገረማቸው ፈርተውታልና።

19በመሸም ጊዜ ከከተማዪቱ ወጥተው ሄዱ11፥19 አንዳንድ ቅጆች ወጥቶ ሄደ ይላሉ።

የበለሷ ዛፍ ደረቀች

11፥20-24 ተጓ ምብ – ማቴ 21፥19-22

20በማግስቱም ጧት በመንገድ ሲያልፉ፣ በለሲቱ ከነሥሯ ደርቃ አዩ። 21ጴጥሮስ ነገሩ ትዝ አለውና ኢየሱስን፣ “መምህር ሆይ፤ እነሆ፤ የረገምሃት በለስ ደርቃለች” አለው።

22ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “በእግዚአብሔር እመኑ11፥22 አንዳንድ የጥንት ቅጆች በእግዚአብሔር ላይ እምነት ካላችሁ ይላሉ።23እውነት እላችኋለሁ፤ ማንም ይህን ተራራ፣ ‘ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር’ ቢለውና ይህንም በልቡ ሳይጠራጠር ቢያምን ይሆንለታል። 24ስለዚህ በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ እንደ ተቀበላችሁት አድርጋችሁ ብታምኑ ይሆንላችኋል። 25እንዲሁም ለጸሎት በምትቆሙበት ጊዜ፣ የሰማዩ አባታችሁ ኀጢአታችሁን ይቅር እንዲልላችሁ፣ እናንተም በሰው ላይ ያላችሁን ሁሉ ይቅር በሉ። 26ይቅር ባትሉ ግን የሰማዩ አባታችሁ ኀጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።11፥26 አንዳንድ ቅጆች 26 የላቸውም።

በኢየሱስ ሥልጣን ላይ ጥያቄ ተነሣ

11፥27-33 ተጓ ምብ – ማቴ 21፥23-27ሉቃ 20፥1-8

27እንደ ገና ወደ ኢየሩሳሌም መጡ፤ ኢየሱስ በቤተ መቅደሱ ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚዘዋወርበት ጊዜ፣ የካህናት አለቆች፣ ጸሐፍትና የሕዝብ ሽማግሌዎች ወደ እርሱ ቀርበው፣ 28“እነዚህን ነገሮች የምታደርገው በምን ሥልጣን ነው? እነዚህን እንድታደርግስ ይህን ሥልጣን የሰጠህ ማን ነው?” አሉት።

29ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “እስቲ እኔም አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፤ መልሱልኝ፤ እኔም እነዚህን ነገሮች በምን ሥልጣን እንደማደርግ እነግራችኋለሁ። 30የዮሐንስ ጥምቀት ከሰማይ ነበረችን ወይስ ከሰው? መልሱልኝ።”

31እነርሱም እርስ በርሳቸው እንዲህ ተባባሉ፤ “ ‘ከሰማይ ነው’ ብንል፣ ‘ታዲያ ለምን አላመናችሁትም?’ ይለናል፤ 32‘ታዲያ፣ ከሰው ነው’ እንበልን?” ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስ እውነተኛ ነቢይ መሆኑን ያምኑ ስለ ነበር ፈሩ።

33ስለዚህ ለኢየሱስ “አናውቅም” ብለው መለሱለት።

ኢየሱስም፣ “እንግዲያው እኔም እነዚህን ነገሮች በምን ሥልጣን እንደማደርግ አልነግራችሁም” አላቸው።

Thai New Contemporary Bible

มาระโก 11:1-33

เสด็จเข้าสู่กรุงเยรูซาเล็มอย่างผู้พิชิต

(มธ.21:1-9; ลก.19:29-38; ยน.12:12-15)

1เมื่อพระเยซูและเหล่าสาวกมาใกล้กรุงเยรูซาเล็มถึงหมู่บ้านเบธฟายีและหมู่บ้านเบธานีที่ภูเขามะกอกเทศ พระเยซูทรงส่งสาวกสองคนไป 2ตรัสสั่งว่า “จงเข้าไปในหมู่บ้านข้างหน้านั้น พอเข้าเขตหมู่บ้านจะพบลูกลาตัวหนึ่งซึ่งยังไม่เคยมีใครขี่เลยผูกอยู่ จงแก้เชือกและจูงมาที่นี่ 3หากมีใครถามว่า ‘ท่านทำเช่นนี้ทำไม?’ จงบอกว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงต้องการลูกลานี้และประเดี๋ยวจะส่งกลับคืนให้ที่นี่’ ”

4เขาทั้งสองก็ไปและพบลูกลาผูกอยู่นอกประตูที่ถนน ขณะกำลังแก้เชือก 5บางคนซึ่งยืนอยู่แถวนั้นถามขึ้นมาว่า “ทำอะไร? เจ้าแก้เชือกผูกลูกลานั้นทำไม?” 6เขาก็ตอบตามที่พระเยซูทรงสั่งไว้ พวกนั้นจึงยอมให้มา 7เขานำลูกลามาให้พระเยซู แล้วเอาเสื้อคลุมของตนปูบนหลังลาให้พระองค์ประทับ 8ฝูงชนเป็นอันมากเอาเสื้อคลุมปูบนทาง บางคนตัดกิ่งไม้จากท้องทุ่งมาปู 9ฝูงชนทั้งที่นำเสด็จและตามเสด็จต่างโห่ร้องว่า

“โฮซันนา!11:9 ภาษาฮีบรูหมายความว่า “ช่วยให้รอด!” จึงกลายเป็นคำแสดงการสรรเสริญเช่นเดียวกับข้อ 10

“สรรเสริญพระองค์ผู้เสด็จมาใน

พระนามขององค์พระผู้เป็นเจ้า!”11:9 สดด.118:25,26

10“ขอให้อาณาจักรของดาวิดบรรพบุรุษของเราที่จะมานี้ จงเจริญ!”

“โฮซันนาในที่สูงสุด!”

11พระเยซูเสด็จเข้าสู่กรุงเยรูซาเล็มและไปยังพระวิหาร พระองค์ทอดพระเนตรทุกสิ่งแต่เนื่องจากใกล้ค่ำแล้วจึงทรงออกไปยังหมู่บ้านเบธานีกับสาวกทั้งสิบสองคน

พระเยซูทรงชำระพระวิหาร

(มธ.21:12-22; ลก.19:45-47; ยน.2:13-16)

12เช้าวันรุ่งขึ้นขณะออกจากหมู่บ้านเบธานีพระเยซูทรงหิว 13พระองค์ทรงเห็นต้นมะเดื่อใบดกแต่ไกลก็เสด็จเข้าไปดูว่ามีผลหรือไม่ เมื่อทรงพบว่ามีแต่ใบไม่มีผลเพราะยังไม่ถึงฤดูออกผล 14จึงตรัสแก่ต้นมะเดื่อนั้นว่า “ตั้งแต่นี้ไปจะไม่มีใครได้กินผลจากเจ้าเลย” และเหล่าสาวกได้ยินพระดำรัสนี้

15เมื่อมาถึงกรุงเยรูซาเล็มพระเยซูเสด็จเข้าไปในบริเวณพระวิหาร ทรงขับไล่บรรดาผู้ที่ซื้อขายของกันที่นั่น ทรงคว่ำโต๊ะของผู้รับแลกเงินและม้านั่งของบรรดาคนขายนกพิราบ 16และทรงห้ามไม่ให้ผู้ใดขนสินค้าผ่านลานพระวิหาร 17พระองค์ทรงสอนพวกเขาว่า “มีคำเขียนไว้ไม่ใช่หรือว่า

“ ‘นิเวศของเราจะได้ชื่อว่า

นิเวศแห่งการอธิษฐานสำหรับมวลประชาชาติ’11:17 อสย.56:7?

แต่พวกเจ้ามาทำให้กลายเป็น ‘ซ่องโจร’11:17 ยรม.7:11

18บรรดาหัวหน้าปุโรหิตและธรรมาจารย์ได้ยินดังนั้นก็เริ่มหาช่องทางที่จะฆ่าพระเยซู เพราะพวกเขากลัวพระองค์เนื่องจากประชาชนทั้งปวงเลื่อมใสในคำสอนของพระองค์

19พอตกเย็นพระเยซูกับสาวก11:19 ภาษากรีกว่าพวกเขาสำเนาต้นฉบับเก่าแก่บางสำเนาว่าพระองค์ก็ออกจากกรุง

ต้นมะเดื่อเหี่ยวเฉา

(มธ.21:19-22)

20ในเวลาเช้าขณะมาตามทางพวกเขาเห็นต้นมะเดื่อเหี่ยวเฉาไปจนถึงราก 21เปโตรนึกขึ้นได้จึงทูลพระเยซูว่า “รับบี ดูสิ! มะเดื่อที่ทรงสาบเหี่ยวเฉาไปแล้ว!”

22พระเยซูตรัสตอบว่า “จงเชื่อ11:22 สำเนาต้นฉบับเก่าแก่บางสำเนาว่าถ้าท่านเชื่อพระเจ้า 23เราบอกความจริงแก่ท่านว่าหากผู้ใดสั่งภูเขาลูกนี้ว่า ‘จงทิ้งตัวลงทะเลไป’ และใจไม่สงสัยเลยแต่เชื่อว่าจะเป็นไปตามที่เขาพูดก็จะเป็นจริงตามนั้น 24เหตุฉะนั้นเราบอกท่านว่าไม่ว่าท่านอธิษฐานทูลขอสิ่งใดจงเชื่อว่าจะได้รับแล้วท่านจะได้สิ่งนั้น 25เมื่อท่านยืนอธิษฐาน จงให้อภัยคนที่ท่านไม่พอใจ เพื่อพระบิดาของท่านในสวรรค์จะทรงอภัยบาปของท่าน11:25 สำเนาต้นฉบับบางสำเนาว่าบาปทั้งหลายของท่าน 26แต่หากท่านไม่ยอมยกโทษ พระบิดาของท่านในสวรรค์ก็จะไม่ทรงอภัยโทษบาปของท่านเหมือนกัน

ปัญหาเรื่องสิทธิอำนาจของพระเยซู

(มธ.21:23-27; ลก.20:1-8)

27เมื่อพวกเขามาถึงกรุงเยรูซาเล็มอีกครั้ง ขณะพระเยซูทรงดำเนินอยู่ในลานพระวิหาร พวกหัวหน้าปุโรหิต ธรรมาจารย์ และเหล่าผู้อาวุโสมาทูลถามพระองค์ว่า 28“ท่านทำสิ่งเหล่านี้โดยอาศัยสิทธิอำนาจใด? และใครให้สิทธิอำนาจท่านทำเช่นนี้?”

29พระเยซูตรัสตอบว่า “เราก็จะถามท่านสักข้อหนึ่ง จงตอบมาแล้วเราจะบอกว่าเราอาศัยสิทธิอำนาจใดทำสิ่งเหล่านี้ 30บัพติศมาของยอห์นมาจากสวรรค์หรือจากมนุษย์? จงบอกเรามา!”

31พวกเขาหารือกันว่า “ถ้าตอบว่า ‘มาจากสวรรค์’ เขาก็จะถามว่า ‘แล้วทำไมท่านไม่เชื่อยอห์น?’ 32แต่ถ้าจะว่า ‘มาจากมนุษย์’…” (พวกเขากลัวประชาชนเพราะทุกคนถือว่ายอห์นเป็นผู้เผยพระวจนะจริงๆ)

33ดังนั้นพวกเขาจึงทูลพระเยซูว่า “พวกเราไม่ทราบ”

พระเยซูตรัสว่า “เราก็จะไม่บอกพวกท่านเช่นกันว่าเราอาศัยสิทธิอำนาจใดทำสิ่งเหล่านี้”