ማርቆስ 12 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ማርቆስ 12:1-44

የወይን ስፍራ የተከራዩ ገበሬዎች ምሳሌ

12፥1-12 ተጓ ምብ – ማቴ 21፥33-46ሉቃ 20፥9-19

1ከዚያም እንዲህ እያለ በምሳሌ ይነግራቸው ጀመር፤ “አንድ ሰው ወይን ተከለ፤ ዙሪያውን ዐጠረ፤ ለመጭመቂያው ጕድጓድ ቈፈረ፤ የመጠበቂያም ማማ ሠራለት፤ ከዚያም ለገበሬዎች አከራይቶ ወደ ሌላ አገር ሄደ። 2በመከር ጊዜም ከወይኑ ፍሬ እንዲያመጣለት ከአገልጋዮቹ አንዱን ወደ ገበሬዎቹ ላከ። 3እነርሱ ግን ይዘው ደበደቡት፤ ባዶ እጁንም ሰደዱት። 4እንደ ገናም ሌላ አገልጋይ ላከ። እነርሱም ራሱን ፈንክተውና አዋርደው መለሱት። 5አሁንም እንደ ገና ሌላ ላከ፤ ይህኛውንም ገደሉት፤ ከሌሎች ከብዙዎቹ መካከል አንዳንዶቹን ደበደቡ፤ አንዳንዶቹንም ገደሉ።

6“አሁንም የሚላክ ሌላ ነበረው፤ እርሱም የሚወድደው ልጁ ነበረ፤ ‘ልጄንስ ያከብሩታል’ በማለት ከሁሉ በኋላ ላከው።

7“ገበሬዎቹ ግን እርስ በርሳቸው፣ ‘ይህማ ዋናው ወራሹ ነው፤ ኑ እንግደለው፤ ርስቱ የእኛ ይሆናል’ ተባባሉ፤ 8ከዚያም ይዘው ገደሉት፤ ከወይኑ ስፍራም አውጥተው ጣሉት።

9“እንግዲህ የወይኑ አትክልት ባለቤት ምን የሚያደርግ ይመስላችኋል? ይመጣል፤ ገበሬዎቹን ይገድላል፤ የወይኑንም አትክልት ለሌሎች ይሰጣል። 10እንዲህ የሚለውን የመጽሐፍ ቃል አላነበባችሁምን፤

“ ‘ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፣

እርሱ የማእዘን ራስ12፥10 ወይም የማእዘን ድንጋይ ሆነ፤

11ጌታ ይህን አድርጓል፣

ይህም ለዐይናችን ድንቅ ነው’?”

12ምሳሌውን የተናገረው ስለ እነርሱ መሆኑን ስላወቁ፣ ሊይዙት ፈለጉ፤ ነገር ግን ሕዝቡን ስለ ፈሩ ትተውት ሄዱ።

ለቄሳር ግብር ስለ መክፈል

12፥13-17 ተጓ ምብ – ማቴ 22፥15-22ሉቃ 20፥20-26

13ከዚያም በነገር እንዲያጠምዱት ከፈሪሳውያንና ከሄሮድስ ወገን ሰዎች ወደ እርሱ ላኩ። 14እነርሱም መጥተው እንዲህ አሉት፤ “መምህር ሆይ፤ አንተ ትክክለኛ ሰው መሆንህን እናውቃለን፤ የሰዎች ማንነት ስለማይገድህም አታዳላም፤ የእግዚአብሔርን መንገድ ብቻ በእውነት ታስተምራለህ፤ ለመሆኑ ለቄሳር ግብር መክፈል ይገባል ወይስ አይገባም? 15እኛስ እንክፈል ወይስ አንክፈል?”

ኢየሱስ ግን ግብዝነታቸውን ዐውቆ፣ “ለምን ልታጠምዱኝ ትፈልጋላችሁ? እስቲ አንድ ዲናር አምጡልኝና ልየው” አላቸው። 16እነርሱም አመጡለት፣ “ይህ የማን መልክ ነው? ጽሕፈቱስ የማን ነው?”

አላቸው፤ እነርሱም፣ “የቄሳር ነው” አሉት።

17ኢየሱስም፣ “የቄሳርን ለቄሳር፣ የእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር ስጡ” አላቸው። እነርሱም በእርሱ ተደነቁ።

ጋብቻና ትንሣኤ

12፥18-27 ተጓ ምብ – ማቴ 22፥23-33ሉቃ 20፥27-38

18ከዚህ በኋላ የሙታን ትንሣኤ የለም የሚሉ ሰዱቃውያን ወደ እርሱ መጥተው እንዲህ ሲሉ ጠየቁት፤ 19“መምህር ሆይ፤ የአንድ ሰው ወንድም ሚስት አግብቶ ልጅ ሳይወልድ ቢሞት፣ ይህ ሰው ሴትየዋን አግብቶ ለወንድሙ ዘር እንዲተካ ሙሴ ጽፎልናል። 20ታዲያ ሰባት ወንድማማቾች ነበሩ፤ የመጀመሪያው አግብቷት ዘር ሳይተካ ሞተ፤ 21ሁለተኛውም ሴትየዋን አገባት፤ እርሱም ዘር ሳይተካ ሞተ፤ ሦስተኛውም እንዲሁ፤ 22ሰባቱም አገቧት፤ ዘር ግን አልተኩም፤ በመጨረሻም ሴትየዋ ሞተች። 23እንግዲህ፣ ሰባቱም አግብተዋታልና በትንሣኤ12፥23 አንዳንድ ቅጆች በትንሣኤ ሰዎች ከሙታን ሲነሡ የሚል አላቸው ለማናቸው ሚስት ልትሆን ነው?” አሉት።

24ኢየሱስም፣ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “የምትስቱት እኮ ቅዱሳት መጻሕፍትንና የእግዚአብሔርን ኀይል ስለማታውቁ ነው! 25ሙታን በሚነሡበት ጊዜ እንደ ሰማይ መላእክት ይሆናሉ እንጂ አያገቡም፤ አይጋቡም። 26ስለ ሙታን መነሣት ግን፣ በሙሴ መጽሐፍ ይኸውም ስለ ቍጥቋጦው በተነገረው ክፍል፣ እግዚአብሔር ‘እኔ የአብርሃም አምላክ፣ የይስሐቅ አምላክ፣ የያዕቆብ አምላክ ነኝ’ ያለውን አላነበባችሁምን? 27እግዚአብሔር የሕያዋን አምላክ እንጂ የሙታን አምላክ አይደለም፤ ስለዚህ እጅግ ተሳስታችኋል።”

ከሁሉ የሚበልጠው ትእዛዝ

12፥28-34 ተጓ ምብ – ማቴ 22፥34-40

28ከጸሐፍትም አንዱ መጥቶ ሲከራከሩ ሰማቸው፤ ኢየሱስ ለቀረበለት ጥያቄ ተገቢውን መልስ መስጠቱን አስተውሎ፣ “ለመሆኑ ከትእዛዞች ሁሉ የሚበልጠው የትኛው ነው?” ሲል ጠየቀው።

29ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰለት፤ “ከሁሉ የሚበልጠው ይህ ነው፤ ‘እስራኤል ሆይ ስማ፤ ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው፤ 30አንተም ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ሐሳብህና በፍጹም ኀይልህ ውደድ።’ 31ሁለተኛውም ይህ ነው፤ ‘ባልንጀራህን እንደ ራስህ ውደድ።’ ከእነዚህም የሚበልጥ ትእዛዝ የለም።”

32ጸሓፊውም እንዲህ አለው፤ “መምህር ሆይ፤ መልካም ብለሃል፤ እርሱ አንድ መሆኑን፣ ከእርሱም ሌላ አለመኖሩን መናገርህ ትክክል ነው፤ 33እርሱን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም አእምሮህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም ኀይልህ መውደድ፣ እንዲሁም ባልንጀራህን እንደ ራስህ መውደድ ከሚቃጠል መሥዋዕት ሁሉና ከሌሎችም መሥዋዕቶች ይበልጣል።”

34ኢየሱስም በማስተዋል እንደ መለሰለት አይቶ፣ “አንተ ከእግዚአብሔር መንግሥት የራቅህ አይደለህም” አለው። ከዚህ በኋላ ሊጠይቀው የደፈረ ማንም አልነበረም።

ክርስቶስ የማን ልጅ ነው?

12፥35-37 ተጓ ምብ – ማቴ 24፥41-46ሉቃ 20፥41-44

12፥38-40 ተጓ ምብ – ማቴ 23፥1-7ሉቃ 20፥45-47

35ኢየሱስ በቤተ መቅደሱ አደባባይ በሚያስተምርበት ጊዜ እንዲህ ሲል ጥያቄ አቀረበ፤ “ጸሐፍት እንዴት ክርስቶስ የዳዊት ልጅ ነው ይላሉ? 36ዳዊት በመንፈስ ቅዱስ ሲናገር፣

“ ‘ጌታ ጌታዬን፣

“ጠላቶችህን ከእግርህ በታች

እስካደርጋቸው ድረስ

በቀኜ ተቀመጥ” ’ አለው። ይላል፤

37ታዲያ ዳዊት ራሱ ‘ጌታ’ ካለው፣ እንዴት ተመልሶ ልጁ ይሆናል?” ብዙ ሕዝብም በደስታ ይሰማው ነበር።

38በሚያስተምርበትም ጊዜ እንዲህ አለ፤ “ከጸሐፍት ተጠንቀቁ፤ የተንዘረፈፈ ቀሚስ ለብሰው መዞርን ይወድዳሉ፤ በየአደባባዩም የአክብሮት ሰላምታ ይሻሉ፤ 39በምኵራብ ከፍተኛውን ወንበር፣ በግብዣም ቦታ የከበሬታን ስፍራ ይፈልጋሉ፤ 40በረጅም ጸሎታቸው እያሳበቡ የመበለቶችን ቤት ያራቍታሉ፤ እነዚህ የባሰ ፍርድ ይቀበላሉ።”

የመበለቲቱ ስጦታ

12፥41-44 ተጓ ምብ – ሉቃ 21፥1-4

41ኢየሱስ በገንዘብ ማስቀመጫው አንጻር ተቀምጦ፣ ብዙ ሰዎች ስጦታቸውን ወደ ቤተ መቅደሱ ገንዘብ ማስቀመጫ ሣጥን ሲያስገቡ ይመለከት ነበር። ብዙ ሀብታሞች ብዙ ገንዘብ አስገቡ፤ 42አንዲት ምስኪን መበለት ግን ከአንድ ሳንቲም የማይበልጡ ሁለት የናስ ቤሳዎች አስገባች።

43ኢየሱስም ደቀ መዛሙርቱን ጠርቶ፣ እንዲህ አላቸው፤ “እውነት እላችኋለሁ፤ ይህች ድኻ መበለት ሣጥኑ ውስጥ ከጣሉት ከሌሎቹ የበለጠ አስገባች። 44እነዚህ ሁሉ ከተረፈው ሀብታቸው ሰጡ፤ እርሷ ግን በድኽነት ዐቅሟ ያላትን ሁሉ አውጥታ ለመኖሪያ የሚሆናትን እንዳለ ሰጠች።”

Thai New Contemporary Bible

มาระโก 12:1-44

คำอุปมาเรื่องผู้เช่าสวน

(มธ.21:33-46; ลก.20:9-19)

1แล้วพระองค์ตรัสคำอุปมาแก่พวกเขาว่า “ชายคนหนึ่งทำสวนองุ่น เขาล้อมรั้วกั้นสวน สกัดบ่อย่ำองุ่น และสร้างหอไว้เฝ้า จากนั้นให้ชาวสวนเช่าแล้วเดินทางจากไปต่างแดน 2เมื่อถึงฤดูเก็บเกี่ยวเขาส่งคนรับใช้มาหาผู้เช่าเพื่อรับส่วนแบ่งของผลผลิตจากสวนองุ่น 3แต่พวกผู้เช่าก็จับคนรับใช้นั้นทุบตีและไล่ให้กลับไปมือเปล่า 4เขาจึงส่งคนรับใช้อีกคนหนึ่งมาก็ถูกพวกนั้นฟาดหัวและทำให้อับอายขายหน้า 5เจ้าของยังส่งอีกคนหนึ่งมา พวกเขาก็ฆ่าคนนั้นเสีย เจ้าของส่งคนอื่นๆ มาอีกหลายคน บางคนก็ถูกทุบตี บางคนก็ถูกฆ่า

6“เหลืออยู่อีกคนเดียวที่จะส่งมาคือลูกชายที่เขารัก เขาส่งมาเป็นคนสุดท้ายเพราะคิดว่า ‘พวกเขาคงจะเคารพบุตรของเรา’

7“แต่พวกผู้เช่าพูดกันว่า ‘นี่ไงทายาท ให้เราฆ่าเขาแล้วมรดกจะตกเป็นของเรา’ 8พวกนั้นจึงจับเขาฆ่าแล้วโยนออกมานอกสวนองุ่น

9“แล้วเจ้าของสวนจะทำอย่างไร? เขาย่อมจะมาฆ่าผู้เช่าเหล่านั้นและให้คนอื่นเช่าสวนองุ่นนี้แทน 10พวกท่านไม่ได้อ่านพระคัมภีร์หรือที่ว่า

“ ‘ศิลาซึ่งช่างก่อได้ทิ้งแล้ว

บัดนี้กลับกลายเป็นศิลามุมเอก12:10 หรือศิลาหัวมุม

11องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ทรงกระทำการนี้

เป็นสิ่งมหัศจรรย์ในสายตาของเรา’12:11 สดด.118:22,23

12พวกเขารู้ว่าพระองค์ตรัสคำอุปมาต่อว่าพวกเขา พวกเขาจึงหาทางจับกุมพระองค์แต่ก็กลัวประชาชน ดังนั้นจึงละจากพระองค์ไป

การเสียภาษีแก่ซีซาร์

(มธ.22:15-22; ลก.20:20-26)

13ต่อมาพวกเขาส่งฟาริสีบางคนกับกลุ่มผู้สนับสนุนเฮโรดมาหาพระเยซูเพื่อจับผิดถ้อยคำของพระองค์ 14พวกนั้นมาทูลว่า “ท่านอาจารย์ เรารู้ว่าท่านเป็นคนซื่อตรงไม่เอนเอียงไปตามมนุษย์ เพราะท่านไม่เห็นแก่หน้าใครแต่สอนทางของพระเจ้าตามความจริง เป็นการถูกต้องหรือไม่ที่จะเสียภาษีให้แก่ซีซาร์? 15เราควรเสียหรือไม่ควรเสีย?”

แต่พระเยซูทรงรู้ทันความหน้าซื่อใจคดของเขาจึงตรัสว่า “พวกท่านมาจับผิดเราทำไม? เอาเหรียญหนึ่งเดนาริอันมาให้เราดูซิ” 16พวกเขาก็นำเหรียญมาถวายและพระองค์ตรัสถามพวกเขาว่า “รูปนี้เป็นของใคร? และคำจารึกเป็นของใคร?”

เขาทูลตอบว่า “ของซีซาร์”

17แล้วพระเยซูจึงตรัสกับพวกเขาว่า “ของของซีซาร์จงให้แก่ซีซาร์ และของของพระเจ้าจงถวายแด่พระเจ้า”

พวกเขาก็ทึ่งในพระองค์ยิ่งนัก

ปัญหาเรื่องการเป็นขึ้นจากตาย

(มธ.22:23-33; ลก.20:27-38)

18ฝ่ายพวกสะดูสีซึ่งกล่าวว่าไม่มีการเป็นขึ้นจากตายมาทูลถามพระองค์ว่า 19“ท่านอาจารย์ โมเสสเขียนสั่งพวกเราไว้ว่าถ้าชายใดเสียชีวิตไปโดยไม่มีบุตร ให้พี่ชายหรือน้องชายของเขาแต่งงานกับภรรยาม่ายเพื่อจะมีบุตรสืบสกุลให้ผู้นั้น 20คราวนี้มีพี่น้องเจ็ดคน พี่ชายคนโตแต่งงานแล้วตายไปโดยไม่มีบุตร 21คนที่สองจึงรับพี่สะใภ้มาเป็นภรรยา แต่แล้วก็ตายไปโดยไม่มีบุตร คนที่สามก็เช่นเดียวกัน 22จนมาถึงคนที่เจ็ด ทั้งหมดล้วนจากไปโดยไม่มีบุตร ท้ายที่สุดหญิงนั้นก็ตายด้วย 23เมื่อเป็นขึ้นจากตายหญิงผู้นี้จะเป็นภรรยาของใครในเมื่อทั้งเจ็ดคนล้วนได้นางเป็นภรรยา?”

24พระเยซูทรงตอบว่า “ท่านผิดแล้ว ที่เป็นเช่นนี้ก็เพราะท่านไม่รู้พระคัมภีร์และไม่รู้จักฤทธิ์เดชของพระเจ้าไม่ใช่หรือ? 25เมื่อเป็นขึ้นจากตายนั้นจะไม่มีการแต่งงานหรือยกให้เป็นสามีภรรยากันอีก แต่จะเป็นเหมือนทูตสวรรค์ 26ส่วนที่เกี่ยวกับการเป็นขึ้นจากตายนั้นพวกท่านยังไม่ได้อ่านหนังสือของโมเสสเรื่องพุ่มไม้นั้นหรือ? ที่พระเจ้าตรัสกับเขาว่า ‘เราเป็นพระเจ้าของอับราฮัม พระเจ้าของอิสอัค และพระเจ้าของยาโคบ’12:26 อพย.3:6? 27พระองค์ไม่ใช่พระเจ้าของคนตายแต่เป็นพระเจ้าของคนเป็น พวกท่านเข้าใจผิดไปมาก!”

พระบัญญัติข้อใหญ่ที่สุด

(มธ.22:34-40)

28ธรรมาจารย์คนหนึ่งได้ฟังการซักไซ้ไล่เลียงกันก็เห็นว่าพระเยซูทรงตอบได้ดี จึงทูลถามว่า “ในบรรดาพระบัญญัติทั้งสิ้นข้อไหนสำคัญที่สุด?”

29พระเยซูตรัสตอบว่า “ข้อที่สำคัญที่สุดคือ ‘อิสราเอลเอ๋ย จงฟังเถิด องค์พระผู้เป็นเจ้าพระเจ้าของเรา องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเป็นหนึ่ง12:29 หรือทรงเป็นองค์พระผู้เป็นเจ้าเดียว 30จงรักองค์พระผู้เป็นเจ้าพระเจ้าของท่านอย่างสุดใจ สุดจิต สุดความคิด และสุดกำลังของท่าน’12:30 ฉธบ.6:4,5 31ส่วนข้อที่สองคือ ‘จงรักเพื่อนบ้านเหมือนรักตนเอง’12:31 ลนต.19:18 ไม่มีบทบัญญัติใดใหญ่กว่าสองข้อนี้”

32คนนั้นทูลว่า “ท่านอาจารย์ตอบได้ดี ถูกอย่างที่ท่านกล่าวคือ พระเจ้าทรงเป็นหนึ่งและไม่มีใครอื่นนอกจากพระองค์ 33การรักพระองค์ด้วยสุดใจ สุดความเข้าใจ และสุดกำลังของท่าน และการรักเพื่อนบ้านเหมือนรักตนเองก็สำคัญยิ่งกว่าเครื่องเผาบูชาและเครื่องบูชาใดๆ ทั้งปวง”

34เมื่อพระเยซูทรงเห็นว่าเขาตอบอย่างมีปัญญาก็ตรัสกับเขาว่า “ท่านไม่ไกลจากอาณาจักรของพระเจ้า” ตั้งแต่นั้นมาไม่มีใครกล้ามาตั้งคำถามกับพระองค์อีก

พระคริสต์เป็นบุตรของใคร

(มธ.22:41—23:7; ลก.20:41-47)

35ขณะพระเยซูทรงสอนอยู่ในลานพระวิหาร พระองค์ตรัสถามว่า “เป็นไปได้อย่างไรที่พวกธรรมาจารย์บอกว่าพระคริสต์12:35 หรือพระเมสสิยาห์เป็นบุตรดาวิด? 36ดาวิดเองเมื่อกล่าวโดยพระวิญญาณบริสุทธิ์ก็ประกาศว่า

“ ‘พระเจ้าตรัสกับองค์พระผู้เป็นเจ้าของข้าพเจ้าว่า

“จงนั่งที่ขวามือของเรา

จนกว่าเราจะสยบศัตรูของเจ้า

ไว้ใต้เท้าของเจ้า” ’12:36 สดด.110:1

37ในเมื่อดาวิดเองเรียกพระองค์ว่า ‘องค์พระผู้เป็นเจ้า’ แล้วพระองค์จะเป็นบุตรของดาวิดได้อย่างไร?”

ฝูงชนกลุ่มใหญ่ฟังพระองค์ด้วยความชื่นชมยินดี

38ขณะที่พระเยซูทรงสอนพระองค์ตรัสว่า “จงระวังพวกธรรมาจารย์ เขาชอบสวมเสื้อชุดยาวเดินไปมา ชอบให้ผู้คนมาคำนับทักทายในย่านตลาด 39ชอบนั่งในที่สำคัญที่สุดในธรรมศาลาและที่อันทรงเกียรติในงานเลี้ยง 40เขาริบเรือนของหญิงม่าย และแสร้งอธิษฐานยืดยาวให้คนเห็น คนเช่นนี้จะถูกลงโทษอย่างหนักที่สุด”

เงินถวายของหญิงม่าย

(ลก.21:1-4)

41พระเยซูประทับอยู่ตรงหน้าที่รับเงินถวายของพระวิหาร ทรงเฝ้าดูฝูงชนนำเงินมาใส่ คนรวยหลายคนเอาเงินจำนวนมากมาเทลงไป 42แต่หญิงม่ายยากจนคนหนึ่งเอาเหรียญสองเหรียญ12:42 ภาษากรีกว่า2 เลฟตันมูลค่าแค่เศษเสี้ยวสตางค์12:42 ภาษากรีกว่า1 โคแดรนเทสมาถวาย

43พระเยซูทรงเรียกเหล่าสาวกมาและตรัสกับพวกเขาว่า “เราบอกความจริงแก่ท่านว่าหญิงม่ายยากจนคนนี้ถวายเข้าคลังพระวิหารมากกว่าคนอื่นๆ ทั้งหมด 44เพราะพวกเขาทั้งปวงล้วนเอาส่วนหนึ่งจากความมั่งคั่งของเขามาถวาย แต่หญิงม่ายนี้ทั้งที่ยากจนก็ยังเอาทุกสิ่ง คือทั้งหมดที่นางมีไว้เลี้ยงชีพมาถวาย”