መዝሙር 46 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 46:1-11

መዝሙር 4646 ርእስ ምናልባት የሙዚቃውን ሁኔታ ሊያሳይ ይችላል።

እግዚአብሔር ከእኛ ጋር

ለመዘምራን አለቃ፤ የቆሬ ልጆች መዝሙር፤ በደናግል የዜማ ስልት የሚዘመር መዝሙር።

1አምላካችን መጠጊያችንና ኀይላችን፣

በሚደርስብን መከራ ሁሉ የቅርብ ረዳታችን ነው።

2ስለዚህ ምድር ብትነዋወጥ እንኳ፣

ተራሮችም ወደ ባሕር ጥልቅ ቢሰምጡ አንፈራም።

3ውሆች ቢያስገመግሙ፣ ዐረፋ ቢደፍቁም፣ ተራሮችም ከውሆቹ ሙላት የተነሣ

ቢንቀጠቀጡም አንደናገጥም። ሴላ

4የእግዚአብሔርን ከተማ፣

የልዑልን የተቀደሰ ማደሪያ ደስ የሚያሰኙ የወንዝ ፈሳሾች አሉ።

5እግዚአብሔር በመካከሏ ነው፤ አትናወጥም፤

አምላክ በማለዳ ይረዳታል።

6ሕዝቦች በዐመፅ ተነሡ፤ መንግሥታትም ወደቁ፤

ድምፁን ከፍ አድርጎ አሰማ፤ ምድርም ቀለጠች።

7የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤

የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ

8ኑና የእግዚአብሔርን ሥራ፣

ምድርንም እንዴት ባድማ እንዳደረጋት እዩ።

9ከዳር እስከ ዳር ጦርነትን ከምድር ያስወግዳል፤

ቀስትን ይሰብራል፤ ጦርን ያነክታል፤

ጋሻንም46፥9 ወይም ሠረገላንም በእሳት ያቃጥላል።

10“ዕረፉ፤ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ ዕወቁ፤

በሕዝቦች ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፤

በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።”

11የሰራዊት አምላክ ከእኛ ጋር ነው፤

የያዕቆብ አምላክ መጠጊያችን ነው። ሴላ

Swedish Contemporary Bible

Psaltaren 46:1-12

Psalm 46

Gud är vår tillflykt

1För körledaren. Av Korachs ättlingar, till Alamót46:1 Betyder till unga kvinnor, kanske en musikalisk term eller benämning på en känd sång.. En sång.

2Gud är vår tillflykt och starkhet,

en beprövad hjälp i vår nöd.

3Därför är vi inte rädda även om jorden skulle skaka

och bergen störta ner i havsdjupen,

4även om dess vatten skulle brusa och skumma

och bergen skaka vid havets uppror. Séla

5Det går en flod vars strömmar gläder Guds stad,

till den Högstes heliga boning.

6Gud själv är i dess mitt, den ska aldrig vackla.

Gud hjälper den när morgonen gryr.

7Folken väsnas och riken faller.

Han höjer sin röst, och jorden förgås.

8Härskarornas Herre är med oss,

Jakobs Gud är vår borg. Séla

9Kom och se Herrens gärningar,

ödeläggelser som han gör på jorden.

10Han gör slut på krigen på jorden,

han bryter sönder bågen och bräcker spjutet,

han bränner upp sköldarna i eld.

11”Bli stilla och inse att jag är Gud,

upphöjd över folken, upphöjd över jorden.”

12Härskarornas Herre är med oss,

Jakobs Gud är vår borg. Séla