ምሳሌ 1 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 1:1-33

መግቢያ፤ የምሳሌዎቹ ዐላማና ጭብጥ

1የእስራኤል ንጉሥ፣ የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ምሳሌዎች፤

2ጥበብንና ተግሣጽን ለመቀበል፤

ጥልቅ ሐሳብ የሚገልጡ ቃላትን ለማስተዋል፤

3ጽድቅን፣ ፍትሕንና ሚዛናዊ ብያኔን በማድረግ፣

የተገራ ጠቢብ ልቦናን ለማግኘት፤

4ብስለት ለሌላቸው አስተዋይነትን፣

በዕድሜ ለጋ ለሆኑት ዕውቀትንና ልባምነትን ለመስጠት፤

5ጥበበኞች ያድምጡ፤ ትምህርታቸውንም ያዳብሩ፤

አስተዋዮችም መመሪያ ያግኙበት፤

6ይህም የጠቢባንን ምሳሌዎችና ተምሳሌቶች፣

አባባሎችና ዕንቈቅልሾች ይረዱ ዘንድ ነው።

7እግዚአብሔርን መፍራት የዕውቀት መጀመሪያ ነው፤

ተላሎች1፥7 በመጽሐፈ ምሳሌና በብሉይ ኪዳን ሌሎች መጻሕፍት ውስጥ ተላላ የሚለው በተደጋጋሚ ተጽፏል፤ ይህም የሞራል ጕድለትን ያመለክታል። ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ።

ጥበብን ገንዘብ ለማድረግ የተሰጠ ምክር

8ልጄ ሆይ፤ የአባትህን ምክር አድምጥ፤

የእናትህንም ትምህርት አትተው።

9ለራስህ ሞገስን የሚያጐናጽፍ አክሊል፣

ዐንገትህን የሚያስውብ ድሪ ይሆንልሃል።

10ልጄ ሆይ፤ ኀጢአተኞች ቢያባብሉህ፣

እሺ አትበላቸው፤

11“ከእኛ ጋር ናና፣ ደም ለማፍሰስ እናድባ፤

በደል በሌለበት ሰው ላይ እንሸምቅ፤

12እንደ መቃብር፣ ወደ ጕድጓድ1፥12 በዕብራይስጡ ሲኦል ይላል። እንደሚወርዱ፣

ከነሕይወታቸው እንዳሉ እንዋጣቸው፤

13ውድ የሆኑ ነገሮችን ሁሉ በየዐይነቱ እናገኛለን፤

ቤቶቻችንንም በዝርፊያ እንሞላለን፤

14ከእኛ ጋር ዕጣህን ጣል፤

የጋራ ቦርሳ ይኖረናል” ቢሉህ፣

15ልጄ ሆይ፤ አብረሃቸው አትሂድ፤

በሚሄዱበትም መንገድ እግርህን አታንሣ፤

16እግራቸው ወደ ኀጢአት ይቸኵላል፤

ደም ለማፍሰስም ፈጣኖች ናቸው።

17ወፎች ፊት እያዩ ወጥመድ መዘርጋት፣

ምንኛ ከንቱ ነው!

18እነዚህ ሰዎች የሚያደቡት በገዛ ደማቸው ላይ ነው፤

የሚሸምቁትም በራሳቸው ላይ ብቻ ነው።

19ያላግባብ ለጥቅም የሚሯሯጡ ሁሉ መጨረሻቸው እንዲህ ነው፤

የሕይወታቸው መጥፊያም ይኸው ነው።

ጥበብን ለሚያናንቁ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

20ጥበብ በጐዳና ላይ ጮኻ ትጣራለች፤

በየአደባባዩ ድምፅዋን ከፍ ታደርጋለች፤

21ዉካታ በበዛባቸው ጐዳናዎች ላይ1፥21 በዕብራይስጡና በሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች በቅጥሮች ጫፍ ላይ ይላሉ። ትጮኻለች፤

በከተማዪቱም መግቢያ በር ላይ እንዲህ ትላለች፤

22“እናንት ብስለት የሌላችሁ1፥22 በዕብራይስጡ ብስለት የሌለው የሚለው ቃል በዚህ መጽሐፍ በአጠቃላይ መልካም ምግባር የሌለውንና ክፋትን ለማድረግ ልቡ ያዘነበለ ሰውን ያመለክታል። ማስተዋል የሌለበት መንገዳችሁን እስከ መቼ ትወዱታላችሁ?

ፌዘኞች በፌዝ ደስ የሚሰኙት፣

ሞኞችስ ዕውቀትን የሚጠሉት እስከ መቼ ነው?

23ዘለፋዬን ብትሰሙኝ ኖሮ፣

ልቤን ባፈሰስሁላችሁ፣

ሐሳቤንም ባሳወቅኋችሁ ነበር።

24ነገር ግን በተጣራሁ ጊዜ እንቢ ስላላችሁኝ፣

እጄንም ስዘረጋ ማንም ግድ ስላልነበረው፣

25ምክሬን ሁሉ ስለ ናቃችሁ፣

ዘለፋዬንም ስላልተቀበላችሁ፣

26እኔ ደግሞ በመከራችሁ እሥቅባችኋለሁ፤

መዓት በሚወርድባችሁም ጊዜ አፌዝባችኋለሁ፤

27መዓት እንደ ማዕበል ሲያናውጣችሁ፣

መከራም እንደ ዐውሎ ነፋስ ሲጠራርጋችሁ፣

ሥቃይና ችግር ሲያጥለቀልቃችሁ አፌዝባችኋለሁ።

28“በዚያን ጊዜ ይጠሩኛል፤ እኔ ግን አልመልስላቸውም፤

አጥብቀው ይፈልጉኛል፤ ነገር ግን አያገኙኝም።

29ዕውቀትን ስለ ጠሉ፣

እግዚአብሔርንም መፍራት ስላልመረጡ፣

30ምክሬን ለመቀበል ስላልፈለጉ፣

ዘለፋዬን ስለ ናቁ፣

31የመንገዳቸውን ፍሬ ይበላሉ፤

የዕቅዳቸውንም ውጤት ይጠግባሉ።

32ብስለት የሌላቸውን ስድነታቸው ይገድላቸዋል፤

ተላሎችንም ቸልተኝነታቸው ያጠፋቸዋል፤

33የሚያዳምጠኝ ሁሉ ግን በሰላም ይኖራል፤

ክፉን ሳይፈራ ያለ ሥጋት ይቀመጣል።”

Swedish Contemporary Bible

Ordspråksboken 1:1-33

Vishetens välsignelse

(1:1—9:18)

1Ordspråk av Salomo, Davids son, Israels kung.

2Av dem får man fostran och vägledning,

så att man förstår de visas ord.

3Av dem får man vägledning till insikt

och till ett ärligt och rättfärdigt liv.

4De ger klokhet till de okunniga,

och lärdom till de unga om vad som är viktigt.

5Den vise hör dem och ökar sin kunskap.

Den kloke skaffar sig vägledning

6för att förstå ordspråk och liknelser,

de visas ord och gåtor.

7Herrens fruktan är vishetens början,

men den som är oklok föraktar vishet och vägledning.

8Hör, min son, din fars förmaning,

förkasta inte din mors undervisning.

9De bildar en skön krans på ditt huvud,

en vacker kedja kring din hals.

10Min son, låt dig inte lockas av syndare.

11De säger:

”Kom! Vi lägger oss i bakhåll för att döda,

för att lura på oskyldiga.

12Likt dödsriket slukar vi dem levande och hela,

så som de som läggs ner i graven.

13Vi ska få alla slags värdefulla ting

och kan fylla våra hus med plundrat gods.

14Du får vara med och dela,

pengarna kan vi ha i en gemensam kassa.”

15Min son, gå inte in på deras väg,

sätt inte din fot på deras stig,

16för med snabba steg söker de sig till ondskan,

och snabbt vill de utgjuta blod.

17Det är meningslöst att breda ut ett nät

inför ögonen på fåglarna.

18Dessa ligger på lur efter sitt eget blod

och i bakhåll för sina egna liv.

19Sådant blir slutet för den som roffar åt sig i oärlighet,

det kostar honom hans eget liv.

20Visheten ropar högt på gatan

och höjer sin röst på torget.

21Mitt bland de bullriga gatorna predikar den

och håller tal vid stadsportarna:

22”Hur länge ska ni okunniga älska okunnighet,

ni smädare njuta av smädelser,

ni dårar hata kunskap?

23Vänd om och ta emot min tillrättavisning,

så ska jag låta min ande komma över er

och dela med mig av min kunskap till er.

24Jag har ropat på er, men ni har inte lyssnat.

Jag har räckt ut min hand,

men ingen har brytt sig om den.

25Ni har struntat i alla mina råd

och avvisat min tillrättavisning.

26Därför ska jag också skratta åt er olycka

och håna er förtvivlan,

27när förskräckelsen griper tag i er som ett oväder

och olyckan sveper över er som en stormby,

när nöd och ångest drabbar er.

28Då kommer de att ropa till mig,

men jag ska inte svara.

De kommer att söka mig

men inte finna.

29De hatade kunskap

och ville inte frukta Herren,

30de avvisade mina råd

och föraktade mina tillrättavisningar.

31Därför får de äta sina gärningars frukt

och mätta sig med sina onda planer.

32De okunnigas avfällighet ska kosta dem livet

och dårarnas sorglöshet förgöra dem.

33Men den som lyssnar till mig ska leva i trygghet

och behöver inte vara rädd för något ont.”