መዝሙር 29 – NASV & NUB

New Amharic Standard Version

መዝሙር 29:1-11

መዝሙር 29

ለማዕበሉ ጌታ የቀረበ ውዳሴ

የዳዊት መዝሙር።

1እናንተ ኀያላን፣ ለእግዚአብሔር ስጡ፤

ክብርንና ብርታትን ለእግዚአብሔር ስጡ።

2ለስሙ የሚገባ ክብር ለእግዚአብሔር ስጡ፤

በቅድስናው ግርማ ለእግዚአብሔር ስገዱ።

3የእግዚአብሔር ድምፅ በውሆች ላይ ነው፤

የክብር አምላክ አንጐደጐደ፤

እግዚአብሔር በታላላቅ ውሆች ላይ አንጐደጐደ።

4የእግዚአብሔር ድምፅ ኀያል ነው፤

የእግዚአብሔር ድምፅ ግርማዊ ነው።

5የእግዚአብሔር ድምፅ ዝግባን ይሰብራል፤

እግዚአብሔር የሊባኖስን ዝግባ ይሰባብራል።

6ሊባኖስን እንደ ጥጃ፣

ስርዮንንም29፥6 አርሞንዔም የተባለው ተራራ ነው። እንደ አውራሪስ ግልገል ያዘልላል።

7የእግዚአብሔር ድምፅ

የእሳት ነበልባል ይረጫል።

8የእግዚአብሔር ድምፅ ምድረ በዳውን ያናውጣል፤

የእግዚአብሔር ድምፅ የቃዴስን ምድረ በዳ ያናውጣል።

9የእግዚአብሔር ድምፅ ወርካዎችን ይወዘውዛል፤29፥9 ወይም እግዚአብሔር አጋዘን እንድትወልድ ያደርጋል

ጫካዎችንም ይመነጥራል፤

ሁሉም በእርሱ ቤተ መቅደስ ሆኖ “ይክበር!” ይላል።

10እግዚአብሔር በጐርፍ ላይ ዙፋኑን ዘርግቶ ተቀምጧል፤29፥10 ወይም ይቀመጣል

እግዚአብሔር በንጉሥነቱ ለዘላለም በዙፋኑ ላይ ይቀመጣል።

11እግዚአብሔር ለሕዝቡ ብርታትን ይሰጣል፤

እግዚአብሔር ሕዝቡን በሰላም ይባርካል።

Swedish Contemporary Bible

Psaltaren 29:1-11

Psalm 29

Herrens ära och makt

1En psalm av David.

Ge Herren, ni Guds söner,

ge Herren ära och makt!

2Ära honom för hans härliga namn!

Böj er inför Herren i helig skrud29:2 Eller härlighet/glans, vilket i så fall syftar på Herren och inte på dem som uppmanas till tillbedjan..

3Herrens röst hörs över vattnen,

Gud, den upphöjde, dundrar.

Herrens röst hörs över de stora vattnen.

4Herrens röst är väldig,

Herrens röst är praktfull.

5Herrens röst knäcker cedrar,

Herren knäcker Libanons cedrar.

6Han får Libanon att hoppa som en kalv

och Sirjon som en vildoxe.

7Herrens röst slår med ljungande blixtar.

8Herrens röst skakar öknen,

Herren skakar Kadeshöknen.

9Herrens röst får hindarna att kalva,

den klär av träden i skogarna.

Allting i hans tempel ropar: ”Ära!”

10Herren satt på sin tron vid syndafloden,

Herren sitter på sin tron för evigt.

11Herren ger sitt folk styrka.

Herren välsignar sitt folk med frid.