መዝሙር 12 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 12:1-8

መዝሙር 12

ከክፉ ዓለም ለመዳን የቀረበ ጸሎት

ለመዘምራን አለቃ፤ በስምንተኛው ቅኝት የሚዘመር፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ ደግ ሰው የለምና አንተው ድረስልኝ!

ከሰዎችም መካከል አንድ ታማኝ አይገኝም።

2እርስ በርሳቸው ውሸት ይነጋገራሉ፤

በሽንገላ ከንፈርና በሁለት ልብ ይናገራሉ።

3ሸንጋዩን ከንፈር ሁሉ፣

ነገር የምታበዛውንም ምላስ እግዚአብሔር ያጥፋ!

4እነዚህም፣ “በአንደበታችን እንረታለን፤

ከንፈራችን የእኛ ነው፤12፥4 ወይም ከንፈራችን ማረሻ ምላጫችን ነው ጌታችንስ ማነው?”

የሚሉ ናቸው።

5እግዚአብሔር፣ “ስለ ድኾች መከራ፣

ስለ ችግረኞችም ጩኸት፣

አሁን እነሣለሁ፤

በናፈቁትም ሰላም አኖራቸዋለሁ” ይላል።

6የእግዚአብሔር ቃል የጠራ ቃል ነው፤

ሰባት ጊዜ እንደ ተጣራ፣

በምድር ላይ በከውር እንደ ተፈተነ ብር ነው።

7እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ትጠብቀናለህ፤

ከዚህም ትውልድ ለዘላለም ትከልለናለህ።

8በሰዎች ዘንድ ክፋት ከፍ ከፍ ባለ ጊዜ፣

ዐመፀኞች በየአቅጣጫው በዛቻ ይዞራሉ።

King James Version

Psalms 12:1-8

To the chief Musician upon Sheminith, A Psalm of David.

1Help, LORD; for the godly man ceaseth; for the faithful fail from among the children of men.12.1 upon…: or, upon the eighth12.1 Help: or, Save

2They speak vanity every one with his neighbour: with flattering lips and with a double heart do they speak.12.2 a double…: Heb. an heart and an heart

3The LORD shall cut off all flattering lips, and the tongue that speaketh proud things:12.3 proud: Heb. great

4Who have said, With our tongue will we prevail; our lips are our own: who is lord over us?12.4 are…: Heb. are with us

5For the oppression of the poor, for the sighing of the needy, now will I arise, saith the LORD; I will set him in safety from him that puffeth at him.12.5 puffeth…: or, would ensnare him

6The words of the LORD are pure words: as silver tried in a furnace of earth, purified seven times.

7Thou shalt keep them, O LORD, thou shalt preserve them from this generation for ever.12.7 them from: Heb. him, etc: that is, every one of them, etc

8The wicked walk on every side, when the vilest men are exalted.12.8 men: Heb. of the sons of the men