መዝሙር 13 – NASV & KJV

New Amharic Standard Version

መዝሙር 13:1-6

መዝሙር 13

በአምላኩ የታመነ ሰው አቤቱታ

ለመዘምራን አለቃ፤ የዳዊት መዝሙር።

1እግዚአብሔር ሆይ፤ እስከ መቼ ድረስ ለዘላለሙ ትረሳኛለህ?

ፊትህንስ ከእኔ የምትሰውረው እስከ መቼ ድረስ ነው?

2ከሐሳቤ ጋር የምሟገተው፣

ልቤም ቀኑን ሙሉ የሚያዝነው እስከ መቼ ነው?

ጠላቴስ በእኔ ላይ የሚያይለው እስከ መቼ ድረስ ነው?

3እግዚአብሔር አምላኬ ሆይ፤ ተመልከት፤

ስማኝም፤

የሞት እንቅልፍ እንዳልተኛ ዐይኖቼን አብራ፤

4በዚህም ጠላቴ፣ “አሸነፍሁት” እንዳይል፣

ባላጋራዎቼም በውድቀቴ ደስ እንዳይላቸው ርዳኝ።

5እኔ ግን በጸናች ፍቅርህ እታመናለሁ፤

ልቤም በማዳንህ ደስ ይለዋል።

6ቸርነቱ በዝቶልኛልና፣

ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ።

King James Version

Psalms 13:1-6

To the chief Musician, A Psalm of David.

1How long wilt thou forget me, O LORD? for ever? how long wilt thou hide thy face from me?13.1 chief…: or, overseer

2How long shall I take counsel in my soul, having sorrow in my heart daily? how long shall mine enemy be exalted over me?

3Consider and hear me, O LORD my God: lighten mine eyes, lest I sleep the sleep of death;

4Lest mine enemy say, I have prevailed against him; and those that trouble me rejoice when I am moved.

5But I have trusted in thy mercy; my heart shall rejoice in thy salvation.

6I will sing unto the LORD, because he hath dealt bountifully with me.