መሳፍንት 12 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 12:1-15

ዮፍታሔና ኤፍሬም

1የኤፍሬም ሰዎች ኀይላቸውን አሰባስበው ወደ ጻፎን በመሻገር ዮፍታሔን፣ “አሞናውያንን ለመውጋት ስትወጣ አብረንህ እንድንሄድ ያልጠራኸን ለምንድን ነው? ቤትህን በላይህ ላይ እናቃጥለዋለን አሉት።”

2ዮፍታሔም መልሶ እንዲህ አላቸው፤ “እኔና ሕዝቤ ከአሞናውያን ጋር ከፍተኛ ትግል ገጥመን በነበረበት ጊዜ ጠርቼያችሁ ከእጃቸው አላዳናችሁኝም፤ 3እኔም እንደማትረዱኝ በተረዳሁ ጊዜ በሕይወቴ ቈርጬ አሞናውያንን ለመውጋት ተሻገርሁ፤ እግዚአብሔርም ድሉን ሰጠኝ። ታዲያ ዛሬ እኔን ለመውጋት የመጣችሁት ለምንድን ነው?”

4ከዚያም ዮፍታሔ የገለዓድን ሰዎች አሰባስቦ ከኤፍሬም ጋር ተዋጋ። ኤፍሬማውያን ገለዓዳውያንን፣ “እናንተ ገለዓዳውያን ከኤፍሬምና ከምናሴ የከዳችሁ ናችሁ” ይሏቸው ስለ ነበር በብርቱ መቷቸው። 5ገለዓዳውያን ወደ ኤፍሬም የሚያሻግሩትን የዮርዳኖስን መልካዎች ያዙ። ታዲያ አምልጦ የሚሸሽ አንድ ኤፍሬማዊ ለመሻገር በሚጠይቃቸው ጊዜ፣ የገለዓድ ሰዎች “አንተ ኤፍሬማዊ ነህ?” ብለው ይጠይቁታል፤ ያም ሰው፣ “አይደለሁም” ብሎ ከመለሰላቸው፣ 6እስቲ “ሺቦሌት” በል ይሉታል፤ ቃሉን በትክክል ማለት ሳይችል ቀርቶ “ሲቦሊት” ካለ፣ ይዘው እዚያው እመልካው ላይ ይገድሉታል። በዚያ ጊዜም አርባ ሁለት ሺሕ ኤፍሬማውያን ተገደሉ።

7ዮፍታሔ በእስራኤል ላይ ለስድስት ዓመት ፈራጅ12፥7 በዚህ እንዲሁም በቍጥር 8-14 ላይ ባለው ክፍል በትውፊት መሳፍንት ይባላል። ሆነ። ገለዓዳዊው ዮፍታሔ ሞተ፤ ከገለዓድም ከተሞች በአንዲቱ ተቀበረ።

ኢብጻን፣ ኤሎም፣ ዔብዶን

8ከዮፍታሔ ቀጥሎ የቤተ ልሔሙ ኢብጻን በእስራኤል ላይ ፈራጅ ሆነ። 9እርሱም ሠላሳ ወንዶችና ሠላሳ ሴቶች ልጆች ነበሩት። ሴቶች ልጆቹንም ከጐሣው ውጭ ለሆኑ ሰዎች ዳራቸው፤ ከጐሣው ውጭ የሆኑ ሠላሳ ልጃገረዶች አምጥቶ ከወንዶች ልጆቹ ጋር አጋባቸው። ኢብጻን በእስራኤል ላይ ሰባት ዓመት ፈራጅ ሆነ። 10ኢብጻን ሞተ፤ በቤተ ልሔምም ተቀበረ።

11ከእርሱም በኋላ ዛብሎናዊው ኤሎም በእስራኤል ላይ ዐሥር ዓመት ፈራጅ ሆነ። 12ከዚያም ኤሎም ሞተ፤ በዛብሎን ምድር በኢያሎን ተቀበረ።

13ከኤሎም ቀጥሎ የጲርዓቶናዊው የሂሌል ልጅ ዓብዶን በእስራኤል ፈራጅ ሆነ። 14እርሱም በሰባ አህዮች ላይ የሚቀመጡ አርባ ወንዶች ልጆችና ሠላሳ ወንዶች የልጅ ልጆች ነበሩት፤ በእስራኤልም ላይ ስምንት ዓመት ፈራጅ ሆነ። 15ከዚያም የሂሌል ልጅ ዓብዶን ሞተ፤ ኰረብታማ በሆነው በአማሌቃውያን አገር በኤፍሬም ምድር በጲርዓቶን ተቀበረ።

Thai New Contemporary Bible

ผู้วินิจฉัย 12:1-15

เยฟธาห์และเอฟราอิม

1ชนเอฟราอิมระดมกำลังและข้ามมาที่ศาโฟน แล้วกล่าวกับเยฟธาห์ว่า “ทำไมท่านไปสู้รบกับคนอัมโมนโดยไม่เรียกพวกเราไปด้วย? เราจะเผาบ้านของท่านให้วอดวายลงมาทับศีรษะของท่าน”

2เยฟธาห์ตอบว่า “ข้าพเจ้ากับพรรคพวกรบติดพันในศึกครั้งใหญ่กับชาวอัมโมน และถึงแม้ข้าพเจ้าเรียกท่าน ท่านก็ไม่ได้มาช่วยข้าพเจ้าให้พ้นจากมือของพวกเขาเลย 3เมื่อข้าพเจ้าเห็นว่าท่านจะไม่ช่วย จึงเสี่ยงเอาชีวิตเข้าแลก ข้าพเจ้าข้ามออกไปสู้กับพวกอัมโมน และองค์พระผู้เป็นเจ้าก็ประทานชัยชนะเหนือพวกเขา เพราะเหตุใดท่านจึงยกพวกมาสู้กับข้าพเจ้าในวันนี้?”

4เยฟธาห์จึงระดมชาวกิเลอาดมาสู้กับชาวเอฟราอิม กิเลอาดพิชิตพวกเขาลงเพราะชาวเอฟราอิมกล่าวหาว่า “กิเลอาดเป็นพวกนอกคอกของเอฟราอิมและมนัสเสห์” 5ชาวกิเลอาดยึดท่าข้ามแม่น้ำจอร์แดนซึ่งจะไปสู่เอฟราอิม และเมื่อใดก็ตามที่ชาวเอฟราอิมซึ่งรอดชีวิตกล่าวว่า “ขอให้เราข้ามไปเถิด” ชาวกิเลอาดก็จะถามเขาว่า “ท่านเป็นชาวเอฟราอิมหรือ?” หากผู้นั้นตอบว่า “ไม่ได้เป็น” 6พวกเขาก็จะกล่าวว่า “ไหนลองพูดคำว่า ‘ชิบโบเลท’ ซิ” ถ้าเขาพูดว่า “สิบโบเลท” ก็จะถูกจับไปฆ่าที่ท่าข้ามแม่น้ำจอร์แดน เพราะว่าพวกเขาออกเสียงไม่ถูกต้อง คราวนั้นมีคนเอฟราอิมถูกจับไปฆ่าถึง 42,000 คน

7เยฟธาห์ชาวกิเลอาดวินิจฉัย12:7 หรือนำเช่นเดียวกับในข้อ 8-14อิสราเอลอยู่หกปี เมื่อเขาสิ้นชีวิตก็ถูกฝังไว้ในเมืองแห่งหนึ่งของกิเลอาด

อิบซาน เอโลน และอับโดน

8ผู้วินิจฉัยคนถัดมาของอิสราเอลคืออิบซานแห่งเบธเลเฮม 9เขามีบุตรชายสามสิบคน บุตรสาวสามสิบคน เขาให้บุตรสาวทั้งสามสิบคนแต่งงานกับชายตระกูลอื่นๆ และหาหญิงสาวสามสิบคนจากตระกูลอื่นมาเป็นภรรยาบุตรชายของตน เขาวินิจฉัยอิสราเอลอยู่เจ็ดปี 10เมื่อเขาสิ้นชีวิตก็ถูกฝังไว้ที่เบธเลเฮม

11ผู้วินิจฉัยคนต่อมาคือเอโลนแห่งเผ่าเศบูลุน เขาวินิจฉัยอิสราเอลอยู่สิบปี 12เมื่อเขาสิ้นชีวิตก็ถูกฝังไว้ที่อัยยาโลนในดินแดนเศบูลุน

13ผู้วินิจฉัยคนต่อมาคืออับโดนบุตรฮิลเลลจากปิราโธน 14เขามีบุตรชายสี่สิบคนและหลานชายสามสิบคน ซึ่งขี่ลาเจ็ดสิบตัว เขาวินิจฉัยอิสราเอลอยู่แปดปี 15เมื่อเขาสิ้นชีวิตก็ถูกฝังไว้ที่ปิราโธนในเอฟราอิม ดินแดนเทือกเขาของชาวอามาเลข