መሳፍንት 11 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 11:1-40

1ገለዓዳዊው ዮፍታሔ ኀያል ጦረኛ ነበረ፤ አባቱ ገለዓድ ነበር፤ እናቱም ጋለሞታ ነበረች። 2እንደዚሁም የገለዓድ ሚስት ለገለዓድ ወንዶች ልጆች ወለደችለት፤ እነርሱም ባደጉ ጊዜ ዮፍታሔን፣ “ከሌላ ሴት ስለ ተወለድህ ከቤተ ሰባችን ምንም ዐይነት ውርስ አይገባህም” በማለት አሳደዱት። 3ስለዚህም ዮፍታሔ ከወንድሞቹ ሸሽቶ መኖሪያውን ጦብ በተባለች ምድር አደረገ፤ እዚያም ወሮበሎች ተሰባስበው ተከተሉት።

4ከጥቂት ጊዜ በኋላም አሞናውያን በእስራኤል ላይ ጦርነት ባደረጉ ጊዜ፣ 5የገለዓድ አለቆች ዮፍታሔን ለማምጣት ወደ ጦብ ምድር ሄዱ። 6እነርሱም፣ “ከአሞናውያን ጋር መዋጋት እንችል ዘንድ መጥተህ ምራን” አሉት።

7ዮፍታሔም፣ “ምነው ጠልታችሁኝ ከአባቴ ቤት አሳድዳችሁኝ አልነበረምን? ታዲያ አሁን ችግር ሲገጥማችሁ ነው የምትፈልጉኝ?” አላቸው።

8የገለዓድ አለቆችም፣ “እንግዲህ አሁን ወደ አንተ መጥተናል፤ አሞናውያንን እንድንወጋ በል ተነሥና አብረን እንሂድ፤ በገለዓድ በምንኖረው በሁላችንም ላይ አለቃ ትሆናለህ” አሉት።

9ዮፍታሔም፣ “አሞናውያንን ለመውጋት ወደ አገሬ ብትመልሱኝና እግዚአብሔር በእጄ አሳልፎ ቢሰጣቸው በርግጥ አለቃችሁ እሆናለሁ?” ሲል ጠየቃቸው።

10የገለዓድ አለቆችም፣ “እግዚአብሔር ምስክራችን ነው፤ ያልኸውንም በርግጥ እናደርጋለን” አሉት። 11ስለዚህ ዮፍታሔ ከገለዓድ አለቆች ጋር ሄደ፤ ሕዝቡም በላያቸው ላይ አለቃና አዛዥ አደረጉት፤ ዮፍታሔም የተናገረውን ቃል ሁሉ ምጽጳ ላይ በእግዚአብሔር ፊት ደገመው።

12ከዚያም ዮፍታሔ ወደ አሞናውያን ንጉሥ፣ “ከእኔ ጋር ምን ጠብ ቢኖርህ ነው መጥተህ አገሬን የወጋኸው?” በማለት መልእክተኞች ላከ።

13የአሞናውያንም ንጉሥ ለዮፍታሔ መልእክተኞች፣ “ይህን ያደረግሁት እስራኤል ከግብፅ በወጣ ጊዜ በአርኖንና በያቦቅ ወንዞች መካከል ያለውንና እስከ ዮርዳኖስ ያለውን አገሬን ስለ ወሰዱብኝ ነው፤ አሁንም በሰላም መልሱልኝ” አላቸው።

14ዮፍታሔም መልእክተኞቹን እንደ ገና ወደ አሞናውያን ንጉሥ ላካቸው፤ 15እንዲህም አላቸው፤ “ዮፍታሔ እንዲህ ይላል፤ እስራኤል የሞዓብንም ሆነ የአሞናውያንን ምድር አልወሰደም። 16እስራኤል ከግብፅ በወጣ ጊዜ በምድረ በዳ አድርጎ ወደ ቀይ ባሕር11፥16 ዕብራይስጡ ያም ሶውፍ ይላል፤ ይህም የዳንኤል ባሕር ማለት ነው። ከዚያም ወደ ቃዴስ ሄደ። 17እስራኤልም ወደ ኤዶም ንጉሥ፣ ‘በአገርህ እንዳልፍ እባክህ ፍቀድልኝ’ በማለት መልእክተኞችን ላከበት፤ የኤዶም ንጉሥ ግን አልሰማውም። ለሞዓብ ንጉሥም እንደዚሁ ላከበት፤ እርሱም አልተቀበለውም፤ ስለዚህ እስራኤል በቃዴስ ተቀመጠ።

18“ቀጥሎም የኤዶምንና የሞዓብን ምድር በመዞር፣ በምድረ በዳው ተጕዞ ከሞዓብ በስተ ምሥራቅ በኩል በማለፍ ከአርኖን ማዶ ሰፈረ፤ የሞዓብም ድንበር አርኖን ስለ ነበር ወደ ሞዓብ ክልል አልገባም።

19“ከዚያም እስራኤል በሐሴቦን ወዳለው ወደ አሞራውያን ንጉሥ ወደ ሴዎን መልእክተኞች ልኮ፣ ‘ወደ ገዛ ስፍራችን ለመሄድ በአገርህ እንዳልፍ ፍቀድልኝ’ አለው። 20ሴዎን ግን በግዛቱ እንዲያልፍ ለመፍቀድ እስራኤልን አላመነውም11፥20 ወይም ከእስራኤል ጋር አልተስማማም፤ ሰራዊቱንም ሰብስቦ በያሃድ ከሰፈረ በኋላ ከእስራኤል ጋር ተዋጋ።

21“ከዚያም የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሴዎንንና ሕዝቡን ሁሉ በእስራኤል እጅ አሳልፎ ሰጣቸው፤ አሸነፏቸውም። እስራኤልም በዚያ አገር የሚኖሩትን የአሞራውያንን ምድር በሙሉ ወረሰ፤ 22ከአርኖን እስከ ያቦቅ፣ ከምድረ በዳው እስከ ዮርዳኖስ ድረስ ያለውን ምድር በሙሉ ወረሱ።

23“እንግዲህ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር አሞራውያንን ከሕዝቡ ከእስራኤል ፊት አሳድዶ ካስወጣቸው፣ አንተ ለመውሰድ ምን መብት አለህ? 24አምላክህ ካሞሽ የሰጠህን ይዞ ማቈየቱ ያንተ ፈንታ ነው፤ እኛም እንደዚሁ አምላካችን እግዚአብሔር የሰጠንን ሁሉ ርስት አድርገን እንወርሳለን። 25አንተ ከሞዓብ ንጉሥ ከሴፎር ልጅ ከባላቅ ትበልጣለህን? ለመሆኑ እርሱ ከእስራኤል ጋር ተጣልቷልን? ወይስ ተዋግቷልን? 26እስራኤልም በሐሴቦንና በመንደሮቿ፣ በአሮዔርና በመንደሮቿ፣ በአርኖንም አቅራቢያ ባሉት ከተሞች ሁሉ ሦስት መቶ ዓመት ተቀምጦ በነበረበት በዚያን ጊዜ ስለ ምን አልወሰዳችኋቸውም ነበር? 27እኔ አልበደልሁህም፤ አንተ ግን በእኔ ላይ ዘምተህ በድለኸኛል፤ እንግዲህማ ፈራጁ11፥27 ወይም መሪው እግዚአብሔር በእስራኤላውያንና በአሞናውያን መካከል ዛሬ ይፍረድ።”

28የአሞን ንጉሥ ግን ዮፍታሔ የላከውን መልእክት ከምንም አልቈጠረውም።

29ከዚያም የእግዚአብሔር መንፈስ በዮፍታሔ ላይ ወረደ፤ ተነሥቶም ገለዓድንና ምናሴን አቋርጦ ሄደ። ገለዓድ ባለችው በምጽጳ በኩል አድርጎም በአሞናውያን ላይ ዘመተባቸው። 30ዮፍታሔም እንዲህ ሲል ለእግዚአብሔር ተሳለ፤ “አሞናውያንን በእጄ አሳልፈህ ብትሰጠኝ፣ 31አሞናውያንን ድል አድርጌ በምመለስበት ጊዜ በመጀመሪያ ሊቀበለኝ ከቤቴ ደጅ የሚወጣው ማንኛውም ሰው ለእግዚአብሔር ይሆናል፤ እኔም የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጌ አቀርበዋለሁ።”

32ከዚያም ዮፍታሔ አሞናውያንን ለመውጋት ወጣ፤ እግዚአብሔርም እርሱን በእጁ አሳልፎ ሰጠው። 33ከአሮዔር አንሥቶ እስከ ሚኒት አካባ፣ ከዚያም ዐልፎ እስከ ክራሚም የሚገኙትን ሃያ ከተሞች ፈጽሞ አጠፋቸው፤ አሞናውያንም ለእስራኤል ተገዙ።

34ዮፍታሔ ምጽጳ ወዳለው ቤቱ ተመለሰ። እነሆ፤ ልጁ አታሞ እየደለቀች በመዝፈን ልትቀበለው ወጣች፤ እርሷም አንዲት ልጁ ብቻ ነበረች፤ ከእርሷ በቀር ወንድም ሆነ ሴት ልጅ አልነበረውም። 35ባያትም ጊዜ ልብሱን በመቅደድ፣ “ወይኔ ልጄ ጕድ አደረግሽኝ! ጭንቅም ላይ ጣልሽኝ፤ ማስቀረት የማልችለውን ስእለት ለእግዚአብሔር ተስያለሁና” ብሎ በሐዘን ጮኸ።

36እርሷም እንዲህ አለች፤ “አባቴ ሆይ፤ መቼም አንዴ ለእግዚአብሔር ቃል ገብተሃል፤ ጠላቶችህን አሞናውያንን አሁን እግዚአብሔር ተበቅሎልሃልና ቃል የገባኸውን ፈጽምብኝ። 37ነገር ግን አንድ ነገር ብቻ እንድትፈቅድልኝ እለምንሃለሁ፤ ከእንግዲህ ባል ስለማላገባ ከባልንጀሮቼ ጋር ወደ ተራሮች ወጥቼ እየዞርሁ ሁለት ወር እንዳለቅስ አሰናብተኝ።”

38እርሱም፣ “በይ ሂጂ” ብሎ ለሁለት ወር አሰናበታት፤ እርሷም ከእንግዲህ ባል ስለማታገባ ከልጃገረድ ጓደኞቿ ጋር ወደ ተራሮች ሄደው አለቀሱ። 39ከሁለት ወር በኋላ ወደ አባቷ ተመለሰች፤ እርሱም የተሳለውን አደረገ፤ ድንግልም ነበረች።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ይህ በእስራኤል ልማድ ሆኖ፣ 40የእስራኤል ወጣት ሴቶች የገለዓዳዊውን የዮፍታሔን ልጅ በማሰብ በየዓመቱ እየወጡ የአራት ቀን ሐዘን ያደርጉላታል።

Thai New Contemporary Bible

ผู้วินิจฉัย 11:1-40

1เยฟธาห์ชาวกิเลอาดเป็นนักรบเกรียงไกร บิดาของเขาคือกิเลอาด แต่มารดาของเขาเป็นหญิงโสเภณีคนหนึ่ง 2ภรรยาของกิเลอาดมีบุตรชายหลายคน และเมื่อพวกเขาโตขึ้นก็ขับไล่ไสส่งเยฟธาห์ พวกเขากล่าวว่า “เจ้าจะไม่ได้กรรมสิทธิ์ใดๆ ในครอบครัวของเรา เพราะเจ้าเป็นลูกของหญิงอื่น” 3ดังนั้นเยฟธาห์จึงหนีพี่น้องไปตั้งถิ่นฐานในแผ่นดินโทบ ซึ่งมีพวกนักเลงมาเข้าเป็นสมัครพรรคพวก

4ต่อมาเมื่อชาวอัมโมนรบกับอิสราเอล 5บรรดาผู้อาวุโสของกิเลอาดไปตามตัวเยฟธาห์มาจากแผ่นดินโทบ 6พวกเขากล่าวว่า “ขอเชิญมาเป็นแม่ทัพของเรา เพื่อเราจะสู้รบกับชาวอัมโมนได้”

7เยฟธาห์กล่าวกับพวกเขาว่า “ท่านเกลียดข้าพเจ้าและไล่ข้าพเจ้าออกมาจากบ้านบิดาไม่ใช่หรือ? ทำไมตอนนี้เดือดร้อนก็มาหาข้าพเจ้า?”

8เหล่าผู้อาวุโสของกิเลอาดตอบเขาว่า “ถึงอย่างไรตอนนี้เราก็กลับมาหาท่านแล้ว ไปสู้พวกอัมโมนร่วมกับเราเถิด แล้วท่านจะได้เป็นหัวหน้าของพวกเราทั้งหมดในกิเลอาด”

9เยฟธาห์ตอบว่า “หากท่านพาข้าพเจ้ากลับไปสู้ชาวอัมโมน และองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงมอบพวกเขาแก่ข้าพเจ้าแล้ว ข้าพเจ้าจะได้เป็นหัวหน้าของพวกท่านแน่หรือ?”

10เหล่าผู้อาวุโสของกิเลอาดตอบว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าเป็นพยาน เราจะทำตามที่ท่านพูดแน่นอน” 11ดังนั้นเยฟธาห์จึงไปกับพวกเขา และประชาชนก็ตั้งเขาให้เป็นหัวหน้าและแม่ทัพของพวกเขา แล้วเยฟธาห์จึงย้ำทุกถ้อยคำที่พูดกับเหล่าผู้อาวุโสของกิเลอาดต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าที่มิสปาห์

12แล้วเยฟธาห์ส่งผู้สื่อสารไปพบกษัตริย์อัมโมนและถามว่า “ท่านขัดแย้งอะไรกับเราหรือ จึงมาโจมตีประเทศของเรา?”

13กษัตริย์อัมโมนตอบกลับมาว่า “เมื่ออิสราเอลออกมาจากอียิปต์ พวกเขาได้ยึดดินแดนของเราไปตั้งแต่แม่น้ำอารโนนถึงแม่น้ำยับบอก ตลอดจนถึงแม่น้ำจอร์แดน บัดนี้จงคืนดินแดนมาแต่โดยดี”

14เยฟธาห์ส่งผู้สื่อสารกลับไปยังกษัตริย์อัมโมน 15พร้อมคำตอบว่า

“เยฟธาร์กล่าวดังนี้ว่า อิสราเอลไม่ได้ยึดดินแดนของโมอับหรือของอัมโมน 16แต่เมื่ออิสราเอลออกมาจากอียิปต์ ผ่านถิ่นกันดารไปจนถึงทะเลแดง และมาถึงคาเดชแล้ว 17จากนั้นอิสราเอลได้ส่งผู้สื่อสารไปพบกษัตริย์เอโดมและกล่าวว่า ‘ขอให้เราผ่านดินแดนของท่าน’ แต่กษัตริย์เอโดมไม่ยอม อิสราเอลส่งคนไปพบกษัตริย์โมอับด้วย แต่ก็ถูกปฏิเสธ ดังนั้นอิสราเอลจึงยังคงอยู่ที่คาเดช

18“จากนั้นพวกเขาเดินทางผ่านถิ่นกันดาร และอ้อมดินแดนเอโดมและโมอับ ผ่านถิ่นกันดารไปตามแนวชายแดนฝั่งทิศตะวันออกของโมอับ และตั้งค่ายอีกฟากหนึ่งของแม่น้ำอารโนน แต่ไม่เคยรุกล้ำเข้าไปในดินแดนโมอับเลย เพราะแม่น้ำอารโนนเป็นพรมแดนของดินแดนนั้น

19“แล้วอิสราเอลก็ส่งผู้สื่อสารไปพบกษัตริย์สิโหนของชาวอาโมไรต์ผู้ครอบครองอยู่ที่เฮชโบน และกล่าวกับเขาว่า ‘ขอให้เราผ่านแดนของท่านไปยังดินแดนของเรา’ 20แต่กษัตริย์สิโหนก็ไม่เชื่อใจ11:20 หรือไม่ตกลงที่จะให้อิสราเอลผ่านดินแดนของตน กลับยกทัพใหญ่มาที่ยาฮาสและสู้รบกับอิสราเอล

21“แล้วพระยาห์เวห์พระเจ้าของอิสราเอลจึงทรงมอบกษัตริย์สิโหนกับไพร่พลทั้งปวงของเขาไว้ในมืออิสราเอล อิสราเอลจึงมีชัยเหนือพวกเขา และยึดครองดินแดนทั้งหมดของชาวอาโมไรต์ 22จากแม่น้ำอารโนนจดแม่น้ำยับบอก และจากถิ่นกันดารจดแม่น้ำจอร์แดน

23“ในเมื่อพระยาห์เวห์พระเจ้าของอิสราเอลทรงขับไล่ชาวอาโมไรต์ออกไปต่อหน้าอิสราเอลประชากรของพระองค์ บัดนี้ท่านมีสิทธิ์อะไรจะยึดคืน? 24ท่านจะไม่รับสิ่งที่พระเคโมชของท่านยกให้ท่านหรือ? ถ้าท่านเองยังรับ เราก็จะครอบครองทุกสิ่งที่พระยาห์เวห์พระเจ้าของเราทรงประทานแก่เราเช่นกัน 25ท่านเหนือกว่ากษัตริย์บาลาคแห่งโมอับบุตรของศิปโปร์หรือ? เขาเคยทะเลาะหรือสู้รบกับอิสราเอลหรือ? 26ตลอดสามร้อยปีอิสราเอลครอบครองเฮชโบน อาโรเออร์ และดินแดนโดยรอบ และเมืองต่างๆ เลียบแม่น้ำอารโนน ทำไมท่านจึงไม่มาเอาคืนตั้งแต่ตอนนั้น? 27ข้าพเจ้าไม่ได้ทำผิดต่อท่าน ท่านต่างหากเป็นฝ่ายผิดที่ยกทัพมารบกับข้าพเจ้า ขอให้พระยาห์เวห์องค์ตุลาการ11:27 หรือผู้ครอบครองทรงตัดสินกรณีพิพาทระหว่างชาวอิสราเอลกับชาวอัมโมนในวันนี้”

28แต่กษัตริย์อัมโมนไม่ใส่ใจกับสาส์นของเยฟธาห์เลย

29แล้วพระวิญญาณขององค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอยู่เหนือเยฟธาห์ เขาข้ามกิเลอาดและมนัสเสห์ ผ่านมิสปาห์แห่งกิเลอาด และเข้าโจมตีกองทัพอัมโมนจากที่นั่น 30เยฟธาห์ได้ถวายปฏิญาณต่อองค์พระผู้เป็นเจ้าว่า “หากพระองค์ทรงมอบชาวอัมโมนไว้ในมือของข้าพระองค์แล้ว 31อะไรก็ตามที่ออกจากประตูบ้านของข้าพระองค์มาต้อนรับข้าพระองค์ เมื่อข้าพระองค์กลับไปพร้อมกับชัยชนะเหนือชาวอัมโมน สิ่งนั้นจะเป็นขององค์พระผู้เป็นเจ้าข้าพระองค์จะถวายเป็นเครื่องเผาบูชา”

32จากนั้นเยฟธาห์จึงไปสู้กับชาวอัมโมน และองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงมอบพวกเขาไว้ในมือของเขา 33เขาบุกทำลายล้างยี่สิบเมือง ตั้งแต่อาโรเออร์จนจดเขตเมืองมินนิท ไปจนถึงเอเบลเครามิม เป็นอันว่าชาวอัมโมนพ่ายแพ้อิสราเอล

34เมื่อเยฟธาห์กลับมาบ้านที่มิสปาห์ บุตรสาวของเขาร่ายรำตามเสียงรำมะนาออกมาต้อนรับเขา! นางเป็นลูกคนเดียว นอกจากนางแล้ว เขาไม่มีลูกชายลูกสาวคนอื่นอีก 35เมื่อเห็นนาง เขาก็ฉีกเสื้อผ้าและร้องว่า “โธ่! ลูกสาวของพ่อเอ๋ย! เจ้าทำให้หัวใจของพ่อแตกสลาย เพราะพ่อได้ถวายสัตย์ปฏิญาณไว้กับองค์พระผู้เป็นเจ้าจะคืนคำก็ไม่ได้”

36นางตอบว่า “พ่อทำกับลูกตามที่สัญญาไว้กับองค์พระผู้เป็นเจ้าเถิด ในเมื่อองค์พระผู้เป็นเจ้าประทานชัยชนะเหนืออัมโมนศัตรูของพ่อแล้ว 37แต่ลูกขอร้องอย่างหนึ่งว่า ขอให้ลูกท่องไปตามเนินเขาต่างๆ ร้องไห้อยู่กับเพื่อนๆ สักสองเดือน เพราะลูกจะไม่มีวันได้แต่งงาน”

38เขากล่าวว่า “ไปเถอะลูก” และเขาให้นางไปเป็นเวลาสองเดือน นางก็ไปที่เนินเขากับเพื่อนๆ และร่ำไห้คร่ำครวญเนื่องจากนางจะไม่มีวันได้แต่งงาน 39หลังจากนั้นสองเดือน นางก็กลับมาหาบิดา เยฟธาห์ก็ทำกับนางตามที่ปฏิญาณไว้ทั้งๆ ที่นางยังเป็นหญิงพรหมจารี

นับแต่นั้นมากลายเป็นขนบประเพณีในอิสราเอล 40คือทุกปีหญิงสาวอิสราเอลจะออกไปไว้อาลัยให้บุตรสาวของเยฟธาห์ชาวกิเลอาดเป็นเวลาสี่วัน