መሳፍንት 13 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

መሳፍንት 13:1-25

የሳምሶን መወለድ

1እስራኤላውያን እንደ ገና በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ድርጊት ፈጸሙ፤ ስለዚህም እግዚአብሔር በፍልስጥኤማውያን እጅ አርባ ዓመት እንዲገዙ አሳልፎ ሰጣቸው።

2ማኑሄ የተባለ ከዳን ወገን የተወለደ አንድ የጾርዓ ሰው ነበረ፤ ሚስቱ መካን ስለ ነበረች ልጅ አልወለደችም። 3የእግዚአብሔርም መልአክ ለሴቲቱ ተገልጦ እንዲህ አላት፤ “እነሆ፤ አንቺ መካን ነሽ፤ ልጅም አልወለድሽም፤ ነገር ግን ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ። 4እንግዲህ ተጠንቀቂ፤ የወይን ጠጅም ሆነ ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አትጠጪ፤ ርኩስ ነገርም አትብዪ፤ 5ምክንያቱም ትፀንሻለሽ፤ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ። በራሱ ላይ ምላጭ አይድረስበት፤ ልጁ ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ ናዝራዊ በመሆን ለእግዚአብሔር የተለየ ይሆናልና፤ እስራኤልንም ከፍልስጥኤማውያን እጅ መታደግ ይጀምራል።”

6ከዚያም ሴቲቱ ወደ ባሏ ሄዳ እንዲህ አለችው፤ “የእግዚአብሔር ሰው ወደ እኔ መጣ፤ የእግዚአብሔር መልአክ የሚመስልና እጅግ የሚያስደነግጥ ነበር። ከየት እንደ መጣ አልጠየቅሁትም፤ እርሱም ስሙን አልነገረኝም፤ 7ነገር ግን፣ ‘ትፀንሻለሽ፤ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፤ ስለዚህ ከእንግዲህ ወዲያ የወይን ጠጅም ሆነ ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አትጠጪ፤ ርኩስ ነገር አትብዪ፤ ልጁም ከእናቱ ማሕፀን ጀምሮ እስኪሞት ድረስ ናዝራዊ በመሆን ለእግዚአብሔር የተለየ ይሆናልና’ ብሎኛል።”

8ከዚያም ማኑሄ፣ “ጌታ ሆይ፤ የሚወለደውን ልጅ እንዴት አድርገን ማሳደግ አንዳለብን እንዲያስተምረን ያ ወደ እኛ የላክኸው የእግዚአብሔር ሰው እንደ ገና እንዲመጣ ታደርግ ዘንድ እለምንሃለሁ” ብሎ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።

9እግዚአብሔርም የማኑሄን ጸሎት ሰማ፤ የእግዚአብሔርም መልአክ ሴቲቱ በዕርሻ ውስጥ ሳለች ተገለጠላት፤ በዚህ ጊዜ ግን ባሏ ማኑሄ አብሯት አልነበረም። 10እርሷም ለባሏ ለመንገር ፈጥና በመሄድ፣ “ባለፈው ጊዜ የተገለጠልኝ ሰው ዛሬም ተገለጠልኝ” አለችው። 11ማኑሄም ተነሥቶ ሚስቱን ተከተላት፤ ሰውየው እንደ ደረሰም፣ “ከሚስቴ ጋር ተነጋግረህ የነበርኸው አንተ ነህ?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፤ “አዎን እኔ ነኝ” አለው።

12ማኑሄም፣ “ያልኸው በሚፈጸምበት ጊዜ የልጁ ሕይወት የሚመራው እንዴት ነው? እኛስ ምን ማድረግ አለብን?” ሲል ጠየቀው።

13የእግዚአብሔርም መልአክ እንዲህ አለው፤ “ሚስትህ የነገርኋትን ሁሉ ታድርግ። 14ከወይን ተክል የሚገኝ ማንኛውንም ነገር አትብላ፤ የወይን ጠጅም ሆነ ሌላ የሚያሰክር መጠጥ አትጠጣ፤ ርኩስ ነገር አትብላ፤ ያዘዝኋትንም ሁሉ ታድርግ።”

15ከዚያም ማኑሄ የእግዚአብሔርን መልአክ፣ “የፍየል ጠቦት ዐርደን እስክናዘጋጅልህ ድረስ እባክህ ቈይ” አለው።

16የእግዚአብሔርም መልአክ፣ “የግድ ብታቈየኝ እንኳ የምታቀርበውን ማንኛውንም ምግብ አልበላም፤ ነገር ግን የሚቃጠል መሥዋዕት የምታዘጋጅ ከሆነ እርሱን ለእግዚአብሔር አቅርበው” አለው። የሚያነጋግረው የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን አላወቀም ነበር።

17ማኑሄ የእግዚአብሔርን መልአክ፣ “የተናገርኸው ሲፈጸም እንድናከብርህ ስምህ ማን ነው?” በማለት ጠየቀው።

18እርሱም፣ “ስሜ ድንቅ13፥18 ወይም ድንቁ ስለሆነ፣ ለምን ትጠይቀኛለህ?” አለው። 19ማኑሄም የፍየሉን ጠቦት ከእህል ቍርባኑ ጋር ወስዶ በዐለት ላይ ለእግዚአብሔር ሠዋው። ማኑሄና ሚስቱ እያዩ እግዚአብሔር አስደናቂ ነገር አደረገ፤ 20ይኸውም የእሳቱ ነበልባል ከመሠዊያው ወደ ሰማይ ሲወጣ፣ የእግዚአብሔር መልአክ በነበልባሉ ውስጥ ዐረገ። ማኑሄና ሚስቱ ይህን ሲመለከቱ በግንባራቸው መሬት ላይ ተደፉ። 21የእግዚአብሔርም መልአክ ለማኑሄና ለሚስቱ ዳግመኛ ባለመገለጡ፣ ቀደም ሲል የተገለጠላቸው የእግዚአብሔር መልአክ መሆኑን ማኑሄ ዐወቀ።

22ሚስቱንም፣ “እግዚአብሔርን ስላየን ያለ ጥርጥር እንሞታለን” አላት።

23ሚስቱ ግን መልሳ እንዲህ አለችው፣ “እግዚአብሔር ሊገድለን ቢፈልግ ኖሮ፣ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የእህል ቍርባኑን ከእጃችን ባልተቀበለን፤ ደግሞም ይህን ነገር ሁሉ ባላሳየንና እንዲህ ያለውንም ነገር በዚህ ጊዜ ባልነገረን ነበር።”

24ሴቲቱ ወንድ ልጅ ወለደች፤ ስሙንም ሳምሶን ብላ ጠራችው። ልጁ አደገ፤ እግዚአብሔርም ባረከው፤ 25የእግዚአብሔርም መንፈስ በጾርዓና በኤሽታኦል መካከል ባለው በዳን ሰፈር ሳለ ያነቃቃው ጀመር።

Thai New Contemporary Bible

ผู้วินิจฉัย 13:1-25

กำเนิดแซมสัน

1อิสราเอลหวนกลับไปทำสิ่งที่ชั่วในสายพระเนตรขององค์พระผู้เป็นเจ้าอีก องค์พระผู้เป็นเจ้าจึงทรงมอบเขาไว้ในมือของชาวฟีลิสเตียเป็นเวลาสี่สิบปี

2ชายคนหนึ่งในโศราห์ชื่อมาโนอาห์จากเผ่าดาน ภรรยาของเขาเป็นหมันและจึงไม่สามารถมีลูก 3ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้ามาปรากฏและกล่าวกับนางว่า “เจ้าเป็นหมันแต่เจ้ากำลังจะตั้งครรภ์และคลอดบุตรชาย 4จงอย่าดื่มเหล้าองุ่นหรือของมึนเมา และอย่ากินสิ่งใดที่เป็นมลทิน 5เพราะเจ้าจะตั้งครรภ์และคลอดบุตรชาย อย่าให้บุตรชายของเจ้าตัดผมเลย เพราะเขาจะเป็นนาศีร์แยกไว้เพื่อพระเจ้าตั้งแต่แรกเกิด เขาจะเป็นผู้ริเริ่มกอบกู้อิสราเอลจากเงื้อมมือชาวฟีลิสเตีย”

6หญิงนั้นวิ่งไปบอกสามีว่า “คนของพระเจ้ามาปรากฏแก่ข้าพเจ้า ดูเหมือนเขาจะเป็นทูตของพระเจ้า น่าเกรงขามมาก ข้าพเจ้าไม่ได้ถามว่าเขามาจากไหน และเขาก็ไม่ได้บอกชื่อของเขา 7แต่เขาบอกข้าพเจ้าว่า ‘เจ้าจะตั้งครรภ์และคลอดบุตรชาย ตั้งแต่นี้ไปเจ้าต้องไม่ดื่มเหล้าองุ่นหรือของมึนเมาและไม่กินสิ่งใดที่เป็นมลทิน เพราะว่าเด็กนั้นจะเป็นนาศีร์ของพระเจ้าตั้งแต่เกิดจวบจนวันตาย’ ”

8มาโนอาห์จึงอธิษฐานทูลองค์พระผู้เป็นเจ้าว่า “ข้าแต่องค์พระผู้เป็นเจ้า ขอทรงโปรดอนุญาตให้คนของพระเจ้าที่ทรงส่งมานั้นกลับมาอีกครั้ง เพื่อสอนข้าพระองค์ทั้งสองในการเลี้ยงดูลูกที่จะเกิดมานั้น”

9พระเจ้าทรงฟังคำอธิษฐานของมาโนอาห์ ทูตของพระเจ้ามาปรากฏแก่ภรรยาของเขาอีกครั้งขณะที่นางอยู่กลางทุ่ง แต่มาโนอาห์ไม่ได้อยู่กับนาง 10นางจึงรีบไปบอกสามีว่า “ชายคนเดิมที่ปรากฏแก่ฉันเมื่อวันก่อนมาที่นี่อีกแล้ว!”

11มาโนอาห์จึงลุกตามภรรยาไป เมื่อเขาพบชายคนนั้นแล้วก็ถามว่า “ท่านเป็นคนเดียวกับที่พูดกับภรรยาของข้าพเจ้าเมื่อวันก่อนหรือ?”

ผู้นั้นตอบว่า “ใช่”

12ดังนั้นมาโนอาห์จึงถามว่า “เมื่อคำพูดของท่านเป็นจริงแล้ว มีกฎเกณฑ์อะไรบ้างในชีวิตและในการงานของเด็กนั้น?”

13ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้าตอบว่า “ภรรยาของเจ้าต้องปฏิบัติตามที่เราสั่งไว้ทุกอย่าง 14นางต้องไม่กินสิ่งที่ทำจากองุ่น ต้องไม่ดื่มเหล้าองุ่นหรือของมึนเมา หรือกินสิ่งใดที่เป็นมลทิน นางต้องทำตามที่เราสั่งไว้ทุกประการ”

15มาโนอาห์จึงกล่าวกับทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้าว่า “โปรดพักอยู่ที่นี่ก่อน เราจะไปปรุงลูกแพะมาให้ท่าน”

16ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้าตอบว่า “แม้เจ้าจะหน่วงเหนี่ยวเราไว้ เราก็จะไม่กินอาหารใดๆ ของเจ้า แต่หากเจ้าจัดเตรียมเครื่องเผาบูชา จงถวายแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าเถิด” (มาโนอาห์ยังไม่ตระหนักว่าผู้นั้นคือทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้า)

17มาโนอาห์จึงเอ่ยถามทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้าว่า “โปรดบอกชื่อของท่านให้ข้าพเจ้าทราบ เพื่อข้าพเจ้าจะให้เกียรติท่าน เมื่อเหตุการณ์เป็นจริงตามที่ท่านพูด?”

18ทูตองค์นั้นตอบว่า “เหตุใดจึงถามชื่อของเรา? ชื่อนั้นเกินความเข้าใจ13:18 หรือมหัศจรรย์19แล้วมาโนอาห์จึงนำลูกแพะและเครื่องธัญบูชามาถวายบนศิลาแด่องค์พระผู้เป็นเจ้าและพระองค์ทรงทำสิ่งอัศจรรย์ต่อหน้ามาโนอาห์กับภรรยา 20ขณะที่เปลวไฟพวยพุ่งจากแท่นบูชาลอยขึ้นสู่ท้องฟ้า ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้าลอยขึ้นเหนือเปลวไฟ เมื่อเห็นดังนั้นมาโนอาห์กับภรรยาจึงซบหน้าลงกับพื้นดิน 21ทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้าไม่ได้ปรากฏแก่มาโนอาห์กับภรรยาอีก มาโนอาห์จึงตระหนักว่าผู้นี้คือทูตขององค์พระผู้เป็นเจ้า

22มาโนอาห์กล่าวกับภรรยาว่า “เราต้องตายแน่ๆ! เพราะเราได้เห็นพระเจ้า!”

23แต่ภรรยาตอบว่า “หากองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงดำริจะประหารเรา พระองค์ก็คงจะไม่รับเครื่องเผาบูชาและธัญบูชาจากมือของเรา และจะไม่มาแจ้งหรือแสดงสิ่งทั้งปวงนี้แก่เรา”

24นางได้คลอดบุตรชายและตั้งชื่อว่าแซมสัน เด็กนั้นเติบโตขึ้น และองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงอวยพรเขา 25พระวิญญาณขององค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเริ่มกระตุ้นเขาที่มาหะเนห์ดาน ซึ่งตั้งอยู่ระหว่างโศราห์กับเอชทาโอล