以賽亞書 2 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 2:1-22

主必統治萬邦

1亞摩斯的兒子以賽亞看到以下有關猶大耶路撒冷的異象。

2在末後的日子,耶和華殿所在的山必聳立,

高過群山,超過萬嶺,

萬族都要湧向它。

3眾民都必來,說:

「來吧!讓我們登耶和華的山,

雅各之上帝的殿。

祂必將祂的路指示給我們,

使我們走祂的道。」

因為訓誨必出於錫安

耶和華的話語必來自耶路撒冷

4祂必在各國施行審判,

為列邦平息紛爭。

他們必將刀劍打成犁頭,

把矛槍製成鐮刀。

國與國不再刀兵相見,

人們不用再學習戰事。

5雅各家啊,來吧!

讓我們走在耶和華的光中。

耶和華審判的日子

6耶和華啊,你離棄了你的子民——雅各的後裔,

因為他們當中充滿了東方的惡俗,

非利士人一樣占卜,

跟外族人同流合污。

7他們境內金銀遍地,

財寶無窮;

他們境內馬匹充裕,

戰車無數。

8他們境內偶像林立,

他們跪拜自己用手所造的物品,

跪拜自己用指頭所造之物。

9他們必遭羞辱和貶抑。

耶和華啊,

求你不要赦免他們。

10要躲進岩穴,藏入地洞,

逃避耶和華的憤怒和威榮!

11到那日,狂妄的人將被挫敗,

驕傲的人將遭貶抑;

唯獨耶和華將受尊崇。

12因為萬軍之耶和華已定了日子,

要懲罰一切驕傲狂妄和自高自大的人,

使他們淪為卑賤;

13祂必毀滅黎巴嫩高大的香柏樹和巴珊的橡樹,

14毀滅一切崇山峻嶺,

15毀滅高聳的城樓和堅固的城牆,

16毀滅他施的商船和一切華美的船隻。

17到那日,狂妄的人必被挫敗,

驕傲的人必遭貶抑,

唯獨耶和華受尊崇。

18偶像必被徹底剷除。

19耶和華使大地震動的時候,

眾人躲進岩穴,藏入地洞,

逃避祂的憤怒和威榮。

20到那日,眾人必把造來敬拜的金銀偶像丟給田鼠和蝙蝠。

21耶和華使大地震動的時候,

眾人必躲進山洞和岩縫,

逃避祂的憤怒和威榮。

22不要再倚靠世人,

他們的生命不過是一口氣,

他們有什麼值得稱道的呢?

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 2:1-22

የእግዚአብሔር ተራራ

1የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ስለ ይሁዳና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ይህ ነው፤

2በዘመኑም ፍጻሜ፣

የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተራራ

ከተራሮች ከፍ ብሎ ይመሠረታል፤

ከኰረብቶችም በላይ ከፍ ከፍ ይላል፤

ሕዝቦችም ሁሉ ወደዚያ ይጐርፋሉ።

3ብዙ ሕዝቦችም መጥተው እንዲህ ይላሉ፤

“ኑ፤ ወደ እግዚአብሔር ተራራ፣

ወደ ያዕቆብ አምላክ ቤት እንውጣ፤

እርሱ መንገዱን ያስተምረናል፤

በጐዳናውም እንሄዳለን።”

ሕግ ከጽዮን፣

የእግዚአብሔር ቃል ከኢየሩሳሌም ይወጣልና።

4እርሱ በሕዝቦች መካከል ይፈርዳል፤

የብዙ ሰዎችን አለመግባባት ያስወግዳል።

እነርሱም ሰይፋቸውን ቀጥቅጠው ማረሻ፣

ጦራቸውንም ማጭድ ያደርጋሉ።

ሕዝብ በሕዝብ ላይ ሰይፍ አያነሣም፤

ጦርነትንም ከእንግዲህ አይማሩም።

5እናንተ የያዕቆብ ቤት ሆይ፤ ኑ፤

በእግዚአብሔር ብርሃን እንመላለስ።

የእግዚአብሔር ቀን

6የያዕቆብ ቤት የሆነውን

ሕዝብህን ትተሃል፤

እነርሱ በምሥራቅ ሰዎች ከንቱ አምልኮ ተሞልተዋልና፤

እንደ ፍልስጥኤማውያን ያሟርታሉ፤

ከባዕዳን ጋር አገና ይማታሉ።

7ምድራቸው በብርና በወርቅ ተሞልታለች፤

ሀብታቸውም ልክ የለውም።

ምድራቸው በፈረሶች ተሞልታለች፤

የሠረገሎቻቸውም ብዛት ልክ የለውም።

8ምድራቸው በጣዖታት ተሞልታለች፤

ጣቶቻቸው ላበጇቸው፣

ለእጆቻቸው ሥራ ይሰግዳሉ።

9ሰው ዝቅ ብሏል፤

የሰው ልጅም ተዋርዷል፤

ስለዚህ በደላቸውን ይቅር አትበል2፥9 ወይም፣ ከፍ አታድርጋቸው ማለት ነው።

10ከእግዚአብሔር አስፈሪነትና ከግርማው ሽሽ፤

ወደ ዐለቶች ሂድ፤

በመሬትም ውስጥ ተሸሸግ።

11የእብሪተኛ ሰው ዐይን ይሰበራል፤

የሰዎችም ትዕቢት ይዋረዳል፤

በዚያን ቀን እግዚአብሔር ብቻውን ከፍ ከፍ ይላል።

12የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

እብሪተኛውንና ትዕቢተኛውን ሁሉ፣

የተኵራራውን በሙሉ

የሚያዋርድበት ቀን አለው።

13ረዥምና ከፍ ከፍ ያሉትን የሊባኖስ ዝግባዎች ሁሉ፣

የባሳንን የወርካ ዛፎች ሁሉ፣

14ታላላቁን ተራራ ሁሉ፣

ከፍ ያለውን ኰረብታ ሁሉ፣

15ረዣዥሙን ግንብ ሁሉ፣

የተመሸገውን ቅጥር ሁሉ፣

16የተርሴስን መርከቦች2፥16 ወይም የንግድ መርከቦች ማለት ነው። ሁሉ፣

የክብር ጀልባዎችን ሁሉ የሚያዋርድበት ቀን አለው።

17የሰው እብሪት ይዋረዳል፤

የሰውም ኵራት ይወድቃል፤

በዚያን ቀን እግዚአብሔር ብቻ ከፍ ከፍ ይላል፤

18ጣዖቶች ሁሉ ፈጽሞ ይወድማሉ።

19እግዚአብሔር ምድርን ለማናወጥ በሚነሣበት ጊዜ፣

ሰዎች ከአስፈሪነቱ

ከግርማውም የተነሣ፣

ወደ ዐለት ዋሻ፣

ወደ መሬትም ጕድጓድ ለመሸሸግ ይሮጣሉ።

20በዚያን ቀን ሰዎች

ሊያመልኳቸው ያበጇቸውን፣

የብርና የወርቅ ጣዖቶቻቸውን

ለፍልፈልና ለሌሊት ወፍ ይወረውራሉ።

21እግዚአብሔር ምድርን ለማናወጥ በሚነሣበት ጊዜ፣

ሰዎች ከአስፈሪነቱ

እንዲሁም ከግርማው የተነሣ፣

ወደ ድንጋይ ዋሻ፣

ወደ ዐለት ስንጣቂ ሮጠው ይገባሉ።

22እስትንፋስ አፍንጫው ላይ ባለች

በሰው አትታመኑ፤

ከቶ ምን የሚበጅ ነገር አለው!