以賽亞書 3 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 3:1-26

對耶路撒冷和猶大的審判

1主——萬軍之耶和華要從耶路撒冷猶大拿去眾人倚靠的一切:糧食、水、

2英雄、戰士、審判官、先知、

占卜者、長老、

3五十夫長、顯貴、謀士、巧匠和巫師。

4主必使少兒做他們的首領,

讓孩童治理他們。

5百姓將彼此欺凌,

鄰居互相爭鬥,

少年目無尊長,

卑賤者欺尊犯上。

6那時,人會拉住一位同族的弟兄說:

「你至少還有件像樣的衣服,

你就做我們的首領吧,

這廢墟之地就交給你了!」

7但那人必高聲說:

「我救不了你們。

我家中無衣無食,

不要讓我做首領。」

8耶路撒冷必崩潰,

猶大必敗落,

因為他們的言行冒犯耶和華,

蔑視榮耀的主。

9他們的表情顯出他們心術不正,

他們跟所多瑪人一樣對自己的罪惡津津樂道,

毫不隱瞞。

他們必大禍臨頭,自招毀滅。

10要告訴義人:他們有福了,

必得善報。

11惡人有禍了!他們必大禍臨頭,

受到報應。

12耶和華說:「我的子民啊!

孩童欺壓你們,

婦女管轄你們。

你們的首領領你們入迷途,

帶你們走歧路。」

13耶和華準備就緒,

要審判祂的子民。

14祂必審問祂子民中的長老和首領,對他們說:

「你們毀壞了我的葡萄園——我的子民,

家裡堆滿了從窮人那裡掠奪的東西。

15你們為何壓榨我的子民,

虐待貧窮人?」

這是主——萬軍之耶和華說的。

16耶和華又說:

錫安的女子狂傲,

昂首走路,賣弄媚眼,

俏步徐行,腳鐲叮噹。

17所以,我要使她們頭上長瘡,

露出頭皮。」

18到那日,主必拿去她們美麗的腳鐲、髮飾、項鏈、 19耳環、手鐲、面紗、 20頭飾、腳鏈、彩帶、香盒、護身符、 21戒指、鼻環、 22禮服、外袍、披肩、錢包、 23鏡子、內衣、頭巾和圍巾。

24她們的香氣將變成臭味,

腰帶將變成繩子,

美髮將變成禿頭,

華服將變成麻衣,

美麗的容顏將佈滿羞辱的烙印。

25城中的男子將喪身刀下,

勇士將戰死沙場。

26錫安的城門必悲傷、哀哭,

錫安必空空地坐在地上。

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 3:1-26

በኢየሩሳሌምና በይሁዳ ላይ የሚመጣ ፍርድ

1እነሆ፤ ጌታ፣

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

ከኢየሩሳሌምና ከይሁዳ

ድጋፉንና ርዳታውን፣

የምግብና የውሃ ርዳታውን ሁሉ ይነሣል፤

2ጀግናውንና ተዋጊውን፣

ፈራጁንና ነቢዩን፣

አስማተኛውንና ሽማግሌውን፣

3የአምሳ አለቃውንና ባለ ማዕረጉን፣

አማካሪውንና ጠቢቡን የእጅ ባለሙያ፣

ብልኁንም ምትሀተኛ ይነሣል።

4ልጆችን መሪዎቻቸው አደርጋለሁ፤

ያልበሰሉ ሕፃናትም ይገዟቸዋል።

5ሕዝብ እርስ በርሱ ይጨቋቈናል፤

ሰው በሰው ላይ፤ ባልንጀራ በባልንጀራው ላይ፣

ወጣቱ በሽማግሌው ላይ፣

ተራው ሰው በተከበረው ላይ ይነሣል።

6ሰውም በአባቱ ቤት

ከወንድሞቹ አንዱን ይዞ፣

“አንተ ልብስ ስላለህ መሪ ሁነን፤

ይህንም የፍርስራሽ ክምር ግዛ!” ይለዋል።

7እርሱ ግን በዚያ ቀን ድምፁን ከፍ አድርጎ፣

“እኔ መፍትሔ አልሆንም፤

በቤቴም ልብስና ምግብ የለኝም፤

የሕዝብ መሪ አታድርጉኝ” ይላል።

8ኢየሩሳሌም ተንገዳግዳለች፤

ይሁዳም ለመውደቅ ተቃርባለች፤

ንግግራቸውም ሆነ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚቃወም፣

የክብሩንም መገኘት የሚያቃልል ነውና።

9የፊታቸው ገጽታ ይመሰክርባቸዋል፤

ኀጢአታቸውን እንደ ሰዶም በይፋ ይናገራሉ፤

አይደብቁትምም፤

ጥፋትን በራሳቸው ላይ ስላመጡ፣

ወዮላቸው!

10ጻድቃን መልካም ነገር እንደሚያገኙ ንገሯቸው፤

የሥራቸውን ፍሬ ይበላሉና።

11በደለኞች ወዮላቸው፤ ጥፋት ይመጣባቸዋል፤

የእጃቸውን ያገኛሉና።

12ወጣቶች ሕዝቤን ያስጨንቃሉ፤

ሴቶችም ይገዟቸዋል።

ሕዝቤ ሆይ፤ መሪዎችህ አሳስተውሃል፤

ከመንገድህም መልሰውሃል።

13እግዚአብሔር በፍርድ ወንበር ላይ ተቀምጧል፤

በሕዝቡም ላይ ለመፍረድ ተነሥቷል።

14እግዚአብሔር

ከአለቆችና ከሕዝቡ ሽማግሌዎች ጋር እንዲህ ሲል ይፋረዳል፤

“የወይኔን ቦታ ያጠፋችሁ እናንተ ናችሁ፤

ከድኾች የዘረፋችሁትም በቤታችሁ ይገኛል፤

15ሕዝቤን በችግር ስታደቅቁት፣

የድኾችንም ፊት በሐዘን ስታገረጡት ምን ማለታችሁ ነው?”

ይላል ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

16እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤

የጽዮን ሴቶች ኰርተዋል፤

ዐንገታቸውን እያሰገጉ፣

በዐይናቸውም እየጠቀሱ ይሄዳሉ፤

እየተቈነኑ በመራመድ፣

የእግራቸውን ዐልቦ ያቃጭላሉ።

17ስለዚህ፣ ጌታ በጽዮን ሴቶች ዐናት ላይ

ቈረቈር ያመጣል፤

እግዚአብሔርም ራሳቸውን ቡሀ ያደርጋል።

18በዚያም ቀን ጌታ የክብር ጌጣቸውን ይነጥቃቸዋል፤ የእግር አንባሩን፣ የጠጕር ጌጡን፣ የጨረቃ ቅርጽ ያለውን የዐንገት ጌጥ፣ 19የጆሮ ጕትቻውን፣ የእጅ አንባሩን፣ የፊት መሸፈኛውን፣ 20የራስ መሸፈኛውን፣ ዐልቦውን፣ ሻሹን፣ የሽቶ ብልቃጡን፣ አሸንክታቡን፣ 21የጣት ቀለበቶችንና የአፍንጫ ቀለበቶችን፣ 22ያማረውን ቀሚስ፣ የውስጥ ልብሱን፣ ካባውን፣ የእጅ ቦርሳውን፣ 23መስተዋቱን፣ ከጥሩ በፍታ የተሠራውን ልብስ፣ የራስ ጌጡን፣ ዐይነ ርግቡን ሁሉ ይነጥቃቸዋል።

24በሽቶ ፈንታ ግማት፣

በሻሽ ፈንታ ገመድ፣

አምሮ በተሠራ ጠጕር ፈንታ ቡሀነት፣

ባማረ ልብስ ፈንታ ማቅ፣

በውበትም ፈንታ ጠባሳ ይሆናል።

25ወንዶቻችሁ በሰይፍ ስለት፣

ተዋጊዎቻችሁ በጦርነት ይወድቃሉ።

26የጽዮን ደጆች ያዝናሉ፣ ያለቅሳሉም፤

እርሷም ተረስታ በመሬት ላይ ትቀመጣለች።