以賽亞書 1 – CCBT & NASV

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以賽亞書 1:1-31

1猶大烏西雅約坦亞哈斯希西迦執政期間,亞摩斯的兒子以賽亞看到了以下有關猶大耶路撒冷的異象。

上帝責備叛逆的子民

2諸天啊,請聽!

大地啊,要側耳聽!

耶和華說:

「我把孩子撫育成人,

他們竟然背叛我。

3牛認識主人,

驢也認得主人的槽,

以色列卻不認識,

我的子民卻不明白。」

4唉!你們這罪惡的民族,

惡貫滿盈的百姓,

作惡的子孫,

敗壞的兒女!

你們背棄耶和華,

藐視以色列的聖者,

與祂疏遠。

5你們為什麼一再叛逆?

你們還要受責打嗎?

你們已經頭破血流,

身心疲憊。

6你們已經體無完膚,

從頭到腳傷痕纍纍,

傷口沒有清洗,

沒有包紮,也沒有敷藥。

7你們的土地荒涼,

城邑化為灰燼。

你們親眼目睹自己的田園被外族人侵吞、毀壞、變成不毛之地。

8僅存的錫安1·8 錫安」又稱「耶路撒冷」。城也像葡萄園裡的草棚、

瓜田中的茅舍、

被困無援的孤城。

9若不是萬軍之耶和華讓我們一些人存活,

我們早就像所多瑪蛾摩拉一樣滅亡了。

10你們這些「所多瑪」的首領啊,

要聆聽耶和華的話!

你們這些「蛾摩拉」的百姓啊,

要側耳聽我們上帝的訓誨!

11耶和華說:

「你們獻上許多祭物,對我有什麼用呢?

我厭煩公綿羊的燔祭和肥畜的脂肪,

我不喜歡公牛、羊羔和公山羊的血。

12「你們來敬拜我的時候,

誰要求你們帶著這些來踐踏我的院宇呢?

13不要再帶毫無意義的祭物了。

我憎惡你們燒的香,

厭惡你們的朔日1·13 朔日」即每月初一。、安息日和大會。

你們又作惡又舉行莊嚴的聚會,

令我無法容忍。

14我憎惡你們的朔日及其他節期,

它們成了我的重擔,

令我厭倦。

15你們舉手禱告,我必掩面不理。

即使你們禱告再多,

我也不會聽,

因為你們雙手沾滿鮮血。

16你們要洗淨自己,

停止作惡,

不要讓我再看見你們的惡行。

17你們要學習行善,

追求正義,

幫助受欺壓的,

替孤兒辯護,

為寡婦伸冤。」

18耶和華說:

「來吧,我們彼此理論!

你們的罪雖如猩紅,

也必潔白如雪;

你們的罪雖如緋紅,

也必白如羊毛。

19如果你們願意聽從,

就必享用這地方的美好出產。

20如果你們執意叛逆,

就必喪身刀下。」

這是耶和華親口說的。

21耶路撒冷啊,

你這忠貞的妻子竟變成了妓女!

你從前充滿公平,

是公義之家,

現在卻住著兇手。

22你曾經像銀子,現在卻像渣滓;

曾經像美酒,現在卻像攙了水的酒。

23你的首領是叛逆之徒,

與盜賊為伍,

個個收受賄賂,

貪圖好處,

不為孤兒辯護,

不替寡婦伸冤。

24所以,主——萬軍之耶和華,

以色列的大能者說:

「我要向我的敵人報仇雪恨。

25我必攻擊你,

用鹼煉淨你的渣滓,

除盡你的雜質。

26我必像從前一樣賜你審判官和謀士。

之後,你必被稱為公義之城、

忠信之邑。」

27耶和華必因祂的公正救贖錫安

必因祂的公義拯救城中悔改的人。

28但叛逆之輩和犯罪之徒必遭毀滅,

背棄耶和華的人必滅亡。

29你們必因在橡樹下,

在你們選擇的園子裡祭拜偶像而蒙羞。

30你們必像枯萎的橡樹,

又如無水的園子。

31你們中間有權勢的人必因他們的惡行而遭毀滅,

好像火花點燃枯木,無人能救。

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 1:1-31

1በይሁዳ ነገሥታት በዖዝያን፣ በኢዮአታም፣ በአካዝና በሕዝቅያስ ዘመን፣ የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ስለ ይሁዳና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ፤

እንቢተኛ ሕዝብ

2ሰማያት ሆይ፤ ስሙ! ምድር ሆይ፤ አድምጪ!

እግዚአብሔር እንዲህ ሲል ተናግሯልና፤

“ልጆች ወለድሁ፣ አሳደግኋቸውም፤

እነርሱ ግን ዐመፁብኝ።

3በሬ ጌታውን፣

አህያ የባለቤቱን ጋጥ ያውቃል፤

እስራኤል ግን አላወቀም፤

ሕዝቤም አላስተዋለም።”

4እናንተ ኀጢአተኛ ሕዝብ፣

በደል የሞላበት ወገን፣

የክፉ አድራጊ ዘር፣

ምግባረ ብልሹ ልጆች ወዮላችሁ!

እግዚአብሔርን ትተዋል፤

የእስራኤልን ቅዱስ አቃልለዋል፤

ጀርባቸውንም በእርሱ ላይ አዙረዋል።

5ለምን ዳግመኛ ትመታላችሁ?

ለምንስ በዐመፅ ትጸናላችሁ?

ራሳችሁ በሙሉ ታምሟል፤

ልባችሁ ሁሉ ታውኳል።

6ከእግር ጥፍራችሁ እስከ ራስ ጠጕራችሁ

ጤና የላችሁም፤

ቍስልና ዕባጭ እንዲሁም እዥ ብቻ ነው፤

አልታጠበም፤ አልታሰረም፤

በዘይትም አልለዘበም።

7አገራችሁ ባድማ፣

ከተሞቻችሁ በእሳት የተቃጠሉ ይሆናሉ፤

ዐይናችሁ እያየ፣

መሬታችሁ በባዕድ ይነጠቃል፤

ጠፍም ይሆናል።

8የጽዮን ሴት ልጅ

በወይን አትክልት ውስጥ እንዳለ ዳስ፣

በዱባ ተክል ወስጥ እንደሚገኝ ጐጆ፣

እንደ ተከበበም ከተማ ተተወች።

9የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ፣

እንደ ሰዶም በሆን፣

ገሞራንም በመሰልን ነበር።

10እናንተ የሰዶም ገዦች፤

የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ፤

እናንተ የገሞራ ሰዎች፤

የእግዚአብሔርን ሕግ አድምጡ።

11“የመሥዋዕታችሁ ብዛት

ለእኔ ምኔ ነው?” ይላል እግዚአብሔር

“የሚቃጠለውን የአውራ በግና

የሠቡ እንስሳትን ሥብ ጠግቤአለሁ፤

በበሬ፣ በበግ ጠቦትና በፍየል ደም ደስ

አልሰኝም።

12በፊቴ ለመቅረብ ስትመጡ፣

ይህን ሁሉ እንድታመጡ፣

የመቅደሴን ደጅ እንድትረግጡ ማን ጠየቃችሁ?

13ከንቱውን መባ አታቅርቡ፤

ዕጣናችሁን እጸየፋለሁ፤

የወር መባቻ በዓላችሁን፣

ሰንበቶቻችሁን፣ ጉባኤያችሁንና

በክፋት የተሞላውን ስብሰባችሁን መታገሥ

አልቻልሁም።

14የወር መባቻችሁንና የተደነገጉ በዓሎቻችሁን

ነፍሴ ጠልታለች፤

ሸክም ሆነውብኛል፤

መታገሥም አልቻልሁም።

15እጆቻቸሁን ለጸሎት ወደ እኔ ስትዘረጉ፣

ዐይኖቼን ከእናንተ እሰውራለሁ፤

አብዝታችሁ ብትጸልዩም እንኳ አልሰማችሁም፤

እጆቻችሁ በደም ተበክለዋል፤

16ታጠቡ፤ ራሳችሁንም አንጹ፤

ክፉ ሥራችሁን ከፊቴ አርቁ፤

ክፉ ማድረጋችሁን ተዉ፤

17መልካም ማድረግን ተማሩ፤

ፍትሕን እሹ፣

የተገፉትን አጽናኑ1፥17 ወይም፣ ጨቋኙን ገሥጹ ማለት ነው።

አባት ለሌላቸው ቁሙላቸው፤

ለመበለቶችም ተሟገቱ።

18“ኑና እንዋቀሥ”

ይላል እግዚአብሔር

“ኀጢአታችሁ እንደ ዐለላ ቢቀላ፣

እንደ በረዶ ይነጣል፤

እንደ ደም ቢቀላም፣

እንደ ባዘቶ ነጭ ይሆናል።

19እሺ ብትሉ፣ ብትታዘዙም

የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤

20እንቢ ብላችሁ ብታምፁ ግን

ሰይፍ ይበላችኋል።”

የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናግሯልና።

21ታማኝ የነበረችው ከተማ

እንዴት አመንዝራ እንደ ሆነች ተመልከቱ፤

ቀድሞ ፍትሕ የሞላባት፣

ጽድቅ የሰፈነባት ነበረች፤

አሁን ግን የነፍሰ ገዳዮች ማደሪያ ሆነች

22ብርሽ ዝጓል፣

ምርጥ የወይን ጠጅሽ ውሃ ገባው፤

23ገዥዎችሽ ዐመፀኞችና

የሌባ ግብረ ዐበሮች ናቸው፤

ሁሉም ጕቦን ይወድዳሉ፤

እጅ መንሻንም በብርቱ ይፈልጋሉ፤

አባት ለሌላቸው አይቆሙም፤

የመበለቶችንም አቤቱታ አይሰሙም።

24ስለዚህ ጌታ፣ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

የእስራኤል ኀያል እንዲህ ይላል፤

“በባላንጣዎቼ ላይ ቍጣዬን እገልጣለሁ፤

ጠላቶቼንም እበቀላለሁ።

25እጄን በአንቺ ላይ አነሣለሁ፤

ዝገትሽን ፈጽሜ አጠራለሁ፤

ጕድፍሽንም ሁሉ አስወግዳለሁ።

26ፈራጆችሽን እንደ ጥንቱ፣

አማካሪዎችሽንም እንደ ቀድሞው እመልሳለሁ፤

ከዚያም የጽድቅ መዲና፣

የታመነች ከተማ

ተብለሽ ትጠሪያለሽ።”

27ጽዮን በፍትሕ፣

በንስሓ የሚመለሱ ነዋሪዎቿም በጽድቅ ይዋጃሉ።

28ዐመፀኞችና ኀጢአተኞች ግን በአንድነት ይደቅቃሉ፤

እግዚአብሔርንም የሚተዉ ይጠፋሉ።

29“ደስ በተሰኛችሁባቸው የአድባር ዛፎች

ታፍራላችሁ፤

በመረጣችኋቸውም የአትክልት ቦታዎች

ትዋረዳላችሁ።

30ቅጠሉ እንደ ጠወለገ ወርካ፣

ውሃም እንደሌለው የአትክልት ቦታ ትሆናላችሁ።

31ብርቱ ሰው እንደ ገለባ፣

ሥራውም እንደ ብልጭታ ይሆናል፤

ሁለቱም አብረው ይቃጠላሉ፤

እሳቱንም የሚያጠፋው የለም።”