但以理书 5 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

但以理书 5:1-31

墙上写字

1伯沙撒王盛宴款待一千大臣,与他们一同饮酒。 2王畅饮的时候,命人将先王尼布甲尼撒耶路撒冷圣殿中掳来的金银器皿拿来,供他与大臣、王后和妃嫔用来饮酒。 3于是,他们把从耶路撒冷上帝殿中掳来的金器拿来,王与大臣、王后和妃嫔便用这些器皿饮酒。 4他们一边饮酒,一边颂赞金、银、铜、铁、木、石所造的神明。

5突然,有人手的指头出现,在灯台对面王宫的粉墙上写字。王看见那只手在写字, 6脸色骤变,惊恐万分,两腿发软,双膝颤抖。 7他大声传令,召来巫师、占星家和占卜者,对这些巴比伦的智者说:“谁能读墙上的字,把意思告诉我,他必身穿紫袍,颈戴金链,在国中位居第三。” 8王所有的智者进来后,竟无人能读懂或把意思告诉王。 9伯沙撒王愈发恐惧,脸色苍白,他的大臣都不知所措。

10太后听到王和大臣的喊声,便来到宴会厅,对王说:“愿王万岁!不要惊慌失色。 11你国中有一个人,他有圣洁神明的灵。先王在世时,曾发现他有神明一样的灼见、悟性和智慧。先王尼布甲尼撒立他为术士、巫师、占星家和占卜者的首领。 12他有非凡的心智、知识和悟性,能解梦、释谜、解惑。他叫但以理,先王给他取名叫伯提沙撒。现在可以把他召来,他必能解释这些字的意思。”

13于是,但以理被带到王面前。王问他:“你就是先王从犹大掳来的但以理吗? 14我听说你有神明的灵,有灼见、悟性和非凡的智慧。 15我召智者和巫师来读这些字,为我解释字的意思,但他们都不能解释。 16我听说你能释梦、解惑。你若能读出墙上的字,把意思告诉我,你必身穿紫袍、颈戴金链,在我的国中位居第三。”

17但以理回答说:“你的礼物自己留着,你的赏赐可以给别人,不过我会为你读这些字,解释意思。 18王啊,至高的上帝曾将国位、权力、尊荣、威严赐给你的先王尼布甲尼撒19因为他有上帝所赐的大权,各族、各邦、各语种的人都在他面前战抖,充满恐惧。他操生杀大权,可随意擢升、罢黜。 20但他变得心高气傲、刚愎自用、狂妄自大,因而被革除王位、剥去尊荣。 21他从人群中被赶走,他的心变成兽心,他与野驴同住,像牛一样吃草,被天上的露水浸湿,直到他知道至高的上帝主宰世上万国,祂要把国赐给谁就赐给谁。

22伯沙撒啊,你是他的后裔,你虽然知道这一切事,仍不谦卑, 23竟在天上的主面前自大,命人拿来祂殿里的器皿,供你和大臣、王后、妃嫔用来饮酒,并颂赞不能看、不能听、一无所知、用金、银、铜、铁、木、石所造的神明,却不尊崇赐你生命气息、掌管你一举一动的上帝。

24“因此,上帝使指头出现,写下这些字, 25就是‘弥尼,弥尼,提客勒,乌法珥新’。 26这些字的意思是这样,弥尼——指上帝已经数算你国度的年日,使之到此为止; 27提客勒——指你已经被放在秤上称了,发现分量不够; 28乌法珥新5:28 乌法珥新”亚兰文是“毗勒斯”,即“乌法珥新”的单数格式。——指你的国要分裂,归给玛代人和波斯人。”

29于是,伯沙撒下令给但以理穿上紫袍,戴上金项链,又宣告他在国中位居第三。 30当夜,迦勒底伯沙撒被杀。 31玛代大流士六十二岁时夺取了王权。

New Amharic Standard Version

ዳንኤል 5:1-31

በግድግዳው ላይ የታየው ጽሕፈት

1ንጉሥ ቤልሻዛር ለሺሕ መኳንንቱ ታላቅ ግብዣ አደረገ፤ በሺሑም ፊት የወይን ጠጅ ይጠጣ ነበር። 2ቤልሻዛር የወይን ጠጁን እየጠጣ ሳለ፣ አባቱ5፥2 ወይም አያት፤ ወይም ቀዳሚ ዘር እንዲሁም 11፡13 እና 18 ናቡከደነፆር ከኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ያመጣቸውን የወርቅና የብር መጠጫዎችን እርሱና መኳንንቱ፣ ሚስቶቹና ቍባቶቹ ይጠጡባቸው ዘንድ እንዲያመጡለት አዘዘ። 3ከዚያም በኢየሩሳሌም ከነበረው ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የተወሰዱትን የወርቅ መጠጫዎች አመጡ፤ ንጉሡና መኳንንቱ፣ ሚስቶቹና ቍባቶቹም ጠጡባቸው። 4የወይን ጠጁንም እየጠጡ የወርቅና የብር፣ የናስ፣ የብረት፣ የዕንጨትና የድንጋይ አማልክትን አመሰገኑ።

5በድንገትም የሰው እጅ ጣቶች ታዩ፤ በቤተ መንግሥቱ ውስጥ በመቅረዙ ትይዩ ባለው ግድግዳ ልስን ላይ ጻፉ፤ ንጉሡም ይጽፍ የነበረውን እጅ አየ፤ 6በዚያን ጊዜ ንጉሡ በድንጋጤ ተሞላ፤ ፊቱም ተለዋወጠ፤ እጆቹና እግሮቹ ከዱት፤ ጕልበቶቹም ተብረከረኩ።

7ንጉሡም ድምፁን ከፍ አድርጎ አስማተኞችን፣ ኮከብ ቈጣሪዎችንና5፥7 ወይም ከለዳውያን፤ እንዲሁም 11 መተተኞችን እንዲያስገቡለት አዘዘ፤ ለባቢሎናውያኑ ጠቢባን እንዲህ አላቸው፤ “ይህን ጽሕፈት አንብቦ ትርጕሙን የሚነግረኝን ሐምራዊ መጐናጸፊያ አለብሰዋለሁ፤ የወርቅ ሐብልም በዐንገቱ ላይ አጠልቅለታለሁ፤ በመንግሥቴም ላይ ሦስተኛ ገዥ ይሆናል።”

8ከዚያም የንጉሡ ጠቢባን ሁሉ ገቡ፤ ነገር ግን ጽሕፈቱን ሊያነብም ሆነ ትርጕሙ ምን እንደ ሆነ ለንጉሡ ሊነግር የሚችል ማንም አልነበረም። 9ንጉሥ ቤልሻዛር ከፊት ይልቅ ፈራ፤ ፊቱም እጅግ ተለወጠ፤ መኳንንቱም ግራ ገብቷቸው ተደናገጡ።

10ንግሥቲቱም5፥10 ወይም የንጉሡ እናት የንጉሡንና የመኳንንቱን ድምፅ ሰምታ ወደ ግብዣው አዳራሽ ገባች፤ እንዲህም አለች፤ “ንጉሥ ሆይ፤ ለዘላለም ንገሥ፤ አትደንግጥ፤ ፊትህም አይለዋወጥ! 11በመንግሥትህ ውስጥ የቅዱሳን አማልክት መንፈስ ያለበት አንድ ሰው አለ፤ ይህ ሰው በአባትህ ዘመን እንደ አማልክት ጥበብና ማስተዋል፣ ዕውቀትም የሞላበት ሆኖ ተገኝቷል፤ አባትህ ንጉሥ ናቡከደነፆርም የጠንቋዮች፣ የአስማተኞች፣ የኮከብ ቈጣሪዎችና የመተተኞች አለቃ አደረገው። 12ንጉሡ ብልጣሶር ብሎ የጠራው ይህ ዳንኤል መልካም መንፈስ፣ ዕውቀትና ማስተዋል ያለው ሆኖ ተገኘ፤ ሕልምን የመተርጐም፣ ዕንቈቅልሽን የመፍታትና የተሰወረውን የመግለጥ ልዩ ችሎታም ነበረው። ስለዚህ ዳንኤልን አስጠራ፤ እርሱም የጽሕፈቱን ትርጕም ይነግርሃል።”

13ዳንኤልንም ወደ ንጉሡ አቀረቡት፤ ንጉሡም እንዲህ አለው፤ “ንጉሡ አባቴ ከይሁዳ ማርኮ ካመጣቸው መካከል አንዱ የሆንኸው ዳንኤል አንተ ነህን? 14የአማልክት መንፈስ በውስጥህ እንዳለ፣ ዕውቀት፣ ማስተዋልና ልዩ ጥበብ እንዳለህ ሰምቻለሁ። 15ይህን ጽሕፈት አንብበው ትርጕሙ ምን እንደ ሆነ ይነግሩኝ ዘንድ ጠቢባንና አስማተኞች በፊቴ ቀርበው ነበር፤ ነገር ግን ሊገልጡት አልቻሉም። 16አንተ ግን መተርጐምና አስቸጋሪ የሆነውን ነገር መፍታት እንደምትችል ሰምቻለሁ። ይህን ጽሕፈት አንብበህ ትርጕሙን ብትነግረኝ፣ ሐምራዊ መጐናጸፊያ ያለብሱሃል፤ የወርቅ ሐብል በዐንገትህ ያጠልቁልሃል፤ የመንግሥት ሦስተኛ ገዥም ትደረጋለህ።”

17ዳንኤልም ለንጉሡ እንዲህ ሲል መለሰ፤ “ስጦታዎችህን ለራስህ አድርግ፤ ሽልማቶችህንም ለሌላ ሰው ስጥ፤ ይሁን እንጂ ጽሕፈቱን ለንጉሡ አነብባለሁ፤ ትርጕሙ ምን እንደ ሆነም እነግረዋለሁ።

18“ንጉሥ ሆይ፤ ልዑል አምላክ ለአባትህ ለናቡከደነፆር ገናናነትንና ታላቅነትን፣ ክብርንና ግርማን ሰጠው። 19ከሰጠው ታላቅ ሥልጣን የተነሣ ሕዝቦችና መንግሥታት፣ ልዩ ልዩ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎችም ሁሉ ተንቀጠቀጡለት፤ ፈሩትም። ንጉሡም ሊገድል የፈለገውን ይገድል፣ ሊያድን የፈለገውን ያድን፣ ሊሾም የፈለገውን ይሾም፣ ሊያዋርድ የፈለገውንም ያዋርድ ነበር። 20ነገር ግን ልቡ በትዕቢት በጸናና በእብሪት በተሞላ ጊዜ ከዙፋኑ ተወገደ፤ ክብሩም ተገፈፈ። 21ከሰው መካከል ተሰደደ፤ የእንስሳም አእምሮ ተሰጠው፤ ከዱር አህዮች ጋር ኖረ፤ እንደ ከብትም ሣር በላ፤ ልዑል አምላክ በሰዎች መንግሥታት ላይ እንደሚገዛና እነርሱንም ለወደደው እንደሚሰጥ እስኪያውቅ ድረስ ሰውነቱ በሰማይ ጠል ረሰረሰ።

22“ቤልሻዛር ሆይ፤ አንተ ልጁ5፥22 ወይም ዘሩ ወይም ምትክ ሆነህ ይህን ሁሉ ብታውቅም፣ ራስህን ዝቅ አላደረግህም፤ 23ይልቁንም በሰማይ አምላክ ላይ በመታበይ፣ ራስህን ከፍ ከፍ አደረግህ፤ የመቅደሱን መጠጫዎች አስመጣህ፤ አንተና መኳንንትህ፣ ሚስቶችህና ቍባቶችህም የወይን ጠጅ ጠጣችሁባቸው፤ ማየት፣ መስማት፣ ማስተዋልም የማይችሉትን የብርና የወርቅ፣ የናስና የብረት፣ የዕንጨትና የድንጋይ አማልክትን አመሰገንህ። ሕይወትህንና መንገድህን ሁሉ በእጁ የያዘውን አምላክ ግን አላከበርህም። 24ስለዚህ እርሱ ጽሕፈቱን የጻፈውን እጅ ላከ።

25“የተጻፈውም ጽሕፈት፣

‘ማኔ፣ ማኔ፣ ቴቄል፣ ፋሬስ’5፥25 በአረማይክ ኢፋርሲን (ይኸውም ፋርሲንና ማለት ነው።) ይላል።

26“የቃሉም ትርጕም ይህ ነው፤

‘ማኔ’5፥26 ማኔ ማለት የተቍጠረ ወይም ምናን (ራሱን የቻለ አንድ የገንዘብ ክፍል) ማለት እግዚአብሔር የመንግሥትህን ዘመን ቈጠረው፤ ወደ ፍጻሜም አደረሰው ማለት ነው።

27‘ቴቄል’5፥27 ቴቄል ማለት የተመዘነ ወይም ሰቅል ሊሆን ይችላል። ማለት በሚዛን ተመዘንህ፤ ቀለህም ተገኘህ፣ ማለት ነው።

28‘ፋሬስ’5፥28 ፋሬስ የፋርሲን ነጠላ ቁጥር ሲሆን ተከፈለ ወይም ፐርሺያ ወይም የሰቅል እኩሌታ ማለት ሊሆን ይችላል። ማለት መንግሥትህ ተከፈለ፣ ለሜዶናውያንና ለፋርስ ሰዎች ተሰጠ ማለት ነው።”

29ከዚህ በኋላ በቤልሻዛር ትእዛዝ ዳንኤልን ሐምራዊ መጐናጸፊያ አለበሱት፣ የወርቅ ሐብል በዐንገቱ ላይ አጠለቁለት፤ የመንግሥቱም ሦስተኛ ገዥ ሆኖ ተሾመ።

30በዚያኑ ሌሊት የባቢሎናውያን5፥30 ወይም ከለዳውያን ንጉሥ ቤልሻዛር ተገደለ፤ 31የስድሳ ሁለት ዓመት ዕድሜ የነበረው ሜዶናዊው ዳርዮስም መንግሥቱን ወሰደ።