传道书 3 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

传道书 3:1-22

万物有时

1天下万物都有定期,

凡事都有定时。

2出生有时,死亡有时;

耕种有时,拔出有时;

3杀戮有时,医治有时;

拆毁有时,建造有时;

4哭泣有时,欢笑有时;

哀伤有时,雀跃有时;

5抛石有时,堆石有时3:5 抛石有时,堆石有时”意义不明,有犹太拉比说是“同房有时,分房有时”。

拥抱有时,避开有时;

6寻找有时,遗失有时;

保存有时,丢弃有时;

7撕裂有时,缝合有时;

沉默有时,发言有时;

8爱慕有时,憎恶有时;

争战有时,和好有时。

9那么,人劳碌做工有什么益处呢? 10我察觉上帝给世人重担,使他们忙碌不休。 11祂使万事各按其时变得美好,又把永恒的意识放在人心里,人却不能测透上帝从始至终的作为。 12我认识到,人生在世没有什么比欢乐、享受更好。 13人人都该吃喝、享受自己劳苦的成果,这是上帝的恩赐。 14我知道,上帝所做的都会存到永远,谁也不能增减。祂这样安排是叫人敬畏祂。 15现在的事并不是新事,未来的事也早已发生过。上帝使过去的事再次出现。

世间的不公

16我又看到日光之下,即使在公道和正义之地也有邪恶。 17我心里想:“不论义人或恶人,上帝必审判,因为万事万务都有受审之时。” 18我又想:“至于世人,上帝试验他们,是要他们知道自己与兽类无异。 19因为人和兽的际遇并无分别,两者都难逃一死,活着都靠一口气。人并不比兽强,一切都是虚空。 20两者都同归一处,出于尘土,也归于尘土。 21谁知道人的气息3:21 气息”或译“灵”,本节同。会向上升,兽的气息会降到地下呢?” 22因此,我觉得没有什么比人享受工作之乐更好,因为这是人当得的。人死后,谁能使他看到世间的事呢?

New Amharic Standard Version

መክብብ 3:1-22

ለሁሉም ጊዜ አለው

1ለሁሉም ነገር ጊዜ አለው፤

ከሰማይ በታች ለሚከናወነው ለማንኛውም ነገር ወቅት አለው፤

2ለመወለድ ጊዜ አለው፤ ለመሞትም ጊዜ አለው፤

ለመትከል ጊዜ አለው፤ ለመንቀልም ጊዜ አለው፤

3ለመግደል ጊዜ አለው፤ ለማዳንም ጊዜ አለው፤

ለማፍረስ ጊዜ አለው፤ ለመገንባትም ጊዜ አለው፤

4ለማልቀስ ጊዜ አለው፤ ለመሣቅም ጊዜ አለው፤

ለሐዘን ጊዜ አለው፤ ለጭፈራም ጊዜ አለው፤

5ድንጋይ ለመጣል ጊዜ አለው፤ ድንጋይ ለመሰብሰብም ጊዜ አለው፤

ለመተቃቀፍ ጊዜ አለው፤ ለመለያየትም ጊዜ አለው፤

6ለመፈለግ ጊዜ አለው፤ ለመተው ጊዜ አለው፤

ለማስቀመጥ ጊዜ አለው፤ አውጥቶ ለመጣልም ጊዜ አለው፤

7ለመቅደድ ጊዜ አለው፤ ለመስፋትም ጊዜ አለው፤

ለዝምታ ጊዜ አለው፤ ለመናገርም ጊዜ አለው፤

8ለመውደድ ጊዜ አለው፤ ለመጥላትም ጊዜ አለው፤

ለጦርነት ጊዜ አለው፤ ለሰላምም ጊዜ አለው።

9ሠራተኛ ከጥረቱ የሚያገኘው ትርፍ ምንድን ነው? 10ሰዎች ይደክሙበት ዘንድ እግዚአብሔር የሰጣቸውን ከባድ የሥራ ጫና አየሁ። 11ሁሉንም ነገር በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው፤ በሰዎችም ልብ ዘላለማዊነትን አኖረ፤ ይሁን እንጂ እግዚአብሔር ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ያደረገውን ማወቅ አይችሉም። 12ለሰዎች፣ በሕይወት እያሉ ደስ ከመሰኘትና መልካምን ነገር ከማድረግ የተሻለ ነገር እንደሌለ ዐወቅሁ። 13ሰው ሁሉ ይበላና ይጠጣ ዘንድ፣ በሚደክምበትም ሁሉ ርካታን ያገኝ ዘንድ ይህ የእግዚአብሔር ችሮታ ነው። 14እግዚአብሔር ያደረገው ሁሉ ለዘላለም እንደሚኖር ዐውቃለሁ፤ በእርሱ ላይ ምንም አይጨመርም፤ ከእርሱም ምንም አይቀነስም፤ ሰዎች ያከብሩት ዘንድ ይህን አደረገ።

15አሁን ያለው ከዚህ በፊት የነበረው ነው፤

ወደ ፊት የሚሆነውም ቀድሞ የነበረ ነው፤

እግዚአብሔርም ያለፈውን መልሶ ይሻዋል3፥15 ወይም እግዚአብሔር ያለፈውን መልሶ ይጠራዋል

16ከፀሓይ በታችም ሌላ ነገር አየሁ፤

በፍርድ ቦታ ዐመፅ ነበር፤

በፍትሕ ቦታ ግፍ ነበር።

17እኔም በልቤ፣

“ለማንኛውም ድርጊት፣

ለማንኛውም ተግባር ጊዜ ስላለው፣

እግዚአብሔር ጻድቁንና ኀጢአተኛውን ወደ ፍርድ ያመጣቸዋል”

ብዬ አሰብሁ።

18እንዲህም ብዬ አሰብሁ፤ “ሰዎች፣ እንደ እንስሳት መሆናቸውን ያዩ ዘንድ እግዚአብሔር ይፈትናቸዋል። 19የሰው ዕድል ፈንታ እንደ እንስሳት ነው፤ ሁለቱም ዕጣ ፈንታቸው አንድ ነው፤ አንዱ እንደሚሞት፣ ሌላውም እንዲሁ ይሞታል። ሁሉ አንድ ዐይነት እስትንፋስ3፥19 ወይም መንፈስ አላቸው፤ ሰውም ከእንስሳ ብልጫ የለውም፤ ሁሉም ከንቱ ነው። 20ሁሉም ወደ አንድ ቦታ ይሄዳሉ፤ ሁሉም ከዐፈር እንደ ሆኑ፣ ተመልሰው ወደ ዐፈር ይሄዳሉ። 21የሰው መንፈስ ወደ ላይ መውጣቱን፣ የእንስሳ እስትንፋስ3፥21 ወይም የሰው መንፈስ ወደ ላይ እንደሚሄድ ወይም የእንስሳት መንፈስ ደግሞ ወደ ታች ወደ ምድር መውረዱን ማን ያውቃል?”

22ስለዚህ ለሰው ዕጣ ፈንታው ስለሆነ፣ በሥራው ከመደሰት የተሻለ ነገር እንደሌለው አየሁ፤ ከእርሱ በኋላ የሚሆነውንስ ተመልሶ እንዲያይ የሚያደርገው ማን ነው?