箴言 1 – CCB & NASV

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

箴言 1:1-33

箴言的价值

1这是大卫的儿子以色列所罗门的箴言。

2为使人认识智慧和教诲,

领悟真知灼见;

3为使人接受劝诫,

为人处事仁义、公平、正直;

4使愚昧人明智,

使青年有知识和明辨力;

5使智者听了长学问,

明哲听了得指引;

6使人领悟箴言和比喻,

明白智者的话和谜语。

7知识始于敬畏耶和华,

愚人轻视智慧和教诲。

8孩子啊,

你要听从父亲的教诲,

不可背弃母亲的训言。

9因为这要作你头上的华冠,

颈上的项链。

10孩子啊,恶人若引诱你,

千万不要听从。

11他们若说:“跟我们来吧,

我们去埋伏杀人,

暗害无辜者取乐;

12我们要像阴间一样生吞他们,

整个吞没他们,

使他们如坠入坟墓的人;

13我们必得到各样宝物,

把战利品装满我们的房屋。

14跟我们一起干吧,

大家有福同享!”

15孩子啊,

不要走他们的道,

切莫行他们的路。

16因为他们奔向罪恶,

急速地去杀人流血。

17在飞鸟眼前设网罗,徒劳无功。

18他们埋伏,却自流己血;

他们伏击,却自害己命。

19这就是贪爱不义之财者的结局,

不义之财终要夺去他们的性命。

智慧的劝诫

20智慧在大街上高喊,

在广场上扬声,

21在热闹的市集宣告,

在城门口演说:

22“你们愚昧人喜爱愚昧,

嘲讽者以嘲弄为乐,

无知者厌恶知识,

要到什么时候呢?

23你们若因我的责备而回转,

我就向你们显明我的旨意1:23 我就向你们显明我的旨意”希伯来文是“我就将我的灵浇灌你们”。

叫你们明白我的话语。

24我呼唤你们,

你们却充耳不闻;

我向你们招手,

你们却视若无睹。

25你们漠视我的劝诫,

不接受我的责备。

26因此,

你们遭遇灾难时,

我必发笑;

惊恐临到你们时,

我必嗤笑——

27那时,恐惧如风暴袭击你们,

灾难如旋风临到你们,

忧愁和苦难吞没你们。

28你们呼求我,

我也不回答;

你们恳切地寻找我,

却找不到。

29因为你们厌恶知识,

不愿意敬畏耶和华,

30不接受我的劝诫,

又藐视我的责备。

31所以,你们必自食其果,

因自己的恶谋而吃尽苦头。

32愚昧人背离正道,

自招灭亡;

愚顽人逍遥自在,

毁掉自己。

33然而,那听从我的必安然居住,

得享安宁,

不怕灾祸。”

New Amharic Standard Version

ምሳሌ 1:1-33

መግቢያ፤ የምሳሌዎቹ ዐላማና ጭብጥ

1የእስራኤል ንጉሥ፣ የዳዊት ልጅ የሰሎሞን ምሳሌዎች፤

2ጥበብንና ተግሣጽን ለመቀበል፤

ጥልቅ ሐሳብ የሚገልጡ ቃላትን ለማስተዋል፤

3ጽድቅን፣ ፍትሕንና ሚዛናዊ ብያኔን በማድረግ፣

የተገራ ጠቢብ ልቦናን ለማግኘት፤

4ብስለት ለሌላቸው አስተዋይነትን፣

በዕድሜ ለጋ ለሆኑት ዕውቀትንና ልባምነትን ለመስጠት፤

5ጥበበኞች ያድምጡ፤ ትምህርታቸውንም ያዳብሩ፤

አስተዋዮችም መመሪያ ያግኙበት፤

6ይህም የጠቢባንን ምሳሌዎችና ተምሳሌቶች፣

አባባሎችና ዕንቈቅልሾች ይረዱ ዘንድ ነው።

7እግዚአብሔርን መፍራት የዕውቀት መጀመሪያ ነው፤

ተላሎች1፥7 በመጽሐፈ ምሳሌና በብሉይ ኪዳን ሌሎች መጻሕፍት ውስጥ ተላላ የሚለው በተደጋጋሚ ተጽፏል፤ ይህም የሞራል ጕድለትን ያመለክታል። ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ።

ጥበብን ገንዘብ ለማድረግ የተሰጠ ምክር

8ልጄ ሆይ፤ የአባትህን ምክር አድምጥ፤

የእናትህንም ትምህርት አትተው።

9ለራስህ ሞገስን የሚያጐናጽፍ አክሊል፣

ዐንገትህን የሚያስውብ ድሪ ይሆንልሃል።

10ልጄ ሆይ፤ ኀጢአተኞች ቢያባብሉህ፣

እሺ አትበላቸው፤

11“ከእኛ ጋር ናና፣ ደም ለማፍሰስ እናድባ፤

በደል በሌለበት ሰው ላይ እንሸምቅ፤

12እንደ መቃብር፣ ወደ ጕድጓድ1፥12 በዕብራይስጡ ሲኦል ይላል። እንደሚወርዱ፣

ከነሕይወታቸው እንዳሉ እንዋጣቸው፤

13ውድ የሆኑ ነገሮችን ሁሉ በየዐይነቱ እናገኛለን፤

ቤቶቻችንንም በዝርፊያ እንሞላለን፤

14ከእኛ ጋር ዕጣህን ጣል፤

የጋራ ቦርሳ ይኖረናል” ቢሉህ፣

15ልጄ ሆይ፤ አብረሃቸው አትሂድ፤

በሚሄዱበትም መንገድ እግርህን አታንሣ፤

16እግራቸው ወደ ኀጢአት ይቸኵላል፤

ደም ለማፍሰስም ፈጣኖች ናቸው።

17ወፎች ፊት እያዩ ወጥመድ መዘርጋት፣

ምንኛ ከንቱ ነው!

18እነዚህ ሰዎች የሚያደቡት በገዛ ደማቸው ላይ ነው፤

የሚሸምቁትም በራሳቸው ላይ ብቻ ነው።

19ያላግባብ ለጥቅም የሚሯሯጡ ሁሉ መጨረሻቸው እንዲህ ነው፤

የሕይወታቸው መጥፊያም ይኸው ነው።

ጥበብን ለሚያናንቁ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

20ጥበብ በጐዳና ላይ ጮኻ ትጣራለች፤

በየአደባባዩ ድምፅዋን ከፍ ታደርጋለች፤

21ዉካታ በበዛባቸው ጐዳናዎች ላይ1፥21 በዕብራይስጡና በሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች በቅጥሮች ጫፍ ላይ ይላሉ። ትጮኻለች፤

በከተማዪቱም መግቢያ በር ላይ እንዲህ ትላለች፤

22“እናንት ብስለት የሌላችሁ1፥22 በዕብራይስጡ ብስለት የሌለው የሚለው ቃል በዚህ መጽሐፍ በአጠቃላይ መልካም ምግባር የሌለውንና ክፋትን ለማድረግ ልቡ ያዘነበለ ሰውን ያመለክታል። ማስተዋል የሌለበት መንገዳችሁን እስከ መቼ ትወዱታላችሁ?

ፌዘኞች በፌዝ ደስ የሚሰኙት፣

ሞኞችስ ዕውቀትን የሚጠሉት እስከ መቼ ነው?

23ዘለፋዬን ብትሰሙኝ ኖሮ፣

ልቤን ባፈሰስሁላችሁ፣

ሐሳቤንም ባሳወቅኋችሁ ነበር።

24ነገር ግን በተጣራሁ ጊዜ እንቢ ስላላችሁኝ፣

እጄንም ስዘረጋ ማንም ግድ ስላልነበረው፣

25ምክሬን ሁሉ ስለ ናቃችሁ፣

ዘለፋዬንም ስላልተቀበላችሁ፣

26እኔ ደግሞ በመከራችሁ እሥቅባችኋለሁ፤

መዓት በሚወርድባችሁም ጊዜ አፌዝባችኋለሁ፤

27መዓት እንደ ማዕበል ሲያናውጣችሁ፣

መከራም እንደ ዐውሎ ነፋስ ሲጠራርጋችሁ፣

ሥቃይና ችግር ሲያጥለቀልቃችሁ አፌዝባችኋለሁ።

28“በዚያን ጊዜ ይጠሩኛል፤ እኔ ግን አልመልስላቸውም፤

አጥብቀው ይፈልጉኛል፤ ነገር ግን አያገኙኝም።

29ዕውቀትን ስለ ጠሉ፣

እግዚአብሔርንም መፍራት ስላልመረጡ፣

30ምክሬን ለመቀበል ስላልፈለጉ፣

ዘለፋዬን ስለ ናቁ፣

31የመንገዳቸውን ፍሬ ይበላሉ፤

የዕቅዳቸውንም ውጤት ይጠግባሉ።

32ብስለት የሌላቸውን ስድነታቸው ይገድላቸዋል፤

ተላሎችንም ቸልተኝነታቸው ያጠፋቸዋል፤

33የሚያዳምጠኝ ሁሉ ግን በሰላም ይኖራል፤

ክፉን ሳይፈራ ያለ ሥጋት ይቀመጣል።”