ปัญญาจารย์ 10 – TNCV & NASV

Thai New Contemporary Bible

ปัญญาจารย์ 10:1-20

1แมลงวันตายทำให้น้ำหอมเหม็นคลุ้งฉันใด

ความโง่เขลานิดหน่อยก็อาจบั่นทอนสติปัญญาและเกียรติฉันนั้น

2ใจของคนฉลาดไขว่คว้าหาความถูกต้อง

ส่วนใจของคนโง่เอียงไปสู่ความชั่วร้าย

3คนโง่แม้เดินไปตามถนนหนทาง

ก็ยังไม่มีสำนึก

และทำให้คนดูออกว่าเขาโง่แค่ไหน

4หากเจ้านายโกรธเคืองท่าน

อย่าเพิ่งทิ้งหน้าที่ไป

ความสงบสยบความผิดพลาดใหญ่หลวงได้

5ข้าพเจ้าได้เห็นความชั่วร้ายอีกอย่างหนึ่งภายใต้ดวงอาทิตย์

เป็นความผิดที่เกิดขึ้นจากผู้ครอบครอง

6คือให้คนโง่ได้ตำแหน่งสูง

ขณะที่คนร่ำรวยอยู่ในตำแหน่งต่ำต้อย

7ข้าพเจ้าเห็นทาสนั่งบนหลังม้า

ขณะที่เจ้านายเดินเท้าไปเหมือนทาส

8คนที่ขุดหลุมอาจจะตกลงไปในหลุม

คนที่รื้อกำแพงอาจจะถูกงูกัด

9คนที่สกัดหินอาจได้รับบาดเจ็บเพราะหิน

คนที่เลื่อยซุงอาจได้รับอันตรายจากซุง

10หากขวานทื่อ

และไม่ได้ลับให้คม

เวลาใช้ก็ต้องออกแรงมากขึ้น

แต่ความเชี่ยวชาญจะนำความสำเร็จมาให้

11หมองูก็ไม่มีประโยชน์

หากเขาถูกกัดก่อนที่จะสะกดมันได้

12ถ้อยคำของคนฉลาดนั้นน่าฟัง

แต่คนโง่ย่อยยับเพราะลมปากของตัวเอง

13พอเริ่มพูดก็แสดงความโง่

พูดจบก็ยิ่งบ้าเลวทราม

14และต่อความยาวสาวความยืดไม่รู้จบ

ไม่มีใครรู้ว่าจะเกิดอะไรขึ้น

ใครเล่าจะบอกเขาได้ว่าจะเกิดอะไรขึ้นในภายหลัง?

15งานของคนโง่ทำให้เขาอ่อนระโหย

เขาไม่รู้จักทางเข้าเมือง

16วิบัติแก่เจ้า ดินแดนซึ่งมีคนรับใช้10:16 หรือเด็กเป็นกษัตริย์

และบรรดาเจ้านายกินเลี้ยงเฮฮากันตั้งแต่เช้า

17ความสุขมีแก่เจ้า ดินแดนที่กษัตริย์ของเจ้ามีคุณธรรมสูง

และเจ้านายรู้จักกินดื่มในเวลาอันควร

เพื่อให้มีกำลังวังชา ไม่ใช่เพื่อเมามาย

18หากผู้ใดเกียจคร้าน จันทัน10:18 หรือคานค้ำหลังคาก็ผุพัง

หากงอมืองอเท้า เรือนก็รั่ว

19งานเลี้ยงสังสรรค์ให้เสียงหัวเราะ

เหล้าองุ่นให้ชีวิตรื่นเริง

แต่เงินคือคำตอบสำหรับทุกสิ่ง

20อย่าแช่งด่ากษัตริย์ แม้แต่ในความคิดคำนึง

หรือแช่งด่าคนรวยในห้องนอนของท่าน

เพราะนกในอากาศอาจจะคาบวาจาของท่านไป

และนกที่โบยบินอาจจะรายงานสิ่งที่ท่านพูด

New Amharic Standard Version

መክብብ 10:1-20

1የሞቱ ዝንቦች ሽቶን እንደሚያገሙ፣

ትንሽ ሞኝነትም ጥበብንና ክብርን ያቀልላል።

2የጠቢብ ልብ ወደ ቀኝ፣

የሞኝ ልብ ግን ወደ ግራ ያዘነብላል።

3ሞኝ በጐዳና ሲሄድ ማስተዋል ይጐድለዋል፤

ጅል መሆኑንም ለማንም ይገልጻል።

4የገዥ ቍጣ በተነሣብህ ጊዜ፣

ስፍራህን አትልቀቅ፤

ትዕግሥት ታላቁን ጥፋት ጸጥ ያደርጋልና።

5ከፀሓይ በታች ያየሁት ክፉ ነገር አለ፤

ይህም ከገዥ የሚወጣ ስሕተት ነው፤

6ሞኞች በብዙ የክብር ስፍራዎች ሲቀመጡ፣

ሀብታሞች ግን በዝቅተኛ ስፍራ ሆነዋል።

7መሳፍንት እንደ ባሮች በእግራቸው ሲሄዱ፣

ባሮች ፈረስ ላይ ተቀምጠው አይቻለሁ።

8ጕድጓድን የሚምስ ራሱ ይገባበታል፤

ቅጥርንም የሚያፈርስ እባብ ይነድፈዋል።

9ድንጋይ የሚፈነቅል ይጐዳበታል፤

ግንድንም የሚፈልጥ አደጋ ላይ መውደቁ አይቀርም።

10መጥረቢያ ቢደንዝ፣

ጫፉም ባይሳል፣

ብዙ ጕልበት ይጨርሳል፤

ብልኀት ግን ለውጤት ያበቃል።

11እባብ በድግምት ከመፍዘዙ በፊት ቢነድፍ፣

ለደጋሚው ምንም አይጠቅመውም።

12ከጠቢብ አፍ የሚወጣ ቃል ባለ ሞገስ ነው፤

ሞኝ ግን በገዛ ከንፈሩ ይጠፋል፤

13ቃሉ በመጀመሪያ ሞኝነት ነው፤

በመጨረሻም ደግሞ ክፉ እብደት ነው፤

14ሞኙም ቃልን ያበዛል።

የሚመጣውን የሚያውቅ የለም፤

ከእርሱ በኋላ የሚሆነውንስ ማን ሊነግረው ይችላል?

15የሞኝ ሥራ ራሱን ያደክመዋል፤

ወደ ከተማ የሚወስደውንም መንገድ አያውቅም።

16አንቺ፣ ንጉሥሽ ልጅ10፥16 ወይም አሽከር የሆነ፣

መሳፍንትሽም በጧት ግብዣ የሚያደርጉ ምድር ሆይ፤ ወዮልሽ!

17አንቺ ንጉሥሽ ከተከበረው ዘር የሆነ፣

ለመስከር ሳይሆን ለብርታት፣

በተገቢው ጊዜ የሚበሉ መሳፍንት ያሉሽ ምድር ሆይ፤ የተባረክሽ ነሽ፤

18ሰው ሰነፍ ከሆነ ጣራው ይዘብጣል፤

እጆቹም ካልሠሩ ቤቱ ያፈስሳል።

19ግብዣ ለሣቅ ያዘጋጃል፤

ወይንም ሕይወትን ያስደስታል፤

ገንዘብም ካለ ሁሉ ነገር አለ።

20በዐሳብህም እንኳ ንጉሥን አትንቀፍ፤

በመኝታ ክፍልህም ባለጠጋን አትርገም፤

የሰማይ ወፍ ቃልህን ልትወስድ፣

የምትበረዋም ወፍ የምትለውን ልታደርስ ትችላለችና።