Isaiah 31 – NIV & NASV

New International Version

Isaiah 31:1-9

Woe to Those Who Rely on Egypt

1Woe to those who go down to Egypt for help,

who rely on horses,

who trust in the multitude of their chariots

and in the great strength of their horsemen,

but do not look to the Holy One of Israel,

or seek help from the Lord.

2Yet he too is wise and can bring disaster;

he does not take back his words.

He will rise up against that wicked nation,

against those who help evildoers.

3But the Egyptians are mere mortals and not God;

their horses are flesh and not spirit.

When the Lord stretches out his hand,

those who help will stumble,

those who are helped will fall;

all will perish together.

4This is what the Lord says to me:

“As a lion growls,

a great lion over its prey—

and though a whole band of shepherds

is called together against it,

it is not frightened by their shouts

or disturbed by their clamor—

so the Lord Almighty will come down

to do battle on Mount Zion and on its heights.

5Like birds hovering overhead,

the Lord Almighty will shield Jerusalem;

he will shield it and deliver it,

he will ‘pass over’ it and will rescue it.”

6Return, you Israelites, to the One you have so greatly revolted against. 7For in that day every one of you will reject the idols of silver and gold your sinful hands have made.

8“Assyria will fall by no human sword;

a sword, not of mortals, will devour them.

They will flee before the sword

and their young men will be put to forced labor.

9Their stronghold will fall because of terror;

at the sight of the battle standard their commanders will panic,”

declares the Lord,

whose fire is in Zion,

whose furnace is in Jerusalem.

New Amharic Standard Version

ኢሳይያስ 31:1-9

በግብፅ ለሚደገፉ ወዮላቸው

1ወደ እስራኤል ቅዱስ ለማይመለከቱ፣

ከእግዚአብሔርም ርዳታን ለማይሹ፣

ነገር ግን፤ ለርዳታ ብለው ወደ ግብፅ ለሚወርዱ፣

በፈረሶች ለሚታመኑ፣

በሠረገሎቻቸው ብዛት፣

በፈረሶቻቸውም ታላቅ ብርታት ለሚመኩ ወዮላቸው!

2እርሱም ግን ጠቢብ ነው፤ ጥፋትን ያመጣል፤

ቃሉን አያጥፍም።

በክፉ አድራጊዎች ቤት ላይ፣

በደለኞችንም በሚረዱ ላይ ይነሣል።

3ግብፃውያን ሰዎች እንጂ አምላክ አይደሉም፤

ፈረሶቻቸውም ሥጋ እንጂ መንፈስ አይደሉም፤

እግዚአብሔር እጁን ሲዘረጋ፣

ርዳታ ሰጪው ይሰናከላል፤

ተረጂውም ይወድቃል፤

ሁለቱም በአንድ ላይ ይጠፋሉ።

4እግዚአብሔር እንዲህ ብሎኛል፤

“አንበሳ ወይም የአንበሳ ደቦል

የሰበረውን ይዞ ሲያገሣ፣

ብዙ እረኞች

ተጠራርተው ሲመጡበት፣

ጩኸታቸው እንደማያስፈራው፣

በድምፃቸውም እንደማይታወክ፣

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር

በጽዮን ተራራና በከፍታዎቿ ላይ ለውጊያ እንዲሁ ይወርዳል።

5በዐናት ላይ እንደሚያንዣብቡ ወፎች፣

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር ኢየሩሳሌምን እንዲሁ ይጋርዳታል፤

ይከልላታል፤ ይታደጋታል፤

በላይዋ ያልፋል፤ ያድናታልም።”

6እናንተ እስራኤላውያን ሆይ፤ እጅግ ወዳመፃችሁበት ወደ እርሱ ተመለሱ። 7በዚያን ቀን በኀጢአት የተሞላ እጃችሁ የሠራቸውን የወርቅና የብር ጣዖቶች ሁላችሁም ትጥላላችሁና።

8“አሦር የሰው ባልሆነ ሰይፍ ይወድቃል፤

የሥጋ ለባሽ ያልሆነም ሰይፍ ይበላዋል።

ከሰይፍ ፊት ይሸሻል፤

ጕልማሶቹም የግዳጅ ሥራ ይሠራሉ።

9ጠንካራ ምሽጉ በሽብር ምክንያት ይወድቃል፤

መሪዎቹም የጦር ዐርማ ሲያዩ

በድንጋጤ ይዋጣሉ”

ይላል እሳቱ በጽዮን፣

ማንደጃውም በኢየሩሳሌም የሆነ እግዚአብሔር