مزمور 77 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 77:1-20

الْمَزْمُورُ السَّابِعُ وَالسَّبْعُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ عَلَى يَدُوثُونَ. لآسَافَ. مَزْمُورٌ

1إِلَى اللهِ أَرْفَعُ صَوْتِي، إِلَى اللهِ أَصْرُخُ فَيُصْغِي إِلَيَّ. 2فِي يَوْمِ ضِيقِي طَلَبْتُ الرَّبَّ. انْبَسَطَتْ يَدِي طُولَ اللَّيْلِ فَلَمْ تَكِلَّ. أَبَتْ نَفْسِي الْعَزَاءَ. 3أَذْكُرُ الرَّبَّ فَأَتَنَهَّدُ، أُنَاجِي نَفْسِي فَيُغْشَى عَلَى رُوحِي.

4أَمْسَكْتَ أَجْفَانِي عَنِ النَّوْمِ. اعْتَرَانِي الْقَلَقُ فَعَجَزْتُ عَنِ الْكَلامِ. 5فَكَّرْتُ فِي الأَيَّامِ الْقَدِيمَةِ وَفِي السِّنِينَ السَّحِيقَةِ. 6فِي اللَّيْلِ أَتَذَكَّرُ تَرْنِيمِي، وَأُنَاجِي قَلْبِي، وَتَجِدُّ فِي الْبَحْثِ نَفْسِي. 7هَلْ إِلَى الأَبَدِ يَرْفُضُنَا الرَّبُّ وَلَا يَرْضَى عَنَّا أَبَداً؟ 8هَلِ انْتَهَتْ رَحْمَتُهُ إِلَى الأَبَدِ؟ هَلِ انْقَطَعَتْ عَنَّا مَوَاعِيدُهُ؟ 9أَلَعَلَّ اللهَ نَسِيَ رَأْفَتَهُ؟ أَمْ حَبَسَ بِغَضَبٍ مَرَاحِمَهُ؟

10ثُمَّ قُلْتُ: «هَذَا يُسْقِمُنِي: أَنَّ يَمِينَ اللهِ الْعَلِيِّ قَدْ تَحَوَّلَتْ (عَنَّا).» 11أَذْكُرُ أَعْمَالَكَ يَا رَبُّ. أَذْكُرُ عَجَائِبَكَ الَّتِي عَمِلْتَهَا فِي الْقَدِيمِ، 12وَأَتَأَمَّلُ جَمِيعَ أَفْعَالِكَ وَأُنَاجِي بِكُلِّ مَا صَنَعْتَهُ.

13يَا اللهُ، إِنَّ طَرِيقَكَ هِيَ الْقَدَاسَةُ، فَأَيُّ إِلَهٍ عَظِيمٌ مِثْلُ اللهِ؟ 14أَنْتَ الإِلَهُ الصَّانِعُ الْعَجَائِبَ، وَقَدْ أَعْلَنْتَ قُوَّتَكَ بَيْنَ الشُّعُوبِ. 15بِذِرَاعِكَ القَدِيرَةِ افْتَدَيْتَ شَعْبَكَ بَنِي يَعْقُوبَ وَيُوسُفَ. 16رَأَتْكَ الْمِيَاهُ يَا اللهُ فَارْتَجَفَتْ وَاضْطَرَبَتْ أَعْمَاقُهَا أَيْضاً. 17سَكَبَتِ الْغُيُومُ مَاءً وَأَرْعَدَتِ السُّحُبُ، وَتَطَايَرَتْ سِهَامُكَ. 18(زَأَرَ) صَوْتُ رَعْدِكَ فِي الزَّوْبَعَةِ، فَأَضَاءَتِ الْبُرُوقُ الْمَسْكُونَةَ، وَارْتَعَدَتِ الأَرْضُ وَاهْتَزَّتْ. 19إِنَّمَا فِي الْبَحْرِ طَرِيقُكَ، وَمَسَالِكُكَ فِي الْمِيَاهِ الْغَامِرَةِ، وَآثَارُ خُطْوَاتِكَ لَا تُتَقَصَّى. 20هَدَيْتَ شَعْبَكَ كَقَطِيعٍ عَلَى يَدِ مُوسَى وَهَارُونَ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 77:1-20

መዝሙር 77

የእስራኤል ጥንተ ነገር አሰላስሎ

ለመዘምራን አለቃ፤ ለኤዶታም፤ የአሳፍ መዝሙር።

1ድምፄን ከፍ አድርጌ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፤

ይሰማኝም ዘንድ ወደ አምላክ ጮኽሁ።

2በመከራዬ ቀን እግዚአብሔርን ፈለግሁት፤

በሌሊትም ያለ ድካም እጆቼን ዘረጋሁ፤

ነፍሴም አልጽናና አለች።

3አምላክ ሆይ፤ አንተን ባሰብሁ ቍጥር ቃተትሁ፤

ባወጣሁ ባወረድሁም መጠን መንፈሴ ዛለች። ሴላ

4ዐይኖቼ እንዳይከደኑ ያዝሃቸው፤

መናገር እስኪሳነኝ ድረስ ታወክሁ።

5የድሮውን ዘመን አሰብሁ፤

የጥንቶቹን ዓመታት አውጠነጠንሁ።

6ዝማሬዬን በሌሊት አስታወስሁ፤

ከልቤም ጋር ተጫወትሁ፤ መንፈሴም ተነቃቅቶ እንዲህ ሲል ጠየቀ፦

7“ለመሆኑ፣ ጌታ ለዘላለም ይጥላልን?

ከእንግዲህስ ከቶ በጎነትን አያሳይምን?

8ምሕረቱስ ለዘላለም ጠፋን?

የገባውስ ቃል እስከ ወዲያኛው ተሻረን?

9እግዚአብሔር ቸርነቱን ዘነጋ?

ወይስ ከቍጣው የተነሣ ርኅራኄውን ነፈገ?” ሴላ

10እኔም፣ “የልዑል ቀኝ እጅ እንደ ተለወጠ ማሰቤ፣

ይህ ድካሜ ነው” አልሁ።

11የእግዚአብሔርን ሥራ አስታውሳለሁ፤

የጥንት ታምራትህን በርግጥ አስታውሳለሁ፤

12ሥራህን ሁሉ አሰላስላለሁ፤

ድንቅ ሥራህን ሁሉ አውጠነጥናለሁ።

13አምላክ ሆይ፤ መንገድህ ቅዱስ ነው፤

እንደ አምላካችን ያለ ታላቅ አምላክ ማን ነው?

14ታምራትን የምታደርግ አምላክ አንተ ነህ፤

በሕዝቦችም መካከል ኀይልህን ትገልጣለህ።

15የያዕቆብንና የዮሴፍን ልጆች፣

ሕዝብህን በክንድህ ተቤዠሃቸው። ሴላ

16አምላክ ሆይ፤ ውሆች አዩህ፤

ውሆች አንተን አይተው ተሸማቀቁ፤

ጥልቆችም ተነዋወጡ።

17ደመናት ውሃን አንጠባጠቡ፤

ሰማያት አንጐደጐዱ፤

ፍላጾችህም ዙሪያውን አብለጨለጩ።

18የነጐድጓድህ ድምፅ በዐውሎ ነፋስ ውስጥ ተሰማ፤

መብረቅህ ዓለምን አበራው፤

ምድርም ራደች፤ ተንቀጠቀጠች።

19መንገድህ በባሕር ውስጥ ነው፤

መሄጃህም በታላቅ ውሃ ውስጥ ነው፤

ዱካህ ግን አልታወቀም።

20በሙሴና በአሮን እጅ፣

ሕዝብህን እንደ በግ መንጋ መራኸው።