مزمور 76 – NAV & NASV

Ketab El Hayat

مزمور 76:1-12

الْمَزْمُورُ السَّادِسُ وَالسَّبْعُونَ

لِقَائِدِ الْمُنْشِدِينَ. عَلَى الآلاتِ الْوَتَرِيَّةِ. مَزْمُورٌ لآسَافَ. تَسْبِيحَةٌ.

1اللهُ مَعْرُوفٌ فِي يَهُوذَا وَاسْمُهُ مُعَظَّمٌ فِي إِسْرَائِيلَ. 2خَيْمَتُهُ فِي أُورُشَلِيمَ وَمَسْكَنُهُ فِي جَبَلِ صِهْيَوْنَ. 3هُنَاكَ حَطَّمَ السِّهَامَ الْبَارِقَةَ، وَالتُّرْسَ وَالسَّيْفَ وَكُلَّ أَسْلِحَةِ الْحَرْبِ.

4أَنْتَ أَمْجَدُ وَأَعْظَمُ جَلالاً مِنَ الْجِبَالِ الْخَالِدَةِ 5سَلَبْتَ أَبْطَالَهُمْ، فَنَامُوا نَوْمَ الْمَوْتِ، وَلَمْ تَنْفَعْهُمْ قُدْرَاتُهُمْ. 6مِنْ زَجْرِكَ يَا إِلَهَ يَعْقُوبَ تُصْرَعُ الْفُرْسَانُ وَالْخُيُولُ. 7إِنَّمَا أَنْتَ مَهُوبٌ، فَمَنْ يَقِفُ أَمَامَكَ فِي غَضَبِكَ؟ 8مِنَ السَّمَاءِ أَصْدَرْتَ حُكْماً فَلَمَّا سَمِعَتْهُ الأَرْضُ فَزِعَتْ وَصَمَتَتْ. 9كَانَ ذَلِكَ عِنْدَمَا قُمْتَ لِلْقَضَاءِ لِتُخَلِّصَ وُدَعَاءَ الأَرْضِ كُلَّهُمْ. 10حَقّاً يَحْمَدُكَ غَضَبُ الإِنْسَانِ، وَمَا تَبَقَّى مِنَ الْغَضَبِ تَتَمَنْطَقُ أَنْتَ بِهِ.

11انْذِرُوا وَأَوْفُوا لِلرَّبِّ إِلَهِكُمْ. يَا جَمِيعَ مَنْ حَوْلَهُ قَدِّمُوا هَدِيَّةً لِلْمَهُوبِ، 12فَهُوَ يَسْتَأْصِلُ أَرْوَاحَ رُؤَسَاءِ الأَرْضِ، وَيُرْهِبُ مُلُوكَهَا الْعُظَمَاءَ.

New Amharic Standard Version

መዝሙር 76:1-12

መዝሙር 76

ግርማው ለሚያስፈራው አምላክ የቀረበ ቅኔ

ለመዘምራን አለቃ፤ በበገናዎች፤ የአሳፍ መዝሙር ማሕሌት።

1እግዚአብሔር በይሁዳ ታወቀ፤

ስሙም በእስራኤል ታላቅ ነው።

2ድንኳኑ በሳሌም፣

ማደሪያውም በጽዮን ነው።

3በዚያም ተወርዋሪውን ፍላጻ፣

ጋሻንና ሰይፍን፣ ጦርንም ሰበረ። ሴላ

4አንተ ብርሃን ተላብሰህ ደምቀሃል፤

ግርማዊነትህም ከዘላለም ተራሮች ይልቃል።

5ልበ ሙሉ የሆኑት ተዘርፈዋል፤

አንቀላፍተውም ተኝተዋል፤

ከጦረኞቹም መካከል፣

እጁን ማንቀሳቀስ የቻለ የለም።

6የያዕቆብ አምላክ ሆይ፤ ከተግሣጽህ የተነሣ፣

ፈረስና ፈረሰኛው ጭልጥ ብለው ተኝተዋል።

7መፈራት ያለብህ አንተ ብቻ ነህ፤

በተቈጣህ ጊዜ ማን በፊትህ መቆም ይችላል?

8አንተ ፍርድን ከሰማይ አሰማህ፤

ምድርም ፈርታ ጸጥ አለች፤

9አምላክ ሆይ፤ ይህም የሆነው አንተ የምድር ጐስቋሎችን ለማዳን፣

ለፍርድ በተነሣህ ጊዜ ነው። ሴላ

10ሰውን ብትቈጣ እንኳ ለክብርህ ይሆናል፤

ከቍጣ የተረፉትንም ትገታቸዋለህ።76፥10 በሕዝብህ ላይ የምታወርደው ቍጣ ለክብርህ ይሆናል ወይም በቍጣውም መታሰቢያነት ራስህን ታስታጥቃለህ የሚሉ አሉ።

11ለአምላካችሁ ለእግዚአብሔር ተሳሉ፤ ስእለቱንም አግቡ፤

በእርሱ ዙሪያ ያሉ ሁሉ፣

አስፈሪ ለሆነው ለእርሱ እጅ መንሻ ያምጡ።

12እርሱ የገዦችን መንፈስ ይሰብራል፤

በምድር ነገሥታትም ዘንድ የተፈራ ነው።