2 ጢሞቴዎስ 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ጢሞቴዎስ 1:1-18

1በክርስቶስ ኢየሱስ ቃል በተገባው የሕይወት ተስፋ መሠረት፣ በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ፤

2ለተወዳጁ ልጄ፣ ለጢሞቴዎስ፤

ጸጋ፣ ምሕረትና ሰላም ከእግዚአብሔር አብ፣ ከጌታችንም ከክርስቶስ ኢየሱስ ይሁን።

ታማኝ ስለ መሆን የተሰጠ ማበረታቻ

3ሳላቋርጥ ሌሊትና ቀን በጸሎቴ ስለ አንተ ሳስብ፣ ቀደምት አባቶች እንዳደረጉት በንጹሕ ኅሊና የማመልከውን እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ። 4እንባህን እያስታወስሁ በደስታ እሞላ ዘንድ ላይህ እናፍቃለሁ። 5ግብዝነት የሌለበት እምነትህን አስታውሳለሁ፤ ይህ እምነት ቀድሞ በአያትህ በሎይድ እንዲሁም በእናትህ በኤውንቄ ዘንድ ነበረ፤ አሁን ደግሞ በአንተ እንዳለ ተረድቻለሁ። 6ስለዚህ በእጆቼ መጫን የተቀበልኸውን በአንተ ውስጥ ያለውን የእግዚአብሔርን ስጦታ እንድታቀጣጥል አሳስብሃለሁ። 7እግዚአብሔር የኀይልና የፍቅር፣ ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሀት መንፈስ አልሰጠንምና።

8እንግዲህ፣ ስለ ጌታችን ለመመስከር ወይም የእርሱ እስረኛ በሆንሁት በእኔ አትፈር፤ ነገር ግን በእግዚአብሔር ኀይል ስለ ወንጌል ከእኔ ጋር መከራን ተቀበል። 9እኛ ስላደረግነው አንዳች ነገር ሳይሆን፣ ከዕቅዱና ከጸጋው የተነሣ ያዳነን፣ ወደ ቅዱስ ሕይወትም የጠራን እርሱ ነው። ይህም ጸጋ ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ ተሰጠን፤ 10አሁን ግን ሞትን ደምስሶ በወንጌል አማካይነት ሕይወትንና ኢመዋቲነትን ወደ ብርሃን ባወጣው በመድኀኒታችን በክርስቶስ ኢየሱስ መምጣት ተገልጧል። 11እኔም ለዚህ ወንጌል የምሥራች ነጋሪና ሐዋርያ፣ አስተማሪም ሆኜ ተሾምሁ። 12መከራን የምቀበለውም ለዚሁ ነው፤ ሆኖም ያመንሁትን እርሱን ስለማውቅ አላፍርበትም፤ የሰጠሁትንም ዐደራ እስከዚያች ቀን ድረስ መጠበቅ እንደሚችል ተረድቻለሁ።

13ከእኔ የሰማኸውን በክርስቶስ ኢየሱስ ባለ እምነትና ፍቅር፣ የጤናማ ትምህርት ምሳሌ አድርገህ ያዝ። 14የተሰጠህን መልካሙን ዐደራ በእኛ ውስጥ በሚኖረው በመንፈስ ቅዱስ ጠብቅ።

15በእስያ አውራጃ ያሉት ሁሉ እንደ ተዉኝ ታውቃለህ፤ ከእነርሱም መካከል ፊሎጎስና ሄርዋጌኔስ ይገኛሉ።

16ጌታ ለሄኔሲፎሩ ቤተ ሰዎች ምሕረትን ይስጥ፤ ምክንያቱም ብዙ ጊዜ ቸርነት አድርጎልኛል፤ በታሰርሁበትም ሰንሰለት አላፈረም። 17እንዲያውም ወደ ሮም በመጣ ጊዜ ፈልጎ ፈልጎ አገኘኝ። 18በዚያች ቀን ምሕረትን ከጌታ ያገኝ ዘንድ ጌታ ይስጠው፤ በኤፌሶንም የቱን ያህል እንዳገለገለኝ አንተ በሚገባ ታውቃለህ።

Thai New Contemporary Bible

2ทิโมธี 1:1-18

1จดหมายฉบับนี้จากข้าพเจ้าเปาโลผู้เป็นอัครทูตของพระเยซูคริสต์โดยพระประสงค์ของพระเจ้าตามพระสัญญาแห่งชีวิตซึ่งอยู่ในพระเยซูคริสต์

2ถึงทิโมธีลูกที่รักของข้าพเจ้า

ขอพระคุณ พระเมตตา และสันติสุขจากพระเจ้าพระบิดาและพระเยซูคริสต์องค์พระผู้เป็นเจ้าของเรามีแก่ท่าน

ให้กำลังใจให้สัตย์ซื่อ

3เมื่อข้าพเจ้าระลึกถึงท่านในคำอธิษฐานอยู่เสมอทั้งวันทั้งคืน ข้าพเจ้าก็ขอบพระคุณพระเจ้าผู้ซึ่งข้าพเจ้ารับใช้อยู่ด้วยจิตสำนึกอันใสสะอาดเช่นเดียวกับบรรพบุรุษของข้าพเจ้า 4เมื่อหวนนึกถึงน้ำตาของท่าน ข้าพเจ้าก็อยากจะมาหาท่านเพื่อข้าพเจ้าจะได้เปี่ยมด้วยความชื่นชมยินดี 5ข้าพเจ้าคิดถึงความเชื่ออันจริงใจของท่าน ซึ่งตั้งแต่แรกนั้นก็มีอยู่ในโลอิสยายของท่านและในยูนีสมารดาของท่าน และข้าพเจ้าเชื่อว่าบัดนี้มีอยู่ในท่านเช่นกัน 6ด้วยเหตุนี้ข้าพเจ้าจึงขอเตือนท่านว่าจงทำให้ของประทานของพระเจ้าซึ่งมีอยู่ในตัวท่านผ่านทางการวางมือของข้าพเจ้านั้นรุ่งเรือง1:6 หรือพัดให้ติดไฟขึ้น 7เพราะพระเจ้าไม่ได้ทรงให้เรามีใจขลาดอาย แต่ประทานใจอันเปี่ยมด้วยฤทธิ์อำนาจ ความรัก และการรู้จักบังคับตนเองแก่เรา

8ดังนั้นอย่าละอายที่จะเป็นพยานเรื่ององค์พระผู้เป็นเจ้าของเราหรือละอายในตัวของข้าพเจ้าผู้ถูกจองจำเพื่อพระองค์ แต่จงร่วมทนทุกข์กับข้าพเจ้าเพื่อข่าวประเสริฐโดยฤทธิ์อำนาจของพระเจ้า 9ผู้ทรงช่วยเราให้รอดและทรงเรียกเรามาสู่ชีวิตอันบริสุทธิ์ ไม่ใช่เพราะการกระทำใดๆ ของเราแต่เพราะพระประสงค์และพระคุณของพระองค์เอง พระคุณนี้ได้ประทานแก่เราในพระเยซูคริสต์ตั้งแต่ก่อนจุดเริ่มต้นของเวลา 10แต่บัดนี้ทรงให้ประจักษ์แจ้งโดยการเสด็จมาของพระเยซูคริสต์พระผู้ช่วยให้รอดของเรา ผู้ได้ทรงทำลายความตายและทรงนำชีวิตกับความเป็นอมตะมาสู่ความสว่างโดยทางข่าวประเสริฐ 11และทรงแต่งตั้งข้าพเจ้าให้เป็นผู้ป่าวประกาศ เป็นอัครทูต และเป็นผู้สอนข่าวประเสริฐนี้ 12นั่นเป็นเหตุให้ข้าพเจ้าทนทุกข์อย่างที่เป็นอยู่ กระนั้นข้าพเจ้าก็ไม่ละอายเพราะข้าพเจ้ารู้จักพระองค์ที่ข้าพเจ้าเชื่อ และมั่นใจว่าพระองค์ทรงสามารถรักษาสิ่งที่ข้าพเจ้ามอบไว้กับพระองค์จนถึงวันนั้นได้

13จงยึดถือแบบอย่างของคำสอนอันมีหลักที่ท่านได้ยินจากข้าพเจ้าด้วยความเชื่อและความรักในพระเยซูคริสต์ 14สำหรับความจริงแห่งข่าวประเสริฐที่ท่านได้รับมอบหมายไว้นั้น จงพิทักษ์รักษาไว้โดยการช่วยเหลือจากพระวิญญาณบริสุทธิ์ผู้สถิตในเราทั้งหลาย

15ท่านก็ทราบว่าทุกคนในแคว้นเอเชียทิ้งข้าพเจ้าไปหมด รวมทั้งฟีเจลัสกับเฮอร์โมเกเนส

16ขอพระเจ้าทรงสำแดงพระเมตตาแก่ครอบครัวของโอเนสิโฟรัสเพราะเขาทำให้ข้าพเจ้าชื่นใจบ่อยครั้งและไม่ละอายเลยที่ข้าพเจ้าถูกจองจำอยู่ 17ตรงกันข้ามเมื่อเขาอยู่ในกรุงโรม เขาพยายามเที่ยวสืบหาข้าพเจ้าจนพบ 18ขอพระเจ้าทรงให้เขาได้รับพระเมตตาจากองค์พระผู้เป็นเจ้าในวันนั้นด้วยเถิด! ท่านก็ทราบดีว่าเมื่ออยู่ที่เมืองเอเฟซัสเขาได้ช่วยเหลือข้าพเจ้าในหลายๆ ด้าน