1 ጢሞቴዎስ 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ጢሞቴዎስ 1:1-20

1በአዳኛችን በእግዚአብሔር፣ ተስፋችንም በሆነው በክርስቶስ ኢየሱስ ትእዛዝ የክርስቶስ ኢየሱስ ሐዋርያ ከሆነው ከጳውሎስ፤

2በእምነት እውነተኛ ልጄ ለሆነው ለጢሞቴዎስ፤

ከእግዚአብሔር ከአባታችን፣ ከጌታችንም ከክርስቶስ ኢየሱስ ጸጋና ምሕረት፣ ሰላምም ይሁን።

ከሐሰተኛ የሕግ መምህራን ስለ መጠበቅ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

3ወደ መቄዶንያ በሄድሁ ጊዜ ዐደራ እንዳልሁህ፣ አንዳንድ ሰዎች ከእንግዲህ የሐሰት ትምህርት እንዳያስተምሩ ታዝዛቸው ዘንድ በዚያው በኤፌሶን ተቀመጥ፤ 4ደግሞም ለተረትና መጨረሻ ለሌለው የትውልዶች ታሪክ ራሳቸውን አሳልፈው እንዳይሰጡ እዘዛቸው። እነዚህ ነገሮች በእምነት ከሆነው ከእግዚአብሔር ሥራ ይልቅ ክርክርን ያነሣሣሉ። 5የዚህ ትእዛዝ ዐላማ ግን ከንጹሕ ልብ፣ ከበጎ ኅሊና እንዲሁም ከእውነተኛ እምነት የሚገኝ ፍቅር ነው። 6አንዳንዶች ከእነዚህ ነገሮች ዘወር ብለው ወደ ከንቱ ንግግር ተመልሰዋል። 7የሕግ መምህራን ለመሆን ይፈልጋሉ፤ ሆኖም ስለሚናገሩት ወይም አስረግጠው ስለሚሟገቱለት ነገር አያውቁም።

8ነገር ግን ሰው በአግባቡ ከተጠቀመበት፣ ሕግ መልካም መሆኑን እናውቃለን። 9ደግሞም ሕግ1፥9 ወይም ሕጉ የተሰጠው ለጻድቃን ሳይሆን፣ ለሕግ ተላላፊዎችና ለዐመፀኞች፣ ፈሪሀ እግዚአብሔር ለሌላቸውና ለኀጢአተኞች፣ ቅድስና ለሌላቸውና እግዚአብሔርን ለሚንቁ፣ አባትና እናታቸውን ለሚገድሉ፣ ለነፍሰ ገዳዮች መሆኑን እናውቃለን፤ 10እንዲሁም ለዘማውያን፣ ከወንድ ጋር ለሚተኙ ወንዶች፣ ሰውን ለሚሸጡና ለሚገዙ፣ ለውሸተኞች፣ በሐሰት ለሚምሉ፣ ጤናማ የሆነውን ትምህርት ለሚፃረሩ ሁሉ ነው። 11ይህ ጤናማ ትምህርት ቡሩክ የሆነው እግዚአብሔር ለእኔ በዐደራ ከሰጠኝ የክብር ወንጌል ጋር የሚስማማ ነው።

ለጳውሎስ የተሰጠው የጌታ ጸጋ

12በአገልግሎቱ በመሾም ታማኝ አድርጎ የቈጠረኝን፣ ብርታትም የሰጠኝን ጌታችንን ክርስቶስ ኢየሱስን አመሰግናለሁ። 13ምንም እንኳ ከዚህ በፊት ተሳዳቢ፣ አሳዳጅና ዐመፀኛ የነበርሁ ብሆንም፣ ባለማወቅና ባለማመን ስላደረግሁት ምሕረት ተደርጎልኛል፤ 14በክርስቶስ ኢየሱስ ከሆኑት እምነትና ፍቅር ጋርም የጌታችን ጸጋ ተትረፈረፈልኝ።

15“ክርስቶስ ኢየሱስ ኀጢአተኞችን ለማዳን ወደ ዓለም መጣ” የሚለው ቃል እውነተኛና ሰው ሁሉ ሊቀበለው የሚገባ ነው፤ ከኀጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ። 16ነገር ግን ክርስቶስ ኢየሱስ በእርሱ ለሚያምኑና የዘላለምን ሕይወት ለሚቀበሉ ወሰን የሌለው ትዕግሥቱን ከኀጢአተኞች ዋና በሆንሁት በእኔ እንደ ምሳሌ አድርጎ ያሳይ ዘንድ ምሕረትን አገኘሁ። 17እንግዲህ ዘላለማዊ ለሆነው፣ ለማይሞተው፣ ለማይታየውና ብቻውን አምላክ ለሆነው ንጉሥ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብርና ምስጋና ይሁን፤ አሜን።

18ልጄ ጢሞቴዎስ ሆይ፤ አስቀድሞ ስለ አንተ በተነገረው ትንቢት መሠረት ይህን ትእዛዝ እሰጥሃለሁ፤ ይኸውም እርሱን በመከተል መልካሙን ገድል እንድትጋደል ነው። 19እምነትና በጎ ኅሊናም ይኑርህ፤ አንዳንዶች ኅሊናቸውን ጥለው ባሕር ላይ አደጋ ደርሶበት እንደሚጠፋ መርከብ እምነታቸውን አጥፍተዋል። 20ከእነርሱም መካከል እንዳይሳደቡ ትምህርት ያገኙ ዘንድ ለሰይጣን አሳልፌ የሰጠኋቸው ሄሜኔዎስና እስክንድሮስ ይገኛሉ።

Thai New Contemporary Bible

1ทิโมธี 1:1-20

1จดหมายฉบับนี้จากข้าพเจ้าเปาโลผู้เป็นอัครทูตของพระเยซูคริสต์ตามพระบัญชาของพระเจ้าพระผู้ช่วยให้รอดของเรา และของพระเยซูคริสต์ผู้ทรงเป็นความหวังของเรา

2ถึงทิโมธีลูกแท้ของข้าพเจ้าในความเชื่อ

ขอพระคุณ พระเมตตา และสันติสุขจากพระเจ้าพระบิดาและพระเยซูคริสต์องค์พระผู้เป็นเจ้าของเรามีแก่ท่าน

คำเตือนเกี่ยวกับผู้สอนผิด

3ตามที่ข้าพเจ้าได้กำชับท่านเมื่อข้าพเจ้าไปยังแคว้นมาซิโดเนียว่าให้ท่านอยู่ที่เอเฟซัส เพื่อท่านจะได้กำชับบางคนไม่ให้สอนหลักข้อเชื่อผิดๆ อีกต่อไป 4ทั้งไม่ให้หมกมุ่นกับนิยายปรัมปราและลำดับวงศ์ตระกูลอันไม่รู้จบ ซึ่งเป็นการคาดเดาแบบส่งเดชมากกว่าจะส่งเสริมพระราชกิจของพระเจ้าซึ่งเป็นไปโดยความเชื่อ 5เป้าหมายของการกำชับนี้คือความรักอันมาจากใจบริสุทธิ์ จากจิตสำนึกที่ดีและจากความเชื่ออย่างจริงใจ 6บางคนหลงเตลิดไปจากสิ่งเหล่านี้ หันไปพูดจาไร้สาระ 7พวกเขาอยากจะเป็นครูสอนบทบัญญัติทั้งๆ ที่ไม่รู้ว่าตนเองพูดอะไรหรือยืนยันอย่างหนักแน่นถึงเรื่องอะไร

8เรารู้อยู่ว่าบทบัญญัตินั้นดีหากใช้ในทางที่ถูก 9ซึ่งหมายความว่าบทบัญญัติไม่ได้มีขึ้นเพื่อผู้ชอบธรรม แต่มีขึ้นเพื่อคนชอบแหกกฎกับคนกบฏ คนอธรรมกับคนบาป คนไม่บริสุทธิ์กับคนไม่มีศาสนา คนฆ่าพ่อกับคนฆ่าแม่ ฆาตกร 10คนสำส่อนและคนรักร่วมเพศ เพื่อคนค้าทาสกับคนโกหก และคนให้การเท็จ และเพื่อสิ่งอื่นๆ อีกสารพัดที่ขัดกับคำสอนอันมีหลัก 11ซึ่งสอดคล้องกับข่าวประเสริฐอันรุ่งโรจน์ของพระเจ้าผู้ทรงเป็นที่สรรเสริญ คือข่าวประเสริฐที่ทรงมอบหมายให้ข้าพเจ้าประกาศนี้

พระคุณของพระเจ้าต่อเปาโล

12ข้าพเจ้าขอบพระคุณพระเยซูคริสต์องค์พระผู้เป็นเจ้าของเราผู้ทรงประทานกำลังแก่ข้าพเจ้า เพราะพระองค์ทรงเห็นว่าข้าพเจ้าสัตย์ซื่อจึงทรงแต่งตั้งข้าพเจ้าให้รับใช้พระองค์ 13ถึงแม้ว่าครั้งหนึ่งข้าพเจ้าเคยหมิ่นประมาทพระองค์ ข่มเหงผู้เชื่อและก่อความรุนแรง แต่พระองค์ทรงกรุณาข้าพเจ้าเพราะข้าพเจ้าได้ทำไปด้วยความไม่รู้และไม่เชื่อ 14พระคุณขององค์พระผู้เป็นเจ้าของเราได้หลั่งลงมาแก่ข้าพเจ้าอย่างเหลือล้น พร้อมด้วยความเชื่อและความรักซึ่งอยู่ในพระเยซูคริสต์

15ข้อความนี้เป็นความจริงซึ่งสมควรแก่การยอมรับโดยไม่มีข้อกังขา คือพระเยซูคริสต์เสด็จเข้ามาในโลกเพื่อช่วยคนบาปให้รอด และในบรรดาคนบาปข้าพเจ้าเป็นตัวร้ายที่สุด 16แต่เนื่องด้วยเหตุนี้เองจึงทรงกรุณาข้าพเจ้าผู้เป็นตัวร้ายที่สุดในบรรดาคนบาป เพื่อพระเยซูคริสต์จะได้ทรงสำแดงความอดกลั้นพระทัยอันไม่จำกัดให้เป็นตัวอย่างแก่คนทั้งปวงที่จะเชื่อในพระองค์และรับชีวิตนิรันดร์ 17บัดนี้ขอพระเกียรติและพระสิริมีแด่จอมราชันองค์นิรันดร์ผู้ทรงอมตะและเราไม่อาจมองเห็นได้ ผู้ทรงเป็นพระเจ้าแต่ผู้เดียวนั้นตลอดกาลสืบๆ ไปเป็นนิตย์ อาเมน

18ทิโมธีลูกชายของข้าพเจ้า ที่ข้าพเจ้ากำชับท่านเช่นนี้ก็สอดคล้องกับคำเผยพระวจนะที่เคยมีมาเกี่ยวกับท่าน เพื่อเมื่อท่านปฏิบัติตามท่านจะได้ต่อสู้อย่างเข้มแข็ง 19จงยึดมั่นในความเชื่อและจิตสำนึกอันดี บางคนละทิ้งข้อนี้ทำให้ความเชื่อของตนอับปาง 20ในหมู่คนเหล่านี้ได้แก่ฮีเมเนอัสกับอเล็กซานเดอร์ ซึ่งข้าพเจ้ามอบไว้แก่ซาตานเพื่อเขาจะได้เรียนรู้ที่จะไม่หมิ่นประมาทพระเจ้า