2 ዮሐንስ 1 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

2 ዮሐንስ 1:1-13

1ሽማግሌው፤

በእውነት ለምወድዳት፣ እኔ ብቻ ሳልሆን እውነትን የሚያውቁ ሁሉ ለሚወድዷት ለተመረጠችው እመቤትና ለልጆቿ፤ 2በውስጣችን ከሚኖርና ከእኛ ጋር ለዘላለም ከሚሆን እውነት የተነሣ፤

3ከእግዚአብሔር አብና የአብ ልጅ ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ ምሕረትና ሰላም በእውነትና በፍቅር ከእኛ ጋር ይሆናል።

4ከልጆችሽ አንዳንዶቹ ከአብ በተሰጠን ትእዛዝ መሠረት በእውነት ጸንተው እየሄዱ በማግኘቴ እጅግ ደስ ብሎኛል። 5አሁንም እመቤት ሆይ፤ ከመጀመሪያ የነበረችውን እንጂ አዲስ ትእዛዝ አልጽፍልሽም፤ ይኸውም እርስ በርሳችን እንዋደድ ዘንድ ነው። 6ይህም ፍቅር፣ በትእዛዞቹ መሠረት እንመላለስ ዘንድ ነው። ትእዛዙም ከመጀመሪያ እንደ ሰማችሁት በፍቅር እንድትኖሩ ነው።

7ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የማያምኑ ብዙ አሳቾች ወደ ዓለም ወጥተዋል። እንዲህ ያለ ማንኛውም ሰው አታላይና የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው። 8እናንተም የደከማችሁበትን ዋጋ እንዳታጡ፣ ነገር ግን ሙሉ ሽልማት እንድትቀበሉ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። 9በክርስቶስ ትምህርት የማይኖርና ከትምህርቱ የሚወጣ ሁሉ አምላክ የለውም፤ በክርስቶስ ትምህርት የሚኖር ግን አብም ወልድም አለው። 10ማንም ወደ እናንተ ቢመጣ፣ ይህንም ትምህርት ባያመጣ በቤታችሁ አትቀበሉት፤ ሰላምም አትበሉት፤ 11የሚቀበለው ሰው፣ የክፉ ሥራው ተባባሪ ይሆናልና።

12የምጽፍላችሁ ብዙ ነገር ነበረኝ፤ ይሁን እንጂ በወረቀትና በቀለም እንዲሆን አልፈልግም፤ ዳሩ ግን ደስታችን ፍጹም ይሆን ዘንድ ወደ እናንተ መጥቼ ፊት ለፊት ላነጋግራችሁ ተስፋ አደርጋለሁ።

13የተመረጠችው የእኅትሽ ልጆች ሰላምታ ያቀርቡልሻል።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרתו השנייה של יוחנן השליח 1:1-13

1לכבוד המאמינה המשיחית, הגברת הבחירה, וילדיה האהובים עלי ועל כל הקהילה.

מאת יוחנן – הזקן בזקני הקהילה.

2‏-3אדוננו ואלוהינו יברך את כולנו בשלום, ברחמים ובאהבה, בזכות האמת החקוקה בלבנו לנצח.

4שמחתי מאוד לפגוש כאן אחדים מילדיך, ולהיווכח שהם מתנהגים כראוי, אוהבים את האמת ושומרים את מצוות ה׳.

5גברתי הנכבדה, ברצוני להזכיר לך את אחת המצוות הראשונות שציווה עלינו ה׳: לאהוב איש את רעהו. 6מי שבאמת אוהב את ה׳ עושה כל מה שה׳ מצווה עליו, והוא הרי ציווה עלינו מבראשית לאהוב איש את רעהו.

7היזהרו ממורי השקר שמסתובבים בכל מקום. אין הם מאמינים שישוע המשיח בא לעולם כבן־אדם בשר ודם. אנשים אלה הם אויבי האמת ושונאי המשיח. 8היזהרו לבל ישפיעו עליכם, פן תפסידו את הפרס שאתם ואני משתדלים מאוד להשיג. עשו הכול כדי לקבל את שכרכם המלא מהאדון. 9מי שמנסה להתחכם ולעבור על תורת המשיח – אין האלוהים איתו, ואילו אדם שנשאר נאמן לתורת המשיח – גם האלוהים וגם המשיח איתו.

10‏-11אם ירצה מישהו ללמד אתכם תורה ששונה מתורת המשיח, אל תזמינוהו לביתכם ואף אל תדברו איתו! שהרי כל מי שמעודד אותו נעשה שותף למעשיו הרעים.

12יש לי עוד הרבה לומר, אך לא אעלה זאת על הנייר, שכן אני מקווה לפגוש אתכם בקרוב פנים אל פנים, ואז נוכל לשוחח ולשמוח יחד.

13ילדי אחותך המאמינה מוסרים לך דרישת שלום חמה.