1 ዮሐንስ 5 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

1 ዮሐንስ 5:1-21

በእግዚአብሔር ልጅ ማመን

1ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዷል፤ አባትንም የሚወድድ ሁሉ ልጁንም እንደዚሁ ይወድዳል። 2እግዚአብሔርን ስንወድድና ትእዛዞቹን ስንፈጽም የእግዚአብሔርን ልጆች እንደምንወድድ በዚህ እናውቃለን፤ 3እግዚአብሔርን መውደድ ትእዛዞቹን መፈጸም ነውና። ትእዛዞቹም ከባድ አይደሉም፤ 4ምክንያቱም ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋል። ዓለምን የሚያሸንፈውም እምነታችን ነው። 5ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በስተቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማነው?

6በውሃና በደም የመጣው ይህ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ በውሃና በደም እንጂ በውሃ ብቻ አልመጣም። የሚመሰክረውም መንፈስ ነው፤ መንፈስ እውነት ነውና። 7ስለዚህ ሦስት ምስክሮች አሉት፤ 8እነርሱም5፥7-8 ጥንታዊ ባልሆነው በቩልጌት ቅጅ ላይ በሰማይ የሚመሰክሩት ሦስቱ ናቸው፤ እነርሱም አባት፣ ቃልና መንፈስ ቅዱስ ናቸው ይላል። 8 በምድር የሚመሰክሩት ሦስቱ ናቸው – ሆኖም ይህ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት በነበሩት የግሪክ ቅጆች ውስጥ አይገኝም። መንፈሱ፣ ውሃውና ደሙ ናቸው፤ ሦስቱም ይስማማሉ። 9የሰውን ምስክርነት ከተቀበልን፣ የእግዚአብሔር ምስክርነት ከዚያም ይልቃል፤ ይህ ስለ ልጁ የሰጠው የእግዚአብሔር ምስክርነት ነውና። 10በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን ሁሉ በልቡ ምስክር አለው፤ ማንም እግዚአብሔርን የማያምን ሁሉ እግዚአብሔር ስለ ልጁ የሰጠውን ምስክርነት ስላላመነ ሐሰተኛ አድርጎታል። 11ምስክርነቱም ይህ ነው፤ እግዚአብሔር የዘላለምን ሕይወት ሰጠን፤ ይህም ሕይወት ያለው በልጁ ነው። 12ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።

ማጠቃለያ ሐሳብ

13በእግዚአብሔር ልጅ ስም የምታምኑ እናንተ፣ የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ ይህን እጽፍላችኋለሁ፤ 14በእግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ ማንኛውንም ነገር እንደ ፈቃዱ ብንለምን እርሱ ይሰማናል። 15የምንለምነውን ሁሉ እንደሚሰማን ካወቅን፣ የለመንነውንም ነገር እንደ ተቀበልን እናውቃለን።

16ማንም ሰው ወንድሙ ለሞት የማያበቃ ኀጢአት ሲያደርግ ቢያየው ይጸልይ፤ እግዚአብሔርም ለሞት የማያበቃ ኀጢአት ላደረጉት ሕይወትን ይሰጣል። ለሞት የሚያበቃም ኀጢአት አለ፤ ስለዚህኛው ግን ይጸልይ አልልም። 17ዐመፅ ሁሉ ኀጢአት ነው፤ ለሞት የማያበቃም ኀጢአት አለ። 18ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኀጢአት እንደማያደርግ፣ ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጅ እንደሚጠብቀው፣ ክፉውም እንደማይነካው እናውቃለን። 19እኛ ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን፣ መላው ዓለምም በክፉው ሥር እንደ ሆነ እናውቃለን።

20የእግዚአብሔር ልጅ እንደ መጣ፣ እውነተኛ የሆነውን እርሱን እንድናውቅ ማስተዋልን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እኛም እውነተኛ በሆነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አለን። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።

21ልጆች ሆይ፤ ራሳችሁን ከጣዖቶች ጠብቁ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרתו הראשונה של יוחנן השליח 5:1-21

1כל המאמין שישוע הוא המשיח, בן־האלוהים ומושיענו, הוא בנו של אלוהים; וכל האוהב את האב אוהב גם את בניו. 2מידת אהבתנו לבני־אלוהים מצביעה על מידת אהבתנו לאלוהים. 3לאהוב את אלוהים פירושו לעשות כל מה שהוא אומר לנו, וזה כלל לא קשה, 4שכן כל בני־האלוהים מסוגלים לנצח את השטן בכוח האמונה בישוע המשיח.

5מי יכול להילחם ולנצח במערכה נגד השטן? רק מי שמאמין באמת שישוע הוא בן־האלוהים! 6זהו ישוע אשר בא במים ובדם – לא רק במים (בעת טבילתו), אלא גם בדם (בעת צליבתו). רוח הקודש הוא שמעיד על כך, והרוח מדבר אמת בלבד.5‏.6 ה 6 דברים אלה אמורים נגד הדעה שרווחה בחוגים מסוימים באותו זמן, שישוע קיבל את תכונתו האלוהית כשרוח הקודש ירדה עליו בעת טבילתו, והסתלקה ממנו בעת צליבתו. 7‏-8אם כן, יש לנו שלושה עדים שעדותם זהה לחלוטין: הרוח, המים והדם. 9הלא כולנו מאמינים לעדותם של אנשים בבית־משפט, אם כך, מה הקושי להאמין לעדותו של אלוהים? ואלוהים העיד שישוע בנו. 10כל המאמינים יודעים היטב בלבם שישוע הוא בן־האלוהים. מי שאינו מאמין עושה את אלוהים לשקרן, שכן אינו מאמין לעדותו של אלוהים על בנו. 11אלוהים העיד על כך שנתן לנו חיי נצח בבנו ישוע המשיח. 12לכן, המאמין בבן־האלוהים יש לו חיי נצח, ומי שאינו מאמין – אין לו.

13כתבתי זאת לכם, המאמינים בבן־האלוהים, כדי שתדעו שיש לכם חיי נצח. 14אנו בטוחים שאלוהים מקשיב לכל בקשותינו, בתנאי שאינן נגד רצונו. 15הואיל ואנחנו בטוחים שהוא מקשיב לכל בקשותינו, אנו יודעים ללא ספק שיענה לנו וימלא אותן.

16אם אתה רואה את אחיך המאמין חוטא חטא שאין עליו עונש מוות, עליך להתפלל בעדו ולבקש מאלוהים שיסלח לו. אלוהים באמת יסלח לו ויטהר אותו, ואף יעניק לו חיים חדשים. אולם אם אחיך ביצע חטא שעונשו מוות, תוכל לחסוך את תפילתך, כי אלוהים בין כך ובין כך לא יסלח לו.

17כמובן שכל מעשה רע הוא חטא, אך איני מתכוון לחטאים הרגילים שעליהם אלוהים סולח. אני מתכוון לחטא שאין עליו סליחה ומחילה.

18אדם המשתייך למשפחת אלוהים אינו חוטא בכוונה תחילה, כי המשיח בן־האלוהים שומר עלינו היטב, והשטן אינו יכול לגעת בנו. 19אנו יודעים, שאנו ילדי־אלוהים, ושכל העולם סביבנו נתון לשלטון השטן. 20אנחנו גם יודעים, שהמשיח בן־האלוהים בא לעולם, כדי לעזור לנו להכיר ולדעת את האל האמיתי. זהו האל היחיד והאמיתי וחיי הנצח!

21בני היקרים, היזהרו והישמרו מפני כל דבר, שעלול לתפוס את מקומו של אלוהים בלבכם. – אמן.