2 ዜና መዋዕል 1 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

2 ዜና መዋዕል 1:1-17

ሰሎሞን ጥበብ እንዲሰጠው ጠየቀ

1፥2-13 ተጓ ምብ – 3፥4-15

1፥14-17 ተጓ ምብ – 1ነገ 10፥26-292ዜና 9፥25-28

1አምላኩ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለ ነበር፣ እጅግም ስላገነነው፣ የዳዊት ልጅ ሰሎሞን በመንግሥቱ ላይ ተደላድሎ ተቀመጠ።

2ከዚያም ሰሎሞን ለመላው እስራኤል፣ ለሻለቆች፣ ለመቶ አለቆች፣ ለዳኞች፣ ለእስራኤል መሪዎች ሁሉ እንዲሁም ለየቤተ ሰቡ አለቆች ተናገረ። 3የእግዚአብሔር ባሪያ ሙሴ በምድረ በዳ የሠራው የአምላክ የመገናኛ ድንኳን በዚያ ስለ ነበር፣ ሰሎሞንና መላው ጉባኤ በገባዖን ወዳለው ኰረብታ ሄዱ። 4በዚያ ጊዜ ዳዊት የአምላክን ታቦት ከቂሪያት ይዓሪም በኢየሩሳሌም ድንኳን ተክሎ ወዳዘጋጀለት ስፍራ አምጥቶት ነበር፤ 5ይሁን እንጂ የሆር ልጅ፣ የኡሪ ልጅ ባስልኤል የሠራው መሠዊያ በገባዖን በእግዚአብሔር ማደሪያ ድንኳን ፊት ለፊት ይገኝ ነበር፤ ስለዚህ ሰሎሞንና ጉባኤው ይህንኑ ፈለጉ። 6ሰሎሞንም በእግዚአብሔር ፊት በመገናኛው ድንኳን ውስጥ ወዳለው ወደ ናሱ መሠዊያ ወጥቶ በላዩ ላይ አንድ ሺሕ የሚቃጠል መሥዋዕት አቀረበ።

7በዚያ ሌሊት እግዚአብሔር ለሰሎሞን ተገልጦ፣ “እንድሰጥህ የምትፈልገውን ሁሉ ጠይቀኝ” አለው።

8ሰሎሞን እግዚአብሔርን እንዲህ አለው፤ “ለአባቴ ለዳዊት ታላቅ በጎነት አድርገህለታል፤ እኔንም በእግሩ ተክተህ አንግሠኸኛል። 9አሁንም እግዚአብሔር አምላክ ሆይ፤ ያነገሥኸኝ ብዛቱ እንደ ትቢያ በሆነ ሕዝብ ላይ ስለሆነ፣ ለአባቴ ለዳዊት የሰጠኸው ተስፋ ይጽና። 10ይህን ሕዝብ ለመምራት እንድችል፣ ጥበብና ዕውቀትን ስጠኝ፤ ይህ ካልሆነ ይህን ታላቅ ሕዝብህን ማን ሊገዛ ይችላል?”

11እግዚአብሔርም ሰሎሞንን እንዲህ አለው፤ “የልብህ መሻት ይህ ስለሆነ፣ ብልጽግናና ሀብት ወይም የጠላቶችህን ነፍስ ወይም ረዥም ዕድሜ ስላልጠየቅህ፣ ነገር ግን ባነገሥሁህ ሕዝቤ ላይ የምትገዛበትን ጥበብና ዕውቀት ስለ ጠየቅህ፣ 12ጥበብና ዕውቀት ይሰጥሃል፤ እንዲሁም ከአንተ በፊት የነበረ ማንኛውም ንጉሥ ያላገኘውን፣ ከአንተ በኋላም የሚነሣው የማያገኘውን ብልጽግና፣ ሀብትና ክብር እሰጥሃለሁ።”

13ሰሎሞንም የመገናኛው ድንኳን ካለበት ከገባዖን ኰረብታ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ፤ በእስራኤልም ላይ ነገሠ።

14ሰሎሞን ሠረገሎችንና1፥14 ወይም ሠረገለኞች ተብሎ መተርጐም ይችላል። ፈረሶችን ሰበሰበ፤ እርሱም አንድ ሺሕ አራት መቶ ሠረገሎችና ዐሥራ ሁለት ሺሕ ፈረሶች ነበሩት፤ እነርሱንም በሠረገላ ከተሞችና እርሱ ባለበት በኢየሩሳሌም ከተማ አኖራቸው። 15ንጉሡም ወርቁና ብሩ በኢየሩሳሌም እንደ ተራ ድንጋይ እንዲበዛ፣ ዝግባውም በየኰረብታው ግርጌ እንደሚገኝ የሾላ ዛፍ እንዲበዛ አደረገ። 16የሰሎሞንም ፈረሶች የመጡት ከግብፅና ከቀዌ1፥16 ምናልባት ኪልቂያ ናት ነበር፤ ከቀዌ የገዟቸውም የንጉሡ ነጋዴዎች ነበሩ። 17ከግብፅ ያስገቧቸውም አንዱን ሠረገላ በስድስት መቶ ሰቅል1፥17 7 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ብር፣ አንዱን ፈረስ በአንድ መቶ አምሳ ሰቅል1፥17 1.7 ኪሎ ግራም ነው። ብር ገዝተው ነው። እነዚህንም ደግሞ ለኬጢያውያንና ለሶርያውያን ነገሥታት ሁሉ ይሸጡላቸው ነበር።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

历代志下 1:1-17

所罗门王求智慧

1大卫的儿子所罗门巩固了自己的王位。因为他的上帝耶和华与他同在,使他极其伟大。

2所罗门召集所有以色列人,包括千夫长、百夫长、审判官、首领和族长, 3与他们一起去基遍的丘坛,因为那里有上帝的会幕,是耶和华的仆人摩西在旷野制造的。 4大卫已经把上帝的约柜从基列·耶琳搬到耶路撒冷,因为他在那里为约柜搭了一个帐篷。 5户珥的孙子、乌利的儿子比撒列造的铜坛在基遍耶和华的会幕前,所罗门和会众就在那里求问耶和华。 6所罗门上到耶和华会幕前的铜坛那里,献上一千头祭牲作为燔祭。

7当天晚上,上帝向所罗门显现,问他:“你要我给你什么?只管求吧。” 8所罗门回答说:“你厚待我父大卫,并让我继位。 9耶和华上帝啊,求你成就你给我父大卫的应许。你立我为王,使我统治这多如地上尘土的百姓。 10现在,求你赐我智慧和知识以带领他们。不然,谁能治理这么多的百姓呢?” 11上帝对所罗门说:“你既然有此心愿,不为自己求富贵、资财、尊荣、长寿,也没有求灭绝你的敌人,只求智慧和知识以治理我的子民——我交在你王权之下的百姓, 12我必赐你智慧和知识,并且我还要赐你空前绝后的富贵、资财和尊荣。”

13于是,所罗门基遍丘坛的会幕前回到耶路撒冷治理以色列

所罗门王的兵力和财富

14所罗门组建了战车和骑兵,有一千四百辆战车、一万二千名骑兵,驻扎在屯车城和他所在的耶路撒冷15王使耶路撒冷的金银多如石头,使香柏木多如丘陵的无花果树。 16所罗门的马匹都是由王室商队从埃及古厄按定价买来的。 17他们从埃及买来的车马,每辆车六百块银子,每匹马一百五十块银子,他们也把车马卖给人诸王和亚兰诸王。