2 ነገሥት 24 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 24:1-20

1በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ምድሪቱን ወረረ፤ ኢዮአቄምም ሦስት ዓመት ገበረለት፤ ከዚያ በኋላ ግን ሐሳቡን ለውጦ በናቡከደነፆር ላይ ዐመፀ። 2እግዚአብሔርም በኢዮአቄም ላይ ባቢሎናውያን24፥2 ወይም ከለዳውያን፣ ሶርያውያን፣ ሞዓባውያንና አሞናውያን አደጋ ጣዮችን ላከበት፤ በአገልጋዮቹ በነቢያቱ አማካይነት በተነገረው በእግዚአብሔር ቃል መሠረት ይሁዳን ያጠፉ ዘንድ እነዚህን ላከ። 3ከፊቱ ያርቃቸው ዘንድ እነዚህ ነገሮች ሁሉ እግዚአብሔር ባዘዘው መሠረት በይሁዳ ላይ በትክክል ሊፈጸሙ ችለዋል፤ ይህም ምናሴ ስለ ሠራው ኀጢአትና ስለ ፈጸመውም ሁሉ፣ 4እንዲሁም ንጹሕ ደም ስላፈሰሰ ነው። ኢየሩሳሌምም በንጹሕ ደም እንድትጥለቀለቅ በማድረጉ፤ እግዚአብሔር ይቅርታ ለማድረግ አልፈለገም።

5በኢዮአቄም ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ሥራ የፈጸመውም ድርጊት ሁሉ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 6ኢዮአቄምም ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ ልጁ ዮአኪንም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

7የባቢሎንም ንጉሥ ከግብፅ ደረቅ ወንዝ እስከ ኤፍራጥስ ወንዝ የነበረውን ግዛቱን ሁሉ ወስዶበት ስለ ነበር፣ የግብፅ ንጉሥ ከአገሩ ዳግም ለዘመቻ አልወጣም።

የይሁዳ ንጉሥ ዮአኪን

24፥8-17 ተጓ ምብ – 2ዜና 36፥9-10

8ዮአኪን ሲነግሥ ዕድሜው ዐሥራ ስምንት ዓመት ነበር፤ እርሱም በኢየሩሳሌም ተቀምጦ ሦስት ወር ገዛ። እናቱ ኔስታ ትባላለች፤ እርሷም የኢየሩሳሌም ሰው የኤልናታን ልጅ ነበረች። 9አባቱ እንደ አደረገው ሁሉ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ክፉ አደረገ።

10በዚያን ጊዜ የባቢሎን ንጉሥ የናቡከደነፆር ጦር አለቆች ወደ ኢየሩሳሌም መጥተው ከበቧት፤ 11የጦር አለቆቹ ከበባ በሚያደርጉበትም ሰዓት ናቡከደነፆር ራሱ ወደ ከተማዪቱ መጣ። 12የይሁዳ ንጉሥ ዮአኪን፣ እናቱ፣ የክብር አጃቢዎቹ፣ መሳፍንቱና ሹማምቱ ሁሉ እጃቸውን ለባቢሎን ንጉሥ ሰጡ። የባቢሎን ንጉሥ በነገሠ በስምንተኛው ዓመት ዮአኪንን ማርኮ ወሰደው። 13እግዚአብሔር አስቀድሞ እንደ ተናገረው፣ ናቡከደነፆር የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስና የቤተ መንግሥቱን ሀብት በሙሉ አጋዘ፤ የእስራኤል ንጉሥ ሰሎሞን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ያሠራቸውንም የወርቅ ዕቃዎች ሁሉ ወሰደ። 14ደግሞም የኢየሩሳሌምን ሕዝብ እንዳለ የጦር አለቆቹንና ተዋጊዎቹን በሙሉ፣ የእጅ ባለሙያዎችንና ቀጥቃጮችን ሁሉ ጨምሮ በአጠቃላይ ዐሥር ሺሕ ሰው በምርኮ ወደ አገሩ ወሰደ። በዚያ የቀሩት የመጨረሻዎቹ ያገሪቱ ድኾች ብቻ ነበሩ። 15ናቡከደነፆር ዮአኪንን ማርኮ ወደ ባቢሎን ወሰደው፤ እንዲሁም የንጉሡን እናት፣ ሚስቶቹን፣ ሹማምቱና በአገር የታወቁትን ታላላቅ ሰዎችም ከኢየሩሳሌም ወደ ባቢሎን ወሰደ። 16ደግሞም የባቢሎን ንጉሥ በአጠቃላይ ብርቱ የሆኑትንና ለጦርነት ብቃት ያላቸውን ሰባት ሺሕ ተዋጊዎች፣ አንድ ሺሕ የእጅ ባለሙያዎችንና ቀጥቃጮችን በምርኮ ወደ ባቢሎን ወሰደ። 17ከዚያም የዮአኪንን አጎት ማታንያን በምትኩ አነገሠው፤ ስሙንም ሴዴቅያስ አለው።

የይሁዳ ንጉሥ ሴዴቅያስ

24፥18-20 ተጓ ምብ – 2ዜና 36፥11-16ኤር 52፥1-3

18ሴዴቅያስ ሲነግሥ ዕድሜው ሃያ አንድ ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ዐሥራ አንድ ዓመት ገዛ። እናቱ አሚጣል ትባላለች፤ እርሷም የልብና ሰው የኤርምያስ ልጅ ነበረች። 19ኢዮአቄም እንደ አደረገው ሁሉ፣ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ነገር አደረገ። 20እንግዲህ ይህ ሁሉ በኢየሩሳሌምና በይሁዳ ላይ ሊደርስ የቻለው ከእግዚአብሔር ቍጣ የተነሣ ነበር፤ በመጨረሻም ከፊቱ አራቃቸው።

የኢየሩሳሌም መውደቅ

25፥1-12 ተጓ ምብ – ኤር 39፥1-10

25፥1-21 ተጓ ምብ – 2ዜና 36፥17-20ኤር 52፥27

25፥22-26 ተጓ ምብ – ኤር 40፥7-941፥1-316-18

በዚህ ጊዜ ሴዴቅያስ በባቢሎን ንጉሥ ላይ ዐመፀ።

Persian Contemporary Bible

دوم پادشاهان 24:1-20

1در دورهٔ سلطنت يهوياقيم، نبوكدنصر، پادشاه بابل به اورشليم حمله كرد. يهوياقيم تسليم شد و سه سال به او باج و خراج پرداخت، اما بعد از آن، سر از فرمان وی پيچيد و شورش نمود. 2خداوند قشون بابلی، سوری، موآبی و عمونی را فرستاد تا همانطور كه بوسيلهٔ انبيا خبر داده بود، يهودا را نابود كنند. 3بدون شک اين بلاها به فرمان خداوند بر يهودا نازل شد. خداوند تصميم داشت يهودا را به سبب گناهان بی‌شمار منسی طرد كند، 4زيرا منسی اورشليم را از خون بی‌گناهان پر كرده بود و خداوند نخواست اين گناهان را ببخشد.

5شرح بقيهٔ رويدادهای دوران سلطنت يهوياقيم و كارهای او در كتاب «تاريخ پادشاهان يهودا» نوشته شده است. 6پس از مرگ يهوياقيم پسرش يهوياكين به جای او بر تخت سلطنت نشست. 7(پادشاه مصر ديگر از مرزهای خود خارج نشد، زيرا پادشاه بابل تمام متصرفات مصر را كه شامل يهودا هم می‌شد، از نهر مصر تا رود فرات، اشغال نمود.)

يهوياكين، پادشاه يهودا

(دوم تواريخ 36‏:9‏-10)

8يهوياكين هجده ساله بود كه پادشاه يهودا شد و سه ماه در اورشليم سلطنت كرد. (مادرش نحوشطا، دختر الناتان و از اهالی اورشليم بود.) 9يهوياكين مانند پدرش نسبت به خداوند گناه ورزيد.

10در دورهٔ سلطنت يهوياكين، قشون نبوكدنصر، پادشاه بابل، اورشليم را محاصره كرد. 11وقتی شهر در محاصره بود، خود نبوكدنصر هم به آنجا رسيد. 12يهوياكين و تمام مقامات و فرماندهان و خدمتگزاران دربارش و ملكهٔ مادر تسليم نبوكدنصر شدند.

پادشاه بابل در سال هشتم سلطنت خود، يهوياكين را زندانی كرد. 13طبق آنچه خداوند فرموده بود، بابلی‌ها تمام اشياء قيمتی خانهٔ خداوند، جواهرات كاخ سلطنتی و تمام ظروف طلا را كه سليمان پادشاه برای خانهٔ خداوند ساخته بود، به بابل بردند. 14نبوكدنصر اهالی اورشليم را كه شامل فرماندهان و سربازان، صنعتگران و آهنگران می‌شدند و تعدادشان به ده هزار نفر می‌رسيد به بابل تبعيد كرد، و فقط افراد فقير را در آن سرزمين باقی گذاشت.

15نبوكدنصر، يهوياكين را با مادر و زنان او، فرماندهان و مقامات مملكتی به بابل برد. 16همچنين تمام سربازان جنگ آزموده را كه هفت هزار نفر بودند و هزار صنعتگر و آهنگر را اسير كرده، به بابل برد. 17بعد پادشاه بابل متنيا عموی يهوياكين را به جای او به پادشاهی تعيين نمود و نامش را به صدقيا تغيير داد.

صدقيا، آخرين پادشاه يهودا

(دوم تواريخ 36‏:11‏-12؛ ارميا 52‏:1‏-3)

18صدقيا بيست و يک ساله بود كه پادشاه يهودا شد و يازده سال در اورشليم سلطنت نمود. (مادرش حموطل، دختر ارميا و از اهالی لبنه بود.) 19او مانند يهوياقيم نسبت به خداوند گناه ورزيد. 20خشم خداوند بر مردم اورشليم و يهودا افروخته شد و او ايشان را طرد نمود.