ኢዮስያስ ኪዳኑን ዐደሰ
23፥1-3 ተጓ ምብ – 2ዜና 34፥29-32
23፥4-20 ተጓ ምብ – 2ዜና 34፥3-7፤ 33
23፥21-23 ተጓ ምብ – 2ዜና 35፥1፡18-19
23፥28-30 ተጓ ምብ – 2ዜና 35፥20–36፥1
1ከዚያም ንጉሡ የይሁዳንና የኢየሩሳሌምን ሽማግሌዎች ሁሉ ጠራ። 2የይሁዳን ሰዎች ሁሉ፣ የኢየሩሳሌምን ከተማ ነዋሪዎች በሙሉ፣ ካህናቱንና ነቢያቱን ሁሉ ከልጅ እስከ ዐዋቂ አንድም ሰው ሳይቀር ይዟቸው ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መጣ። በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የተገኘውንም የኪዳኑን መጽሐፍ ቃል በጆሯቸው እንዲሰሙት በሙሉ አነበበላቸው። 3ንጉሡም በዐምደ ወርቁ አጠገብ በእግዚአብሔር ፊት ቆሞ እግዚአብሔርን እንደሚከተል ትእዛዞቹን፣ ደንቦቹን፣ ሥርዐቶቹን በፍጹም ልቡ፣ በፍጹምም ነፍሱ እንደሚጠብቅ፣ በዚህም መጽሐፍ የተጻፈውን ኪዳን እንደሚያጸና በእግዚአብሔር ፊት ኪዳኑን አደሰ፤ ከዚያም ሕዝቡ ሁሉ ለኪዳኑ ያላቸውን ታማኝነት አረጋገጡ።
4ንጉሡም ለበኣል፣ ለአሼራና ለሰማይ ከዋክብት ሰራዊት ሁሉ የተሠሩትን የመገልገያ ዕቃዎች በሙሉ፣ ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ እንዲያወጡ ሊቀ ካህናቱን ኬልቅያስን በሁለተኛ ማዕረግ ያሉትን ካህናትና የቤተ መቅደሱን በር ጠባቂዎች አዘዘ። ዕቃዎቹንም ከኢየሩሳሌም ውጭ በቄድሮን ሸለቆ ሜዳ ላይ አቃጠላቸው፤ ዐመዱንም ወደ ቤቴል ወሰደው። 5በይሁዳ ከተሞችና በኢየሩሳሌም ዙሪያ በሚገኙ ኰረብቶች ላይ ዕጣን እንዲያጥኑ የይሁዳ ነገሥታት የሾሟቸውን የጣዖት ካህናት አባረረ እንዲሁም ለበኣል፣ ለፀሓይና ለጨረቃ፣ ለስብስብ ከዋክብትና ለመላው የሰማይ ከዋክብት ሰራዊት የሚያጥኑትን አስወገደ። 6የአሼራንም ምስል ዐምድ ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አውጥቶ ከኢየሩሳሌም ውጭ ወዳለው ወደ ቄድሮን ሸለቆ ወስዶ አቃጠለው፤ አድቅቆ ፈጭቶም በሕዝቡ መቃብር ላይ በተነው። 7እንዲሁም ስለ አምልኮ ባዕድ ሥርዐት በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ የቤተ ጣዖት ወንደቃዎችን ክፍሎችና ሴቶች ለአሼራ መጋረጃ የሚፈትሉባቸውን ክፍሎች አፈረሰ።
8ኢዮስያስ የቤተ ጣዖት ካህናትን ሁሉ ከይሁዳ ከተማ ወደ ኢየሩሳሌም አወጣቸው፤ ከጌባ ጀምሮ እስከ ቤርሳቤህ ድረስ፣ ካህናቱ ዕጣን ያጥኑባቸው የነበሩትን የኰረብታ ማምለኪያ ስፍራዎችን አረከሰ። ከከተማዪቱ በር በስተ ግራ በኩል፣ በከተማዪቱ ገዥ በኢያሱ በር መግቢያ አጠገብ የነበሩትን የበሮቹን ማምለኪያ ስፍራዎች23፥8 ወይም፣ ከፍተኛ ቦታዎች አፈረሰ። 9የየኰረብታው ማምለኪያ ካህናት ኢየሩሳሌም ባለው በእግዚአብሔር መሠዊያ ላይ ባያገለግሉም እንኳ ከካህናት ወንድሞቻቸው ጋር እርሾ ያልነካው ቂጣ ይበሉ ነበር።
10በሄኖም ሸለቆ የነበረውን ቶፌት የተባለውን ማምለኪያ አረከሰ፤ ይኸውም ማንም ሰው ወንድ ወይም ሴት ልጁን ለሞሎክ በእሳት የሚቃጠል መሥዋዕት አድርጎ እንዳያቀርብበት23፥10 ወይም ወንድ ወይም ሴት ልጁን የገደለ ነው። 11የይሁዳ ነገሥታት ወደ እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መግቢያ ላይ ለፀሓይ አምልኮ የሰጧቸውን ፈረሶች ከዚያ አስወገደ። እነዚህም ናታን ሜሌክ በተባለ በአንድ ሹም ቤት አጠገብ በአደባባዩ ላይ ነበሩ። ኢዮስያስም ለፀሓይ አምልኮ የተሰጡትን ሠረገሎች አቃጠለ።
12የይሁዳ ነገሥታት በላይኛው የአካዝ እልፍኝ አጠገብ በሰገነቱ ላይ ያቆሟቸውን መሠዊያዎች፣ ምናሴም በሁለቱ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አደባባዮች ላይ ያሠራቸውን መሠዊያዎች አስወገደ፤ ስብርብራቸውን አወጣ፤ ድቃቂውንም አንሥቶ ወደ ቄድሮን ሸለቆ ጣለው። 13እንዲሁም ከኢየሩሳሌም በስተ ምሥራቅ ከርኩሰት ኰረብታ በስተ ደቡብ የነበሩትን የእስራኤል ንጉሥ ሰሎሞን ለሲዶናውያን የርኩሰት አምላክ ለአስታሮት፣ ለሞዓብ ሕዝቦች የርኩሰት አምላክ ለካሞሽ፣ ለአሞን ሕዝቦች የርኩሰት አምላክ ለሞሎክ ያሠራቸውን የኰረብታ ላይ ማምለኪያዎች ንጉሡ አረከሰ። 14አሁንም ኢዮስያስ ማምለኪያ የድንጋይ ሐውልቶችን ሰባበረ፤ የአሼራን ምስል ዐምዶች ቈራረጠ፤ ስፍራውንም በሙታን ዐጥንት ሞላው።
15እስራኤልን ባሳተው በናባጥ ልጅ በኢዮርብዓም የተሠራውን መሠዊያ፣ በቤቴል የነበረውን ያን የኰረብታ ማምለኪያ ስፍራ፣ መሠዊያው ያለበትን ያን የኰረብታ ማምለኪያ ስፍራ እንኳ እንደዚሁ አፈረሰ፤ ድንጋዮቹን ሰባበረ፤ እንደ ዱቄትም አደቀቃቸው፤ የአሼራንም ምስል ዐምድ አቃጠለ። 16ኢዮስያስ ዘወር ሲል በኰረብታው ላይ የነበሩትን መቃብሮች አየ፤ ዐፅሞቹንም ከየመቃብሩ አስወጣ፤ ያ የእግዚአብሔር ሰው አስቀድሞ እንደ ተናገረው፣ የእግዚአብሔር ቃል ይፈጸም ዘንድ፣ መሠዊያውን ለማርከስ ሲል ዐፅሞቹን በላዩ ላይ አቃጠለበት።
17ንጉሡም፣ “ያ የማየው የመቃብር ሐውልት የማን ነው?” ሲል ጠየቀ የከተማዪቱም ሰዎች፣ “ከይሁዳ መጥቶ አሁን አንተ ያደረግኸውን ነገር ሁሉ በቤቴል መሠዊያ ላይ እንደሚደርስ የተናገረ የዚያ የእግዚአብሔር ሰው መቃብር ነው” አሉት።
18ኢዮስያስም፣ “በሉ እንዳለ ተዉት፤ ዐፅሙን ማንም ሰው ከቦታው እንዳያንቀሳቅሰው” አለ፤ ስለዚህ የእርሱንና ከሰማርያ የመጣውን ነቢይ ዐፅም ሳይነኩ እንዳለ ተውት። 19ኢዮስያስም በቤቴል እንዳደረገው ሁሉ በሰማርያም ከተሞች ኰረብቶች ላይ የእስራኤል ነገሥታት አሠርተዋቸው የነበሩትንና እግዚአብሔርን ያስቈጡበትን ቤተ ጣዖቶች ሁሉ አስወገደ፤ አረከሳቸውም። 20ኢዮስያስ እነዚያን የየኰረብታውን ማምለኪያ ቦታ ካህናትን ሁሉ፣ በየመሠዊያው ላይ ዐረዳቸው፤ በመሠዊያዎቹ ላይ የሰው ዐፅም አቃጠለ፣ ከዚያም ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።
21ንጉሡም መላውን ሕዝብ፣ “በዚህ በኪዳኑ መጽሐፍ በተጻፈው መሠረት የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ፋሲካ አክብሩ” ብሎ አዘዘ። 22እስራኤልን ከመሩ ከመሳፍንት ዘመን ጀምሮ፣ በእስራኤልና በይሁዳ ነገሥታት ዘመን ሁሉ፣ እንደዚህ ያለ ፋሲካ መቼም ተከብሮ አያውቅም። 23በኢዮስያስ ዘመነ መንግሥት በዐሥራ ስምንተኛው ዓመት ግን ይህ ፋሲካ በኢየሩሳሌም ለእግዚአብሔር ተከበረ። 24ከዚህም በቀር ኢዮስያስ ሙታን አነጋጋሪዎችንና መናፍስት ጠሪዎችን፣ የየቤተ ሰቡ ሰውን አማልክት፣ ጣዖታትን እንዲሁም በይሁዳና በኢየሩሳሌም የተገኙትን ሌሎች አስጸያፊ ነገሮች ሁሉ አስወገደ፤ ይህን ያደረገውም ካህኑ ኬልቅያስ ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ባገኘው መጽሐፍ የተጻፈው የሕጉ ቃል ተፈጻሚነት እንዲኖረው ለማድረግ ነው። 25በሙሴ ሕግ በተጻፈው መሠረት በፍጹም ልቡ፣ በፍጹም ነፍሱ፣ በፍጹም ኀይሉ ወደ እግዚአብሔር የተመለሰ፣ እንደ ኢዮስያስ ያለ ንጉሥ፣ ከእርሱ በፊትም ሆነ ከእርሱ በኋላ ፈጽሞ አልተነሣም። 26ይህም ሆኖ እንኳ ለቍጣ እንዲነሣሣ ምናሴ ካደረጋቸው ነገሮች ሁሉ የተነሣ፣ እግዚአብሔር በይሁዳ ላይ ከነደደው ከአስፈሪው ቍጣው ገና አልበረደም ነበር። 27ስለዚህ እግዚአብሔር፣ “እስራኤልን እንዳስወገድሁ ሁሉ ይሁዳንም ከፊቴ አስወግዳለሁ፤ የመረጥኋትን ከተማ ኢየሩሳሌምንና፣ ‘ስሜ በዚያ ይሆናል’23፥27 1ነገ 8፥29 ይመ። ብዬ የተናገርሁለትን ይህን ቤተ መቅደስ እተዋለሁ” አለ።
28በኢዮስያስ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ሥራ፣ የፈጸመውም ሁሉ በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን?
29ኢዮስያስ ንጉሥ በነበረበት ዘመን የግብፅ ንጉሥ ፈርዖን ኒካዑ የአሦርን ንጉሥ ለመርዳት ወደ ኤፍራጥስ ወንዝ ወጥቶ ነበር፤ ንጉሥ ኢዮስያስም ጦርነት ሊገጥመው ወጣ፤ ሆኖም ፈርዖን ኒካዑ ፊት ለፊት ገጥሞት መጊዶ ላይ ገደለው። 30የኢዮስያስም አገልጋዮች ከመጊዶ ሬሳውን በሠረገላ ወደ ኢየሩሳሌም አምጥተው በገዛ መቃብሩ ቀበሩት። የአገሩም ሰዎች የኢዮስያስን ልጅ ኢዮአክስን ወሰዱት፤ ቀብተውም በአባቱ እግር አነገሡት።
የይሁዳ ንጉሥ ኢዮአክስ
23፥31-34 ተጓ ምብ – 2ዜና 36፥2-4
31ኢዮአክስ ሲነግሥ ዕድሜው ሃያ ሦስት ዓመት ነበር፤ እርሱም በኢየሩሳሌም ተቀምጦ ሦስት ወር ገዛ። እናቱ አሚጣል ትባላለች፤ እርሷም የልብና ሰው የኤርምያስ ልጅ ነበረች። 32አባቶቹ እንዳደረጉ ሁሉ፣ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ክፉ አደረገ። 33በኢየሩሳሌም ተቀምጦ እንዳይገዛም ፈርዖን ኒካዑ በሐማት ምድር ሪብላ በምትባል ቦታ በሰንሰለት አሰረው23፥33 ዕብራይስጡ ከዚህ ጋር ይስማማል፤ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ግን (2ዜና 36፥3 ይመ)፣ ኒካዑ በሐማት ምድር ሪብላ በምትባል ላይ አስወገደው፤ በይሁዳም ላይ መቶ መክሊት23፥33 3.4 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ብርና አንድ መክሊት23፥33 34 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ወርቅ ግብር ጣለበት። 34ፈርዖን ኒካዑ የኢዮስያስን ልጅ ኤልያቄምን በአባቱ በኢዮስያስ እግር አነገሠው፤ ኤልያቄም የተባለ ስሙንም ኢዮአቄም ብሎ ለወጠው። ነገር ግን ኢዮአክስን በምርኮ ወደ ግብፅ ወሰደው፤ እርሱም በዚያ ሞተ። 35ኢዮአቄምም ፈርዖን ኒካዑ የጠየቀውን ብርና ወርቅ ከፈለ፤ ይህን ለማድረግም የመሬት ግብር ጣለ፤ የአገሩም ሰዎች እንደ ገቢው መጠን ብሩንና ወርቁን እንዲከፍሉ አደረገ።
ኢዮአቄም የይሁዳ ንጉሥ
23፥36–24፥1፡5-6 ተጓ ምብ – 2ዜና 36፥5-8
36ኢዮአቄም ሲነግሥ ዕድሜው ሃያ አምስት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ዐሥራ አንድ ዓመት ገዛ። እናቱ ዘቢዳ ትባላለች፤ እርሷም የሩማ ተወላጅ የፈዳያ ልጅ ነበረች። 37ኢዮአቄም አባቶቹ እንደ አደረጉት ሁሉ፣ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ክፉ ነገር አደረገ።
يوشيا بتپرستی را ريشهكن میكند
(دوم تواريخ 34:3-7،29-33)
1پادشاه تمام بزرگان يهودا و اورشليم را احضار كرد 2و همگی، در حالی كه كاهنان و انبيا و مردم يهودا و اورشليم از كوچک تا بزرگ به دنبال آنها میآمدند، به خانهٔ خداوند رفتند. در آنجا پادشاه تمام دستورات كتاب عهد را كه در خانهٔ خداوند پيدا شده بود، برای آنها خواند.
3پادشاه نزد ستونی كه در برابر جمعيت قرار داشت، ايستاد و با خداوند عهد بست كه با دل و جان از دستورات و احكام او پيروی كند و مطابق آنچه كه در آن كتاب نوشته شده است رفتار نمايد. تمام جماعت نيز قول دادند اين كار را بكنند.
4سپس پادشاه به حلقيا، كاهن اعظم و ساير كاهنان و نگهبانان خانهٔ خداوند دستور داد تا تمام ظروفی را كه برای پرستش بعل، اشيره، آفتاب، ماه و ستارگان به کار میرفت از بين ببرند. پادشاه تمام آنها را در بيرون اورشليم در درهٔ قدرون سوزانيد و خاكستر آنها را به بيتئيل برد. 5او كاهنان بتها را كه بوسيلهٔ پادشاهان يهودا تعيين شده بودند بركنار كرد. اين كاهنان در بتخانههای بالای تپهها در سراسر يهودا و حتی در اورشليم به بعل و آفتاب و ماه و ستارگان و بتها قربانی تقديم میكردند. 6او بت شرمآور اشيره را از خانهٔ خداوند برداشته، آن را از اورشليم به درهٔ قدرون برد و سوزاند و خاكسترش را به قبرستان عمومی برده، روی قبرها پاشيد. 7خانههای لواط را نيز كه در اطراف خانهٔ خداوند بودند و زنان در آنجا برای بت اشيره لباس میبافتند، خراب كرد.
8او كاهنان خداوند را كه در ديگر شهرهای يهودا بودند به اورشليم باز آورد و تمام معبدهای بالای تپهها را كه در آنها قربانی میكردند از جبع تا بئرشبع در هم كوبيد. او همچنين بتخانهای را كه يهوشع، حاكم شهر اورشليم، در سمت چپ دروازهٔ شهر ساخته بود، خراب كرد. 9كاهنان بتخانهها اجازه نداشتند در خانهٔ خداوند خدمت كنند، ولی میتوانستند با ساير كاهنان از نان مخصوص فطير بخورند.
10پادشاه، قربانگاه توفت را كه در درهٔ حنوم بود خراب كرد تا ديگر كسی پسر يا دختر خود را برای بت مولک روی آن قربانی نكند. 11او اسبانی را كه پادشاهان يهودا به خدای آفتاب وقف كرده بودند از خانهٔ خدا بيرون راند و عرابههای آنها را سوزاند. (اينها در حياط خانهٔ خدا، نزديک دروازه و كنار حجرهٔ يكی از مقامات به نام نتنملک نگهداری میشدند.) 12سپس قربانگاههايی را كه پادشاهان يهودا بر پشت بام قصر آحاز ساخته بودند خراب كرد. در ضمن قربانگاههايی را كه منسی در حياط خانهٔ خداوند بنا كرده بود در هم كوبيد و تمام ذرات آن را در درهٔ قدرون پاشيد.
13او بتخانههای روی تپههای شرق اورشليم و جنوب كوه زيتون23:13 نسخهٔ عبری اين متن از کوه زيتون به عنوان «کوه فساد» ياد میکند. را نيز خراب كرد. (اين بتخانهها را سليمان برای عشتاروت، الهه صيدون و برای كموش، بت نفرتانگيز موآب و ملكوم، بت نفرتانگيز عمون ساخته بود.) 14او مجسمهها را خرد كرد و بتهای شرمآور اشيره را از بين برد و زمينی را كه آنها روی آن قرار داشتند با استخوانهای انسان پر ساخت. 15همچنين قربانگاه و بتخانهٔ بيتئيل را كه يربعام ساخته و بوسيلهٔ آنها بنیاسرائيل را به گناه كشانده بود، در هم كوبيد، سنگهای آنها را خرد كرد و بت شرمآور اشيره را سوزانيد. 16سپس يوشيا متوجه شد كه در دامنهٔ كوه چند قبر هست. پس به افرادش دستور داد تا استخوانهای درون قبرها را بيرون آورند و آنها را بر قربانگاه بيتئيل بسوزانند تا قربانگاه نجس شود. اين درست همان چيزی بود كه نبی خداوند دربارهٔ قربانگاه يربعام پيشگويی كرده بود.23:16 نگاه کنيد به اول پادشاهان 13:2. 17يوشيا پرسيد: «آن ستون چيست؟»
اهالی شهر به او گفتند: «آن قبر مرد خدايی است كه از يهودا به اينجا آمد و آنچه را كه شما امروز با قربانگاه بيتئيل كرديد، پيشگويی نمود.»
18يوشيای پادشاه گفت: «آن را واگذاريد و به استخوانهايش دست نزنيد.» بنابراين استخوانهای او و استخوانهای آن نبی سامری را نسوزانيدند.23:18 نگاه کنيد به اول پادشاهان 13:31و32.
19يوشيا تمام بتخانههای روی تپههای سراسر سامره را نيز از ميان برداشت. اين بتخانهها را پادشاهان اسرائيل ساخته بودند و با اين كارشان خداوند را به خشم آورده بودند. ولی يوشيا آنها را با خاک يكسان كرد، همانطور كه در بيتئيل كرده بود. 20كاهنان بتخانههای بالای تپهها را روی قربانگاههای خودشان كشت و استخوانهای مردم را روی آن قربانگاهها سوزانيد. سرانجام وی به اورشليم بازگشت.
يوشيا عيد پِسَح را جشن میگيرد
(دوم تواريخ 35:1-19)
21يوشيای پادشاه به قوم خود دستور داد تا آيين عيد پسح را همانطور كه بهوسیله خداوند، خدای ايشان در كتاب عهد نوشته شده است، برگزار نمايند. 22از زمان يوشع به بعد، هيچ رهبر يا پادشاهی در اسرائيل يا يهودا هرگز با چنين شكوهی عيد پسح را برگزار نكرده بود. 23اين عيد پسح در سال هجدهم سلطنت يوشيا در اورشليم برگزار شد.
ساير اقدامات يوشيا
24در ضمن، يوشيا احضار ارواح و جادوگری و هر نوع بتپرستی را در اورشليم و در سراسر آن سرزمين ريشهكن كرد، زيرا میخواست مطابق دستورات كتاب تورات كه حلقيا كاهن اعظم در خانهٔ خداوند پيدا كرده بود، رفتار كند. 25هيچ پادشاهی قبل از يوشيا و بعد از او نبوده كه اينچنين با تمام دل و جان و قوت خود از خداوند پيروی كند و تمام احكام موسی را اطاعت نمايد.
26ولی با وجود اين، خداوند از شدت خشم خود عليه يهودا كه مسبب آن منسی پادشاه بود، برنگشت. 27خداوند فرمود: «يهودا را نيز مثل اسرائيل طرد خواهم كرد و شهر برگزيدهٔ خود، اورشليم و خانهای را كه گفتم اسم من در آن خواهد بود، ترک خواهم نمود.»
پايان سلطنت يوشيا
(دوم تواريخ 35:20—36:1)
28شرح بقيهٔ رويدادهای دوران سلطنت يوشيا و كارهای او در كتاب «تاريخ پادشاهان يهودا» نوشته شده است. 29در آن روزها، نكو پادشاه مصر، با قشون خود به طرف رود فرات رفت تا به آشور در جنگ كمک كند. يوشيا در مجدو با او مقابله كرد، ولی در جنگ كشته شد. 30سردارانش جنازهٔ وی را بر عرابهای نهاده از مجدو به اورشليم بردند و او را در قبری كه از پيش تدارک ديده بود دفن كردند. مردم يهودا پسر او يهوآحاز را به پادشاهی خود انتخاب كردند.
يهوآحاز، پادشاه يهودا
(دوم تواريخ 36:2-4)
31يهوآحاز بيست و سه ساله بود كه پادشاه شد و سه ماه در اورشليم سلطنت كرد. (مادرش حموطل دختر ارميا از اهالی لبنه بود.) 32يهوآحاز مانند اجدادش نسبت به خداوند گناه ورزيد.
33نكو، پادشاه مصر، يهوآحاز را در ربله در سرزمين حمات زندانی كرد تا از فرمانروايی وی در اورشليم جلوگيری نمايد و از يهودا سه هزار و چهارصد كيلوگرم نقره و سی و چهار كيلوگرم طلا باج خواست. 34پادشاه مصر سپس الياقيم يكی ديگر از پسران يوشيا را انتخاب كرد تا در اورشليم سلطنت كند و اسم او را به يهوياقيم تبديل كرد. پادشاه مصر، يهوآحاز را به مصر برد و او در همانجا مرد. 35يهوياقيم از قوم خود ماليات سنگينی گرفت تا باجی را كه نكو، پادشاه مصر خواسته بود به او بدهد.
يهوياقيم، پادشاه يهودا
(دوم تواريخ 36:5-8)
36يهوياقيم بيست و پنج ساله بود كه پادشاه يهودا شد و يازده سال در اورشليم سلطنت كرد. (مادرش زبيده، دختر فدايه و اهل رومه بود.) 37يهوياقيم مانند اجدادش نسبت به خداوند گناه ورزيد.