2 ነገሥት 14 – NASV & PCB

New Amharic Standard Version

2 ነገሥት 14:1-29

የይሁዳ ንጉሥ አሜስያስ

14፥1-7 ተጓ ምብ – 2ዜና 25፥1-411-12

14፥8-22 ተጓ ምብ – 2ዜና 25፥17–26፥2

1የእስራኤል ንጉሥ የኢዮአካዝ ልጅ ዮአስ በነገሠ በሁለተኛው ዓመት፣ የይሁዳ ንጉሥ የኢዮአስ ልጅ አሜስያስ ነገሠ። 2በነገሠም ጊዜ ዕድሜው ሃያ አምስት ዓመት ነበር፤ በኢየሩሳሌም ተቀምጦም ሃያ ዘጠኝ ዓመት ገዛ። እናቱም ዮዓዳን የተባለች የኢየሩሳሌም ሴት ነበረች። 3እርሱም በእግዚአብሔር ፊት መልካም ነገር አደረገ፤ ነገር ግን አባቱ ዳዊት እንደ አደረገው ዐይነት አልነበረም፤ በማናቸውም ረገድ የአባቱን የኢዮአስን ፈለግ ተከተለ። 4በየኰረብታው ላይ ያሉት ማምለኪያዎች አልተወገዱም፤ ሕዝቡም በየኰረብታው ላይ መሥዋዕት ማቅረቡንና ዕጣን ማጤሱን እንደ ቀጠለ ነበር።

5አሜስያስ መንግሥቱን አጽንቶ ከያዘ በኋላ፣ ንጉሡን አባቱን የገደሉትን ሹማምት ገደላቸው፤ 6ይሁን እንጂ በሙሴ የሕግ መጽሐፍ እግዚአብሔር፣ “እያንዳንዱ በራሱ ኀጢአት ይገደል እንጂ አባቶች በልጆቻቸው፣ ልጆችም በአባቶቻቸው ኀጢአት አይገደሉ”14፥6 ዘዳ 2፥16 ይመ ሲል ያዘዘ በመሆኑ፣ የነፍሰ ገዳዩን ልጆች አልገደላቸውም።

7የጨው ሸለቆ በተባለው ቦታ ዐሥር ሺሕ ኤዶማውያንን ድል ያደረገ፣ ሴላን በጦርነት የያዘና እስከ ዛሬም ድረስ ዮቅትኤል ተብላ የምትጠራበትን ስም ያወጣላት አሜስያስ ነው።

8ከዚያም አሜስያስ የኢዩ የልጅ ልጅ፣ የኢዮአካዝ ልጅ ወደ ሆነው ወደ እስራኤል ንጉሥ ወደ ዮአስ፣ “ናና ፊት ለፊት ይዋጣልን” ሲል መልእክተኞች ላከበት።

9የእስራኤል ንጉሥ ዮአስ ግን ለይሁዳ ንጉሥ ለአሜስያስ እንዲህ ሲል ላከበት፤ “አንድ የሊባኖስ ኵርንችት፣ ለአንድ የሊባኖስ ዝግባ፣ ‘ሴት ልጅህን ለልጄ በሚስትነት ስጠው’ አለው፤ ከዚያም አንድ የሊባኖስ ዱር አውሬ መጥቶ ኵርንችቱን በእግሩ ረገጠው። 10በርግጥ ኤዶምን ድል አድርገሃል፤ ልብህ አለመጠን አይኵራራ። ድል በማድረግህ አትንጠራራ፤ ዐርፈህ ተቀመጥ! ጠብ በመጫር የራስህን፣ የይሁዳንስ ውድቀት ለምን ትሻለህ?”

11አሜስያስ ግን አልሰማም፤ ስለዚህ የእስራኤል ንጉሥ ዮአስ ወጣ፤ እርሱና የይሁዳ ንጉሥ አሜስያስም በይሁዳ ምድር በቤትሳሚስ ፊት ለፊት ጦርነት ገጠሙ።

12ይሁዳ በእስራኤል ድል ሆነ፤ እያንዳንዱም ወደ ድንኳኑ ሸሸ። 13የእስራኤል ንጉሥ ዮአስም የአካዝያስን የልጅ ልጅ፣ የኢዮአስን ልጅ የይሁዳን ንጉሥ አሜስያስን ቤትሳሚስ ላይ ማረከው። ከዚያም ዮአስ ወደ ኢየሩሳሌም ሄደ፤ ከኤፍሬም ቅጥር በር አንሥቶ የማእዘን ቅጥር በር እስከ ተባለው ድረስ ርዝመቱ አራት መቶ ክንድ14፥13 ዕብራይስጡ 180 ሜትር ይላል። የሆነውን ቅጥር አፈረሰ። 14በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስና በቤተ መንግሥቱ ግምጃ ቤቶች ያለውን ወርቅና ብር በሙሉ፣ በዚያም የተገኘውን ዕቃ ሁሉ በመውሰድ ምርኮኞችንም ይዞ ወደ ሰማርያ ተመለሰ። 15በዮአስ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ነገር፣ ያደረገውና የፈጸመው ሁሉ በይሁዳ ንጉሥ በአሜስያስ ላይ ያደረገው ጦርነት ጭምር በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 16ዮአስ ከአባቶቹ ጋር አንቀላፋ፤ በሰማርያም ከእስራኤል ነገሥታት ጋር ተቀበረ፤ ልጁ ኢዮርብዓምም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ። 17የኢዮአስ ልጅ የይሁዳ ንጉሥ አሜስያስም የእስራኤል ንጉሥ የኢዮአካዝ ልጅ ዮአስ ከሞተ በኋላ ዐሥራ አምስት ዓመት ኖረ። 18በአሜስያስ ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ነገር በይሁዳ ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን?

19አሜስያስ በኢየሩሳሌም ሤራ ስለ ጠነሰሱበት ሸሽቶ ወደ ላኪሶ ሄደ፤ እነርሱ ግን የሚከታተሉት ሰዎች ወደዚያው ልከው አስገደሉት፤ 20ሬሳውም በፈረስ ተጭኖ መጥቶ በዳዊት ከተማ ከአባቶቹ ጋር በኢየሩሳሌም ተቀበረ።

21ከዚያም የይሁዳ ሕዝብ በሙሉ ዕድሜው ዐሥራ ስድስት ዓመት የሆነውን ዓዛርያስን ወስደው በአባቱ በአሜስያስ ፈንታ አነገሡት። 22አሜስያስ ከአባቶቹ ጋር ካንቀላፋ በኋላ ኤላትን እንደ ገና ሠርቶ ወደ ይሁዳ የመለሳት ይኸው ዓዛርያስ14፥22 ኢዩስያስ ነበር።

የእስራኤል ንጉሥ ዳግማዊ ኢዮርብዓም

23የኢዮስያስ ልጅ አሜስያስ በይሁዳ በነገሠ በዐሥራ አምስተኛው ዓመት፣ የእስራኤል ንጉሥ የዮአስ ልጅ ኢዮርብዓም በሰማርያ ነገሠ፤ አርባ አንድ ዓመትም ገዛ። 24በእግዚአብሔርም ፊት ክፉ ነገር አደረገ፤ የናባጥ ልጅ ኢዮርብዓም እስራኤልን ካሳተበት ኀጢአት አልተመለሰም። 25የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር በጋትሔፌር ነቢይ፣ በአማቴ ልጅ በባሪያው በዮናስ አማካይነት እንደ ተናገረው፣ ከሐማት መተላለፊያ14፥25 ሊቦ አንሥቶ እስከ ሙት ባሕር14፥25 የዓረባ ባሕር ድረስ የነበረውን የእስራኤልን ድንበር ያስመለሰ ኢዮርብዓም ነው።

26ባሪያም ይሁን ነጻ ዜጋ፣ በእስራኤል የሚኖር ሁሉ እንዴት እጅግ ይሠቃይ እንደ ነበር እግዚአብሔር አየ፤ የሚረዳቸውም አልነበረም። 27ይሁን እንጂ እግዚአብሔር የእስራኤልን ስም ከምድረ ገጽ እንደሚያጠፋ ስላልተናገረ፣ በዮአስ ልጅ በኢዮርብዓም አማካይነት ታደጋቸው።

28በኢዮርብዓም ዘመነ መንግሥት የተከናወነው ሌላው ነገር፣ የፈጸመው ሁሉና ያደረጋቸው ጦርነቶች እንዲሁም የይሁዳ ግዛት የነበሩትን ደማስቆንና ሐማትን እንዴት ለእስራኤል እንዳስመለሰ በእስራኤል ነገሥታት ታሪክ ተጽፎ የሚገኝ አይደለምን? 29ኢዮርብዓም ከአባቶቹ ከእስራኤል ነገሥታት ጋር አንቀላፋ፤ ልጁ ዘካርያስም በእግሩ ተተክቶ ነገሠ።

Persian Contemporary Bible

دوم پادشاهان 14:1-29

امصيا، پادشاه يهودا

(دوم تواريخ 25‏:1‏-24)

1در دومين سال سلطنت يهوآش، پادشاه اسرائيل، امصيا (پسر يوآش) پادشاه يهودا شد. 2امصيا بيست و پنج ساله بود كه پادشاه شد و بيست و نه سال در اورشليم سلطنت كرد. مادرش يهوعدان نام داشت و اهل اورشليم بود. 3امصيا مانند پدرش يوآش هر چه در نظر خداوند پسنديده بود انجام می‌داد، اما نه به اندازهٔ جدش داوود. 4او بتخانه‌های روی تپه‌ها را از بين نبرد و از اين رو قوم هنوز در آنجا قربانی می‌كردند و بخور می‌سوزانيدند.

5وقتی امصيا زمام امور را در دست گرفت، افرادی را كه پدرش را كشته بودند، از بين برد، 6ولی فرزندان ايشان را نكشت، زيرا خداوند در تورات موسی امر فرموده بود كه پدران به سبب گناه پسران كشته نشوند و نه پسران برای گناه پدران؛ بلكه هر كس به سبب گناه خود مجازات شود. 7امصيا يكبار ده هزار ادومی را در درهٔ نمک كشت. همچنين شهر سالع را تصرف كرد و اسم آن را به يقت‌ئيل تغيير داد كه تا به امروز به همان نام خوانده می‌شود.

8يک روز امصيا قاصدانی نزد يهوآش، پادشاه اسرائيل (پسر يهواخاز و نوهٔ ييهو) فرستاده، به او اعلام جنگ داد.

9اما يهوآش پادشاه با اين مثل جواب امصيا را داد: «روزی در لبنان يک بوتهٔ خار به درخت سرو آزاد گفت: ”دخترت را به پسر من به زنی بده.“ ولی درست در همين وقت حيوانی وحشی از آنجا عبور كرد و آن خار را پايمال نمود! 10تو ادوم را نابود كرده‌ای و مغرور شده‌ای؛ ولی به اين پيروزيت قانع باش و پا را از گليمت بيرون نگذار. چرا می‌خواهی كاری كنی كه به زيان تو و قومت تمام شود؟»

11ولی امصيا توجهی ننمود، پس يهوآش، پادشاه اسرائيل، سپاه خود را آمادهٔ جنگ كرد. جنگ در بيت‌شمس، يكی از شهرهای يهودا، درگرفت. 12سپاه يهودا شكست خورد و سربازان به شهرهای خود فرار كردند. 13امصيای پادشاه اسير شد و سپاه اسرائيل بر اورشليم تاخت و حصار آن را از دروازهٔ افرايم تا دروازهٔ زاويه كه طولش در حدود دويست متر بود، در هم كوبيد. 14يهوآش عده‌ای را گروگان گرفت و تمام طلا و نقره و لوازم خانهٔ خداوند و كاخ سلطنتی را برداشت و به سامره بازگشت.

15شرح بقيهٔ رويدادهای دوران سلطنت يهوآش، جنگهای او با امصيا (پادشاه يهودا)، كارها و فتوحات او در كتاب «تاريخ پادشاهان اسرائيل» ثبت شده است. 16يهوآش مرد و در آرامگاه سلطنتی سامره دفن شد و پسرش يربعام دوم به جای او به سلطنت رسيد.

مرگ امصيا، پادشاه يهودا

(دوم تواريخ 25‏:25‏-28)

17امصيا بعد از مرگ يهوآش پانزده سال ديگر هم زندگی كرد. 18شرح بقيهٔ رويدادهای دوران سلطنت امصيا در كتاب «تاريخ پادشاهان يهودا» نوشته شده است. 19در اورشليم عليه او توطئه چيدند و او به لاكيش گريخت، ولی دشمنانش او را تعقيب كرده، در آنجا او را كشتند. 20سپس جنازه‌اش را روی اسب گذاشته، به اورشليم برگرداندند و در آرامگاه سلطنتی شهر داوود دفن كردند.

21مردم يهودا، پسرش عزيا را در سن شانزده سالگی به جای او پادشاه خود ساختند. 22عزيا بعد از مرگ پدرش شهر ايلت را برای يهودا پس گرفت و آن را بازسازی نمود.

يربعام دوم، پادشاه اسرائيل

23يربعام دوم (پسر يهوآش) در پانزدهمين سال سلطنت امصيا، پادشاه يهودا، پادشاه اسرائيل شد و چهل و يک سال در سامره سلطنت نمود. 24او نيز مانند يربعام اول (پسر نباط) نسبت به خداوند گناه ورزيد و اسرائيل را به گناه كشاند. 25يربعام دوم زمينهای از دست رفتهٔ اسرائيل را كه بين گذرگاه حمات در شمال و دريای مرده در جنوب واقع شده بود، پس گرفت؛ درست همانطور كه خداوند، خدای اسرائيل توسط يونس نبی (پسر امتای) اهل جت حافر پيشگويی فرموده بود.

26خداوند مصيبت تلخ اسرائيل را ديد؛ و كسی نبود كه به داد ايشان برسد. 27ولی خواست خداوند اين نبود كه نام اسرائيل را از روی زمين محو كند، پس توسط يربعام دوم ايشان را نجات داد.

28شرح بقيهٔ دوران سلطنت يربعام دوم، كارها و فتوحات و جنگهای او، و اينكه چطور دمشق و حمات را كه در تصرف يهودا بودند باز به دست آورد، همه در كتاب «تاريخ پادشاهان اسرائيل» نوشته شده است. 29وقتی يربعام دوم مرد، جنازهٔ او را در كنار ساير پادشاهان اسرائيل به خاک سپردند و پسرش زكريا بر تخت سلطنت اسرائيل نشست.