2 ሳሙኤል 3 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 3:1-39

1በዳዊት ቤትና በሳኦል ቤት መካከል የነበረው ጦርነት ብዙ ጊዜ ቈየ፤ ዳዊት እየበረታ ሲሄድ፣ የሳኦል ቤት ግን እየተዳከመ መጣ።

2ዳዊት በኬብሮን ሳለ፣ ስድስት ወንዶች ልጆች ተወለዱለት፤

የበኵር ልጁ፣ ከኢይዝራኤላዊቷ ከአኪናሆም የተወለደው አምኖን፣

3ሁለተኛው፣ የቀርሜሎሳዊው የናባል ሚስት ከነበረችው ከአቢግያ የተወለደው ኪልአብ፣

ሦስተኛው፣ ተልማይ ከተባለው ከጌሹር ንጉሥ ልጅ ከመዓካ የተወለደው አቤሴሎም፣

4አራተኛው፣ ከአጊት የተወለደው አዶንያስ፤

አምስተኛው፣ ከአቢጣል የተወለደው ሰፋጥያ፣

5ስድስተኛው፣ ከዳዊት ሚስት ከዔግላ የተወለደው ይትረኃም ነበር፤

እነዚህ ዳዊት በኬብሮን ሳለ የተወለዱለት ናቸው።

አበኔር ከዳዊት ጋር ተባበረ

6የሳኦል ቤትና የዳዊት ቤት በጦርነት ላይ በነበሩበት ጊዜ፣ አበኔር በሳኦል ቤት ላይ ኀይሉን ያጠናክር ነበር። 7ሳኦልም የኢዮሄልን ልጅ ሪጽፋን በቁባትነት አስቀምጧት ነበር፤ ኢያቡስቴም አበኔርን፣ “ለምንድን ነው ከአባቴ ቁባት ጋር የተኛኸው?” አለው።

8አበኔርም በኢያቡስቴ ንግግር እጅግ ስለ ተቈጣ እንዲህ አለ፤ “እኔ ለይሁዳ የምወግን የውሻ ጭንቅላት ነኝን? ለአባትህ ለሳኦል ቤት ለወንድሞቹና ለዘመዶቹ ታማኝነቴን እስከ ዛሬ ድረስ አላጓደልሁም፤ አንተንም አሳልፌ ለዳዊት አልሰጠሁም፤ አሁን ግን አንተ ከዚህች ሴት ጋር በፈጸምሁት ነገር ትከሰኛለህን? 9እግዚአብሔር ለዳዊት በመሐላ የሰጠውን ተስፋ እዳር እንዲደርስ ሳላደርግ ብቀር እግዚአብሔር በአበኔር ላይ ክፉ ያድርግበት፤ ከዚያ የባሰም ያምጣበት፤ 10የማለለትም መንግሥትን ከሳኦል ቤት አውጥቶ፣ ከዳን እስከ ቤርሳቤህ ባለው በእስራኤልና በይሁዳ ምድር ላይ የዳዊትን ዙፋን ለመመሥረት የሰጠው ተስፋ ነው።” 11ኢያቡስቴም አበኔርን አጥብቆ ፈርቶት ስለ ነበር፣ እንደ ገና አንዲት ቃል እንኳ ሊመልስለት አልደፈረም።

12ከዚያም አበኔር ለዳዊት፣ “ምድሪቱ የማን ናት? ከእኔ ጋር ተስማማ፤ እነሆ እስራኤል ሁሉ ወደ አንተ እንዲመለስ እኔ እረዳሃለሁ” ብለው ለዳዊት እንዲነግሩለት መልክተኞች ላከ።

13ዳዊትም፣ “ይሁን እሺ፣ ከአንተ ጋር ስምምነቱን አደርጋለሁ፤ ነገር ግን ከአንተ አንዲት ነገር እሻለሁ፤ ይኸውም ወደ እኔ ስትመጣ በመጀመሪያ የሳኦልን ሴት ልጅ ሜልኮልን ይዘህልኝ እንድትመጣ ነው፤ ያለዚያ ግን ወደ እኔ እንዳትመጣ” አለ። 14ከዚያም ዳዊት፣ “የመቶ ፍልስጥኤማውያን ሸለፈት ማጫ የከፈልሁባትን ሚስቴን ሜልኮልን ስጠኝ” ብሎ ወደ ሳኦል ልጅ ወደ ኢያቡስቴ መልክተኞች ላከበት።

15ስለዚህም ኢያቡስቴ መልክተኛ ልኮ፣ ሜልኮልን ከባሏ ከሌሳ ልጅ ከፈልጢኤል ወሰዳት። 16ባሏም እስከ ብራቂም ከተማ ድረስ እያለቀሰ ተከትሏት ሄደ፤ ከዚያም አበኔር፣ “በል ይበቃል! ወደ ቤትህ ተመለስ” አለው። ስለዚህም ተመለሰ።

17አበኔር ከእስራኤል ሽማግሌዎች ጋር ተመካከረ፤ እንዲህም አለ፤ “ባለፈው ጊዜ ዳዊት በላያችሁ እንዲነግሥ ፈልጋችሁ ነበር፤ 18እግዚአብሔር ለዳዊት፣ ‘በባሪያዬ በዳዊት ሕዝቤን እስራኤልን ከፍልስጥኤማውያን እጅና ከጠላቶቻቸው እጅ እታደጋቸዋለሁ’ ብሎ ተስፋ ስለ ሰጠው፣ ይህን አሁኑኑ አድርጉት።”

19እንዲሁም አበኔር ለብንያማውያን ራሱ ሄዶ ይህንኑ ነገራቸው፤ ከዚያም እስራኤልና መላው የብንያም ቤት ለማድረግ የፈለጉትን ሁሉ ለዳዊት ለመንገር ወደ ኬብሮን ሄደ። 20አበኔር ከሃያ ሰዎች ጋር ዳዊት ወዳለበት ወደ ኬብሮን መጣ፤ ዳዊትም ለአበኔርና አብረውት ለነበሩት ሰዎች ግብዣ አደረገላቸው። 21ከዚያም አበኔር ዳዊትን፤ “ከአንተ ጋር ቃል ኪዳን እንዲያደርጉ፣ ልብህ እንደተመኘውም ሁሉን እንድትገዛ ፈጥኜ ሄጄ፣ ለጌታዬ ለንጉሡ መላውን እስራኤልን ልሰብስብ” አለው። ስለዚህ ዳዊት አበኔርን አሰናበተው፤ በሰላምም ሄደ።

ኢዮአብ አበኔርን ገደለው

22የዳዊትና የኢዮአብ ሰዎች በዚያኑ ጊዜ ብዙ ምርኮ ይዘው ከዘመቻ ተመለሱ። አበኔር ግን ዳዊት በሰላም አሰናብቶት ስለ ሄደ፣ በኬብሮን አልነበረም። 23ኢዮአብና አብሮት የነበረው ሰራዊት ሁሉ እዚያ እንደ ደረሱ፣ የኔር ልጅ አበኔር ወደ ንጉሡ መምጣቱን፣ ንጉሡ እንዳሰናበተውና እርሱም በሰላም እንደ ሄደ፣ ኢዮአብ ሰማ።

24ስለዚህ ኢዮአብ ወደ ንጉሡ ገብቶ እንዲህ አለ፤ “ምን ማድረግህ ነው? እነሆ አበኔር መጥቶልህ እንዴት በሰላም እንዲሄድ አሰናበትኸው? 25የኔርን ልጅ አበኔርን ታውቀዋለህ፤ የመጣው ሊያታልልህ፣ መውጣት መግባትህን ለማወቅና የምታደርገውን ሁሉ ሊሰልል ነው።”

26ከዚያም ኢዮአብ ከዳዊት ዘንድ ወጣ፤ አበኔርን እንዲያመጡትም መልክተኞች ላከ፤ መልክተኞቹም ከሴይር የውሃ ጕድጓድ አጠገብ መለሱት። ዳዊት ግን ይህን አላወቀም ነበር። 27አበኔር ወደ ኬብሮን በተመለሰ ጊዜ፣ ኢዮአብ በቈይታ የሚያነጋግረው በመምሰል ዞር አድርጎ ወደ ቅጽሩ በር ይዞት ሄደ፤ እዚያም የወንድሙን የአሣሄልን ደም ለመበቀል ሲል፣ ሆዱ ላይ ወግቶ ገደለው።

28ዳዊት ይህን ነገር ቈይቶ በሰማ ጊዜ እንዲህ አለ፤ “እኔም ሆንሁ መንግሥቴ ከኔር ልጅ ከአበኔር ደም በእግዚአብሔር ፊት ለዘላለም ንጹሕ ነን፤ 29ደሙ በኢዮአብ ራስና በአባቱ ቤት ሁሉ ላይ ይሁን፤ ፈሳሽ ነገር የሚወጣው ወይም አሠቃቂ የቈዳ በሽታ3፥29 የዕብራይስጡ ቃል ማናቸውንም ዐይነት የቈዳ በሽታ የሚያመለክት ነው። ያለበት፣ በምርኵዝ የሚሄድ ዐንካሳ፣ ወይም በሰይፍ ተመትቶ የሚወድቅ ወይም የሚበላው ያጣ ራብተኛ ከኢዮአብ ቤት አይታጣ።”

30አበኔር ገባዖን ላይ በተደረገው ጦርነት የኢዮአብንና የአቢሳን ወንድም አሣሄልን ገድሎት ስለ ነበር፣ እነርሱም አበኔርን ገደሉት።

31ከዚያም ዳዊት ለኢዮአብና አብሮት ለነበረው ሕዝብ ሁሉ፣ “ልብሳችሁን ቀድዳችሁ፣ ማቅ ለብሳችሁ በአበኔር ፊት አልቅሱ” አላቸው፤ ራሱ ንጉሥ ዳዊትም አስከሬኑን አጀበ። 32ከዚያም አበኔርን በኬብሮን ቀበሩት፤ ንጉሡም በአበኔር መቃብር ላይ ጮኾ አለቀሰ፤ ሕዝቡም ሁሉ እንደዚሁ አለቀሱ።

33ንጉሡም ለአበኔር ይህን የሐዘን እንጕርጕሮ ተቀኘ፤

“አበኔር እንደ ተራ ሰው ይሙት?

34እጆችህ አልታሰሩም፤

እግሮችህ በእግር ብረት አልገቡም፤

ሰው በክፉ ሰዎች ፊት እንደሚወድቅ

አንተም እንደዚሁ ወደቅህ።”

ሕዝቡም ሁሉ እንደ ገና አለቀሱለት።

35ከዚያም ሕዝቡ ሁሉ እህል በሚቀምስበት ሰዓት ወደ ዳዊት መጥተው ምግብ እንዲበላ አጥብቀው ለመኑት። ዳዊት ግን፣ “ፀሓይ ከመጥለቋ በፊት እንጀራ ወይም ሌላ ነገር ብቀምስ፣ እግዚአብሔር ይህን ያድርግብኝ፤ ከዚህም የባሰ ያምጣብኝ” ብሎ ማለ።

36ሕዝቡም ሁሉ ይህንኑ ተመለከቱ፤ ደስም አላቸው፤ በርግጥ ንጉሡ ያደረገው ሁሉ ሕዝቡን ደስ አሰኛቸው። 37እንዲሁም በዚያን ዕለት ሕዝቡ ሁሉና እስራኤል በሙሉ ንጉሡ በኔር ልጅ በአበኔር ሞት እጁ እንዳልገባበት ዐወቁ። 38ከዚያም ንጉሡ ለራሱ ሰዎች እንዲህ አለ፤ “በዛሬዪቱ ዕለት በእስራኤል መስፍንና ታላቅ ሰው መውደቁን አላወቃችሁምን? 39ምንም እንኳ ዛሬ የተቀባሁ ንጉሥ ብሆንም፣ እኔ ደካማ ሰው ነኝ፤ እነዚህ የጽሩያ ልጆች እጅግ በርትተውብኛል። እግዚአብሔር ለክፉ አድራጊ የእጁን ይስጠው።”

Thai New Contemporary Bible

2ซามูเอล 3:1-39

1การสู้รบระหว่างฝ่ายวงศ์วานของซาอูลกับฝ่ายดาวิดยืดเยื้อเป็นเวลานาน ดาวิดทรงเข้มแข็งขึ้นทุกทีๆ ในขณะที่ฝ่ายวงศ์วานของซาอูลเริ่มอ่อนแอลงเรื่อยๆ

2ราชโอรสของดาวิดที่ประสูติในเมืองเฮโบรน ได้แก่ อัมโนนราชโอรสหัวปี ประสูติจากนางอาหิโนอัมแห่งยิสเรเอล

3องค์ที่สองคือ คิเลอาบบุตรนางอาบีกายิลภรรยาม่ายของนาบาลแห่งคารเมล

องค์ที่สามคือ อับซาโลมบุตรนางมาอาคาห์ราชธิดาของกษัตริย์ทัลมัยแห่งเกชูร์

4องค์ที่สี่คือ อาโดนียาห์บุตรนางฮักกีท

องค์ที่ห้าคือ เชฟาทิยาห์บุตรนางอาบีตัล

5และองค์ที่หกคือ อิทเรอัมบุตรนางเอกลาห์

ราชโอรสเหล่านี้ของดาวิดประสูติที่เมืองเฮโบรน

อับเนอร์มาอยู่ฝ่ายดาวิด

6ขณะที่การสู้รบระหว่างฝ่ายวงศ์วานของซาอูลกับฝ่ายดาวิดดำเนินไป อับเนอร์ก็ขยายอิทธิพลมากขึ้นเรื่อยๆ ในฝ่ายวงศ์วานของซาอูล

7ซาอูลมีสนมคนหนึ่งชื่อริสปาห์บุตรสาวของอัยยาห์ และอิชโบเชทตรัสถามอับเนอร์ว่า “เหตุใดท่านจึงหลับนอนกับสนมของเสด็จพ่อ?”

8คำพูดนี้ทำให้อับเนอร์โกรธจัดจึงตอบว่า “ข้าพระบาทเป็นสุนัขรับใช้ยูดาห์หรือ? ข้าพระบาทยังคงจงรักภักดีต่อซาอูลราชบิดาของฝ่าพระบาท และราชวงศ์กับพระสหายมาจนถึงบัดนี้ ข้าพระบาทไม่ได้มอบฝ่าพระบาทให้กับดาวิด แต่บัดนี้ฝ่าพระบาททรงกล่าวหาข้าพระบาทด้วยเรื่องผู้หญิงคนนี้! 9ขอพระเจ้าทรงจัดการกับข้าพระบาทอย่างสาหัส หากข้าพระบาทไม่ช่วยดาวิดให้ลุล่วงตามพระสัญญาที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงปฏิญาณไว้กับเขา 10และย้ายอาณาจักรจากราชวงศ์ซาอูล มาสถาปนาราชบัลลังก์ดาวิดขึ้นเหนืออิสราเอลและยูดาห์ จากดานจดเบเออร์เชบา” 11อิชโบเชททรงไม่กล้าโต้ตอบประการใดเพราะกลัวอับเนอร์

12แล้วอับเนอร์ส่งตัวแทนไปทูลดาวิดว่า “แผ่นดินนี้เป็นของใคร? หากทรงทำข้อตกลงกับข้าพระบาท ข้าพระบาทก็จะช่วยนำอิสราเอลทั้งหมดมาสวามิภักดิ์ต่อฝ่าพระบาท”

13ดาวิดตรัสว่า “ดี เราจะทำข้อตกลงกับท่าน แต่มีข้อแม้ว่าท่านต้องนำตัวมีคาลราชธิดาของซาอูลมาด้วยเมื่อท่านมาพบเรา” 14แล้วดาวิดจึงทรงใช้ผู้สื่อสารไปทูลเรียกร้องกับอิชโบเชทราชโอรสของซาอูลว่า “จงคืนตัวมีคาลมเหสีของเรา ซึ่งเราได้ใช้หนังปลายองคชาติของชาวฟีลิสเตียร้อยคนสู่ขอนางมา”

15อิชโบเชทจึงตรัสสั่งให้ชิงตัวมีคาลจากสามีของนางคือปัลทีเอลบุตรลาอิช 16ปัลทีเอลเดินตามนางมาจนถึงบาฮูริมและร้องไห้มาตลอดทาง อับเนอร์จึงกล่าวแก่เขาว่า “กลับบ้านไป!” เขาก็กลับ

17อับเนอร์เกลี้ยกล่อมบรรดาผู้อาวุโสของอิสราเอลว่า “พวกท่านก็อยากให้ดาวิดเป็นกษัตริย์มาตั้งนานแล้ว 18ก็จงทำเดี๋ยวนี้! เพราะองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงสัญญากับดาวิดไว้ว่า ‘ดาวิดนี่แหละคือผู้ที่เราจะใช้ให้กอบกู้ประชากรอิสราเอลของเราจากมือชาวฟีลิสเตียและจากศัตรูทั้งปวง’ ”

19อับเนอร์ยังได้พูดกับชนตระกูลเบนยามินด้วย แล้วเขาก็เดินทางมายังเมืองเฮโบรนเพื่อทูลทุกสิ่งทุกอย่างที่อิสราเอลและตระกูลเบนยามินต้องการจะทำแก่ดาวิด 20เมื่ออับเนอร์พร้อมคนยี่สิบคนมาเข้าเฝ้าดาวิดที่เมืองเฮโบรน ดาวิดทรงจัดงานเลี้ยงให้เขาเหล่านั้น 21อับเนอร์จึงทูลดาวิดว่า “ข้าพระบาทจะไปรวบรวมอิสราเอลทั้งหมดมาเพื่อฝ่าพระบาท พวกเขาจะได้ถวายสัตยาบัน และฝ่าพระบาทจะได้ทรงปกครองทุกคนตามชอบพระทัย” ดาวิดจึงทรงส่งอับเนอร์กลับไปโดยสวัสดิภาพ

โยอาบสังหารอับเนอร์

22ขณะนั้นโยอาบและคนของดาวิดเพิ่งกลับจากการปล้น และนำข้าวของมากมายที่ริบได้กลับมาด้วย แต่อับเนอร์ไม่ได้อยู่กับดาวิดที่เมืองเฮโบรนแล้วเพราะดาวิดทรงส่งเขากลับไปอย่างสันติ 23เมื่อโยอาบและทหารทั้งหมดที่อยู่กับเขามาถึง โยอาบก็รู้ว่าอับเนอร์บุตรเนอร์เพิ่งมาเข้าเฝ้ากษัตริย์แล้วถูกส่งกลับไปอย่างสันติ

24โยอาบก็เข้าเฝ้าดาวิดและทูลว่า “เหตุใดฝ่าพระบาททรงทำอย่างนี้? ดูเถิด อับเนอร์มาถึงแล้ว แต่ทรงปล่อยเขาไปได้อย่างไร? ตอนนี้เขาก็ไปแล้ว! 25ฝ่าพระบาทก็ทรงทราบอยู่แล้วว่าเขามาสืบดูลาดเลาเพื่อจะวางแผนและกลับมาเล่นงานเรา”

26โยอาบจึงทูลลาแล้วส่งคนตามอับเนอร์ไปทันที่บ่อสีราห์ อับเนอร์ก็กลับมาพร้อมกับพวกนั้นแต่ดาวิดไม่ทรงทราบเรื่องนี้ 27เมื่ออับเนอร์มาถึงเมืองเฮโบรน โยอาบดึงตัวเขามาข้างประตูเมือง ทำเหมือนมีเรื่องจะคุยเป็นการส่วนตัว แต่แล้วโยอาบก็แทงท้องอับเนอร์ตาย เป็นการแก้แค้นแทนอาสาเฮลน้องชายของตน

28เมื่อดาวิดทรงทราบเรื่องจึงตรัสว่า “ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้า เรากับอาณาจักรของเราไม่ได้มีส่วนเกี่ยวข้องใดๆ กับการตายของอับเนอร์บุตรเนอร์ 29ขอให้ความผิดครั้งนี้ตกแก่โยอาบและวงศ์ตระกูลของเขา! ขอให้วงศ์ตระกูลของเขามีคนที่เป็นแผลพุพองหรือโรคเรื้อน3:29 คำภาษาฮีบรูอาจหมายถึงโรคผิวหนังต่างๆ ไม่จำเป็นต้องหมายถึงโรคเรื้อนเท่านั้น พิกลพิการ ตายด้วยความอดอยาก หรือล้มตายด้วยสงครามเสมอ”

30(โยอาบและอาบีชัยน้องชายของเขาได้สังหารอับเนอร์เพราะเขาได้ฆ่าอาสาเฮลน้องชายของพวกเขาในการต่อสู้ที่กิเบโอน)

31ดาวิดตรัสกับโยอาบและพรรคพวกที่อยู่ด้วยว่า “จงฉีกเสี้อผ้า สวมชุดผ้ากระสอบ และไว้ทุกข์ให้อับเนอร์” กษัตริย์ดาวิดเองทรงติดตามขบวนแห่ศพไปยังสุสาน 32ศพของอับเนอร์ถูกฝังไว้ที่เมืองเฮโบรน กษัตริย์ทรงร่ำไห้เสียงดังตรงที่ฝังศพ ประชากรทั้งปวงก็ร่ำไห้ด้วย

33ดาวิดทรงขับร้องบทคร่ำครวญสำหรับอับเนอร์ว่า

“ควรหรือที่อับเนอร์ต้องมาตายเยี่ยงคนเถื่อน?

34มือของท่านไม่ได้ถูกมัด

เท้าของท่านไม่ได้ถูกจองจำ

ท่านล้มลงดั่งผู้ที่ล้มต่อหน้าคนชั่ว”

ประชากรทั้งปวงก็ร่ำไห้ให้กับอับเนอร์อีกครั้ง

35แล้วพวกเขามาทูลดาวิดให้ทรงยอมเสวยพระกระยาหารบ้างขณะที่ยังกลางวันอยู่ แต่ดาวิดตรัสสาบานว่า “ขอพระเจ้าทรงจัดการกับเราอย่างหนัก หากเรากินขนมปังหรือสิ่งอื่นใดก่อนดวงอาทิตย์ลับฟ้า!”

36การทำเช่นนี้เป็นที่ชื่นชอบแก่ประชาชนอย่างยิ่ง อันที่จริงพวกเขาชื่นชอบทั้งนั้นไม่ว่ากษัตริย์จะทำสิ่งใด 37ในวันนั้นประชาชนทั้งหมดและชนอิสราเอลทั้งปวงจึงทราบว่าดาวิดไม่ได้มีส่วนเกี่ยวข้องใดๆ กับการสังหารอับเนอร์บุตรเนอร์เลย

38แล้วกษัตริย์ดาวิดตรัสกับคนของพระองค์ว่า “ท่านรู้หรือไม่ว่าในวันนี้คนสำคัญและผู้นำที่ยิ่งใหญ่คนหนึ่งได้สิ้นชีพแล้วในอิสราเอล? 39และวันนี้ถึงแม้เราจะเป็นกษัตริย์ที่พระเจ้าทรงเจิมตั้งไว้ เราก็อ่อนแอ และบุตรทั้งสองของนางเศรุยาห์นี้ก็แข็งแกร่งเกินไปสำหรับเรา ขอองค์พระผู้เป็นเจ้าทรงตอบสนองคนชั่วที่ได้ทำการชั่วเถิด!”