2 ሳሙኤል 4 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 4:1-12

ኢያቡስቴ ተገደለ

1አበኔር በኬብሮን መሞቱን የሳኦል ልጅ ኢያቡስቴ በሰማ ጊዜ ወኔ ከዳው፤ መላው እስራኤልም ደነገጠ። 2በዚህ ጊዜ የሳኦል ልጅ ኢያቡስቴ የወራሪ ጭፍራ ቡድን መሪዎች የሆኑ ሁለት ሰዎች ነበሩት፤ አንዱ በዓና ሌላው ደግሞ ሬካብ ይባሉ ነበር። እነርሱም ከብንያም ነገድ የብኤሮት ተወላጅ የሆነው የሬሞን ልጆች ነበሩ፤ ብኤሮት ከብንያም ክፍል እንደ አንዱ ትቈጠራለች። 3የብኤሮት ሕዝብ ወደ ጌቴም በመሸሽ እስከ ዛሬም በመጻተኝነት እዚያው ይኖራልና።

4የሳኦል ልጅ ዮናታን ሁለት እግሮቹ ሽባ የሆኑ አንድ ልጅ ነበረው። እርሱም የሳኦልና የዮናታን አሟሟት ወሬ ከኢይዝራኤል በመጣ ጊዜ የአምስት ዓመት ልጅ ነበረ። ሽባ የሆነውንም በዚህ ጊዜ ሞግዚቱ አንሥታው በጥድፊያ ስትሸሽ በመውደቁ ነው። ስሙም ሜምፊቦስቴ ይባል ነበር።

5በዚህ ጊዜ የብኤሮታዊው የሬሞን ልጆች ሬካብና በዓና ወደ ኢያቡስቴ ቤት ለመሄድ ዐልጋው ላይ ተኝቶ ሳለ፣ ሙቀት ሲሆን እኩለ ቀን ላይ ደረሱ፤ 6ስንዴ እንደሚፈልግም ሰው ሆነው ወደ ቤቱ ውስጥ ዘልቀው በመግባት ሆዱ ላይ ወጉት። ከዚያም ሬካብና ወንድሙ በዓና ሹልክ ብለው ወጡ።

7ወደ ቤቱ ውስጥ የገቡት ኢያቡስቴ በመኝታ ክፍሉ ውስጥ ተኝቶ ሳለ ነበር፤ ወግተው ከገደሉትም በኋላ ራሱን ቈርጠው በመውሰድ፣ ሌሊቱን ሁሉ በዓረባ መንገድ ተጓዙ። 8የኢያቡስቴንም ራስ ወደ ኬብሮን ዳዊት ዘንድ አምጥተው ንጉሡን፣ “አንተን ሊገድል ይፈልግ የነበረው የጠላትህ የሳኦል ልጅ የኢያቡስቴ ራስ ይኸውልህ፤ እነሆ እግዚአብሔር በዛሬው ቀን ስለ ጌታዬ ስለ ንጉሡ ሳኦልንና ዘሩን ተበቅሏል” አሉት።

9ዳዊትም ለብኤሮታዊው ለሬሞን ልጆች ለሬካብና ለወንድሙ ለበዓና እንዲህ ሲል መለሰላቸው፤ “ከመከራ ሁሉ ያዳነኝ ሕያው እግዚአብሔርን10የምሥራች ያመጣልኝ መስሎት፣ ‘እነሆ ሳኦል ሞተ’ ብሎ የነገረኝን ሰው ይዤ ጺቅላግ ላይ ገደልሁት፤ እንግዲህ ለዚያ ሰው ስላመጣው ምሥራች የሸለምሁት ይህን ነበር። 11ታዲያ በገዛ ቤቱ፣ በገዛ ዐልጋው ላይ ዐርፎ የተኛውን ንጹሕ ሰው የገደሉትን ክፉ ሰዎች እንዴት የባሰ ቅጣት አይገባቸውም? ደሙን ከእጃችሁ መፈለግ፣ እናንተን ከምድሪቱ ማጥፋት የለብኝምን?”

12ስለዚህም ዳዊት የራሱን ሰዎች አዘዘ፤ እነርሱንም ገደሏቸው፤ እጅና እግራቸውንም ቈርጠው በኬብሮን ካለው ኵሬ አጠገብ ሰቀሏቸው። ነገር ግን የኢያቡስቴን ራስ ወስደው ኬብሮን በሚገኘው በአበኔር መቃብር አጠገብ ቀበሩት።

Thai New Contemporary Bible

2ซามูเอล 4:1-12

อิชโบเชทถูกปลงพระชนม์

1เมื่ออิชโบเชทราชโอรสของซาอูลทรงทราบว่าอับเนอร์เสียชีวิตที่เมืองเฮโบรนก็ทรงหวาดหวั่น และชาวอิสราเอลทั้งปวงก็ตื่นตกใจ 2อิชโบเชทมีหัวหน้ากองโจรสองคน คือบาอานาห์และเรคาบ ทั้งสองเป็นบุตรของริมโมนเผ่าเบนยามินแห่งเมืองเบเอโรท ซึ่งถือว่าเป็นส่วนหนึ่งของเบนยามิน 3เพราะชาวเบเอโรทหนีไปอาศัยอยู่ที่เมืองกิททาอิมในฐานะคนต่างถิ่นตราบจนทุกวันนี้

4(โยนาธานราชโอรสของซาอูลมีบุตรชายคนหนึ่งซึ่งขาพิการทั้งสองข้าง เพราะขณะที่เด็กนั้นอายุห้าขวบ มีคนนำข่าวซาอูลกับโยนาธานจากยิสเรเอลมาแจ้ง พี่เลี้ยงจึงอุ้มขึ้นและพาหนี แต่ด้วยความรีบเด็กนั้นจึงตกลงมาและเป็นง่อย เขาชื่อว่า เมฟีโบเชท)

5ฝ่ายเรคาบและบาอานาห์ บุตรของริมโมนชาวเมืองเบเอโรทออกเดินทางมายังตำหนักของอิชโบเชทและมาถึงในเวลาใกล้เที่ยง ขณะอิชโบเชทกำลังบรรทมพักเที่ยง 6ทั้งสองเข้าไปยังส่วนในของตำหนักและทำทีว่าจะเข้าไปเอาข้าวสาลี แล้วพวกเขาก็แทงที่ท้องของอิชโบเชท จากนั้นเรคาบกับบาอานาห์ก็หนีไป

7ทั้งสองเข้าไปในตำหนักขณะอิชโบเชทบรรทมอยู่บนพระแท่นในห้องบรรทม หลังจากพวกเขาจ้วงแทงและปลงพระชนม์แล้ว ก็ตัดพระเศียรและหิ้วหนีมาตลอดคืนตามเส้นทางอาราบาห์ 8เขานำพระเศียรอิชโบเชทมาเข้าเฝ้าดาวิดที่เมืองเฮโบรน และกราบทูลว่า “นี่คือศีรษะของอิชโบเชทราชโอรสของซาอูล ศัตรูผู้พยายามตามฆ่าฝ่าพระบาท วันนี้องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงแก้แค้นต่อซาอูลและลูกหลานของเขาเพื่อฝ่าพระบาทแล้ว”

9ดาวิดตรัสตอบเรคาบและบาอานาห์สองพี่น้องซึ่งเป็นบุตรของริมโมนชาวเมืองเบเอโรทว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าผู้ทรงกอบกู้เราพ้นจากความทุกข์ร้อนทั้งปวงนั้นทรงพระชนม์อยู่แน่ฉันใด 10เมื่อมีคนมาบอกเราว่า ‘กษัตริย์ซาอูลสิ้นพระชนม์แล้ว’ โดยหลงคิดว่าเอาข่าวดีมาบอกเรา เราก็ได้จับฆ่าในศิกลากฉันนั้น นั่นเป็นบำเหน็จที่เราให้สำหรับข่าวของเขา 11ยิ่งกว่านั้นสักเท่าใดเราจะตอบแทนอย่างสาสมกับคนสารเลวที่ลอบฆ่าคนบริสุทธิ์ถึงในบ้านทั้งๆ ที่เขายังหลับอยู่บนเตียง เราไม่ควรเอาชีวิตเจ้ามาทดแทนและกำจัดเจ้าออกจากแผ่นดินหรือ!”

12แล้วดาวิดจึงตรัสสั่งทหารให้ฆ่าเรคาบกับบาอานาห์ ตัดมือและเท้าของคนทั้งสองออกมา เอาร่างแขวนไว้ข้างสระในเมืองเฮโบรน แต่พวกเขาก็นำพระเศียรของอิชโบเชทไปฝังไว้ในอุโมงค์ฝังศพของอับเนอร์ที่เมืองเฮโบรน