1 ዮሐንስ 5 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ዮሐንስ 5:1-21

በእግዚአብሔር ልጅ ማመን

1ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ እንደ ሆነ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዷል፤ አባትንም የሚወድድ ሁሉ ልጁንም እንደዚሁ ይወድዳል። 2እግዚአብሔርን ስንወድድና ትእዛዞቹን ስንፈጽም የእግዚአብሔርን ልጆች እንደምንወድድ በዚህ እናውቃለን፤ 3እግዚአብሔርን መውደድ ትእዛዞቹን መፈጸም ነውና። ትእዛዞቹም ከባድ አይደሉም፤ 4ምክንያቱም ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋል። ዓለምን የሚያሸንፈውም እምነታችን ነው። 5ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በስተቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማነው?

6በውሃና በደም የመጣው ይህ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ በውሃና በደም እንጂ በውሃ ብቻ አልመጣም። የሚመሰክረውም መንፈስ ነው፤ መንፈስ እውነት ነውና። 7ስለዚህ ሦስት ምስክሮች አሉት፤ 8እነርሱም5፥7-8 ጥንታዊ ባልሆነው በቩልጌት ቅጅ ላይ በሰማይ የሚመሰክሩት ሦስቱ ናቸው፤ እነርሱም አባት፣ ቃልና መንፈስ ቅዱስ ናቸው ይላል። 8 በምድር የሚመሰክሩት ሦስቱ ናቸው – ሆኖም ይህ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት በነበሩት የግሪክ ቅጆች ውስጥ አይገኝም። መንፈሱ፣ ውሃውና ደሙ ናቸው፤ ሦስቱም ይስማማሉ። 9የሰውን ምስክርነት ከተቀበልን፣ የእግዚአብሔር ምስክርነት ከዚያም ይልቃል፤ ይህ ስለ ልጁ የሰጠው የእግዚአብሔር ምስክርነት ነውና። 10በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን ሁሉ በልቡ ምስክር አለው፤ ማንም እግዚአብሔርን የማያምን ሁሉ እግዚአብሔር ስለ ልጁ የሰጠውን ምስክርነት ስላላመነ ሐሰተኛ አድርጎታል። 11ምስክርነቱም ይህ ነው፤ እግዚአብሔር የዘላለምን ሕይወት ሰጠን፤ ይህም ሕይወት ያለው በልጁ ነው። 12ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም።

ማጠቃለያ ሐሳብ

13በእግዚአብሔር ልጅ ስም የምታምኑ እናንተ፣ የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ ይህን እጽፍላችኋለሁ፤ 14በእግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ ማንኛውንም ነገር እንደ ፈቃዱ ብንለምን እርሱ ይሰማናል። 15የምንለምነውን ሁሉ እንደሚሰማን ካወቅን፣ የለመንነውንም ነገር እንደ ተቀበልን እናውቃለን።

16ማንም ሰው ወንድሙ ለሞት የማያበቃ ኀጢአት ሲያደርግ ቢያየው ይጸልይ፤ እግዚአብሔርም ለሞት የማያበቃ ኀጢአት ላደረጉት ሕይወትን ይሰጣል። ለሞት የሚያበቃም ኀጢአት አለ፤ ስለዚህኛው ግን ይጸልይ አልልም። 17ዐመፅ ሁሉ ኀጢአት ነው፤ ለሞት የማያበቃም ኀጢአት አለ። 18ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኀጢአት እንደማያደርግ፣ ነገር ግን የእግዚአብሔር ልጅ እንደሚጠብቀው፣ ክፉውም እንደማይነካው እናውቃለን። 19እኛ ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን፣ መላው ዓለምም በክፉው ሥር እንደ ሆነ እናውቃለን።

20የእግዚአብሔር ልጅ እንደ መጣ፣ እውነተኛ የሆነውን እርሱን እንድናውቅ ማስተዋልን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እኛም እውነተኛ በሆነው በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ አለን። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው።

21ልጆች ሆይ፤ ራሳችሁን ከጣዖቶች ጠብቁ።

Thai New Contemporary Bible

1ยอห์น 5:1-21

ความเชื่อในพระบุตรของพระเจ้า

1ทุกคนที่เชื่อว่าพระเยซูคือพระคริสต์ก็บังเกิดจากพระเจ้า และทุกคนที่รักบิดาย่อมรักบุตรของเขาด้วย 2เช่นนี้แหละเราจึงรู้ว่าเรารักคนทั้งหลายที่เป็นบุตรของพระเจ้า คือโดยการรักพระเจ้าและทำตามพระบัญชาของพระองค์ 3การรักพระเจ้าคือการเชื่อฟังพระบัญชาของพระเจ้า และพระบัญชาของพระองค์ก็ไม่เหลือบ่ากว่าแรง 4เพราะทุกคนที่เกิดจากพระเจ้าย่อมชนะโลก และความเชื่อของเรานี่แหละคือชัยชนะที่พิชิตโลก 5ใครเล่าชนะโลก? ก็มีแต่ผู้ที่เชื่อว่าพระเยซูเป็นพระบุตรของพระเจ้าเท่านั้น

6พระเยซูคริสต์คือผู้ที่เสด็จมาโดยน้ำและพระโลหิต พระองค์ไม่ได้เสด็จมาโดยน้ำเพียงอย่างเดียว แต่โดยน้ำและพระโลหิต และพระวิญญาณทรงเป็นพยานให้เพราะพระวิญญาณทรงเป็นความจริง 7เพราะมีสามสิ่งที่เป็นพยานคือ 8พระวิญญาณ น้ำ และพระโลหิต และทั้งสามนี้สอดคล้องกัน 9ถ้าเรารับคำพยานของมนุษย์ คำพยานของพระเจ้าย่อมยิ่งใหญ่กว่าเพราะเป็นคำพยานจากพระเจ้าเกี่ยวกับพระบุตรของพระองค์ 10ผู้ที่เชื่อในพระบุตรของพระเจ้าก็มีคำพยานนี้อยู่ในใจ ผู้ที่ไม่เชื่อก็หาว่าพระเจ้ามุสาเพราะไม่เชื่อคำพยานที่พระเจ้าให้เกี่ยวกับพระบุตรของพระองค์ 11คำพยานนี้ก็คือพระเจ้าประทานชีวิตนิรันดร์แก่เรา และชีวิตนี้อยู่ในพระบุตรของพระองค์ 12ผู้ที่มีพระบุตรก็มีชีวิต ผู้ที่ไม่มีพระบุตรของพระองค์ก็ไม่มีชีวิต

บทสรุป

13ข้าพเจ้าเขียนข้อความเหล่านี้มาถึงท่านทั้งหลายที่เชื่อในพระนามของพระบุตรของพระเจ้า เพื่อท่านจะรู้ว่าท่านมีชีวิตนิรันดร์ 14นี่คือความมั่นใจที่เรามีเมื่อเข้าเฝ้าพระเจ้า คือถ้าเราทูลขอสิ่งใดที่สอดคล้องกับพระประสงค์ของพระองค์ พระองค์ก็ทรงฟังเรา 15และถ้าเรารู้ว่าพระองค์ทรงฟังเรา เมื่อเราทูลขอสิ่งใดๆ เราก็รู้ว่าจะได้รับสิ่งที่เราทูลขอจากพระองค์

16ถ้าผู้ใดเห็นพี่น้องของตนทำบาปอย่างหนึ่งอย่างใดที่ไม่นำไปสู่ความตาย ผู้นั้นควรอธิษฐานขอ และพระเจ้าจะประทานชีวิตแก่ผู้ที่ทำบาป ข้าพเจ้าหมายถึงคนที่ทำบาปซึ่งไม่นำไปสู่ความตาย บาปที่นำไปสู่ความตายก็มี ข้าพเจ้าไม่ได้กล่าวว่าให้อธิษฐานขอสำหรับคนที่ทำบาปเช่นนั้น 17การอธรรมทั้งปวงล้วนเป็นบาป แต่บาปที่ไม่นำไปสู่ความตายก็มีอยู่

18เรารู้ว่าผู้ที่เกิดจากพระเจ้าไม่ทำบาปต่อไป แต่พระองค์ผู้บังเกิดจากพระเจ้าทรงคุ้มครองเขาไว้ให้ปลอดภัยและมารร้ายไม่อาจทำอันตรายเขา 19เรารู้ว่าเราเป็นบุตรของพระเจ้าและทั่วทั้งโลกอยู่ใต้การควบคุมของมารร้าย 20เรายังรู้ด้วยว่าพระบุตรของพระเจ้าได้เสด็จมาและได้ประทานความเข้าใจแก่เรา เพื่อเราจะรู้จักพระเจ้าที่แท้จริงและเราอยู่ในพระเจ้าที่แท้จริง คืออยู่ในพระเยซูคริสต์พระบุตรของพระองค์ พระองค์ทรงเป็นพระเจ้าแท้และเป็นชีวิตนิรันดร์

21ลูกที่รัก จงรักษาตนเองให้พ้นจากรูปเคารพเถิด