2 ዮሐንስ 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

2 ዮሐንስ 1:1-13

1ሽማግሌው፤

በእውነት ለምወድዳት፣ እኔ ብቻ ሳልሆን እውነትን የሚያውቁ ሁሉ ለሚወድዷት ለተመረጠችው እመቤትና ለልጆቿ፤ 2በውስጣችን ከሚኖርና ከእኛ ጋር ለዘላለም ከሚሆን እውነት የተነሣ፤

3ከእግዚአብሔር አብና የአብ ልጅ ከሆነው ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ፣ ምሕረትና ሰላም በእውነትና በፍቅር ከእኛ ጋር ይሆናል።

4ከልጆችሽ አንዳንዶቹ ከአብ በተሰጠን ትእዛዝ መሠረት በእውነት ጸንተው እየሄዱ በማግኘቴ እጅግ ደስ ብሎኛል። 5አሁንም እመቤት ሆይ፤ ከመጀመሪያ የነበረችውን እንጂ አዲስ ትእዛዝ አልጽፍልሽም፤ ይኸውም እርስ በርሳችን እንዋደድ ዘንድ ነው። 6ይህም ፍቅር፣ በትእዛዞቹ መሠረት እንመላለስ ዘንድ ነው። ትእዛዙም ከመጀመሪያ እንደ ሰማችሁት በፍቅር እንድትኖሩ ነው።

7ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የማያምኑ ብዙ አሳቾች ወደ ዓለም ወጥተዋል። እንዲህ ያለ ማንኛውም ሰው አታላይና የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው። 8እናንተም የደከማችሁበትን ዋጋ እንዳታጡ፣ ነገር ግን ሙሉ ሽልማት እንድትቀበሉ ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። 9በክርስቶስ ትምህርት የማይኖርና ከትምህርቱ የሚወጣ ሁሉ አምላክ የለውም፤ በክርስቶስ ትምህርት የሚኖር ግን አብም ወልድም አለው። 10ማንም ወደ እናንተ ቢመጣ፣ ይህንም ትምህርት ባያመጣ በቤታችሁ አትቀበሉት፤ ሰላምም አትበሉት፤ 11የሚቀበለው ሰው፣ የክፉ ሥራው ተባባሪ ይሆናልና።

12የምጽፍላችሁ ብዙ ነገር ነበረኝ፤ ይሁን እንጂ በወረቀትና በቀለም እንዲሆን አልፈልግም፤ ዳሩ ግን ደስታችን ፍጹም ይሆን ዘንድ ወደ እናንተ መጥቼ ፊት ለፊት ላነጋግራችሁ ተስፋ አደርጋለሁ።

13የተመረጠችው የእኅትሽ ልጆች ሰላምታ ያቀርቡልሻል።

Thai New Contemporary Bible

2ยอห์น 1:1-13

1จดหมายฉบับนี้จากข้าพเจ้าผู้อาวุโส1:1 หรือผู้ปกครอง

ถึงท่านสุภาพสตรีที่ทรงเลือกไว้กับบุตรทั้งหลายของท่าน ข้าพเจ้ารักพวกท่านทุกคนในความจริง และไม่ใช่เพียงข้าพเจ้าเท่านั้นแต่คนทั้งปวงที่รู้จักความจริงด้วย 2ข้าพเจ้ารักพวกท่านเพราะความจริงซึ่งอยู่ในเราทั้งหลายและซึ่งจะคงอยู่กับเราตลอดไป

3ขอพระคุณ พระเมตตา และสันติสุขจากพระเจ้าผู้เป็นพระบิดาและจากพระเยซูคริสต์ผู้เป็นพระบุตรของพระบิดาดำรงอยู่กับเราทั้งหลายในความจริงและในความรัก

4ข้าพเจ้าชื่นชมยินดียิ่งนักที่เห็นว่าบุตรของท่านบางคนดำเนินในความจริงเหมือนที่พระบิดาได้ทรงบัญชาเรา 5และบัดนี้ท่านสุภาพสตรีที่รัก ข้าพเจ้าไม่ได้เขียนถึงท่านเกี่ยวกับบัญญัติใหม่ แต่เป็นบัญญัติที่เรามีมาตั้งแต่แรกคือ ข้าพเจ้าขอให้เรารักซึ่งกันและกัน 6และความรักคือการที่เราดำเนินชีวิตตามบัญญัติของพระองค์ด้วยความเชื่อฟัง ตามที่ท่านได้ยินมาแล้วตั้งแต่ต้น บัญญัติของพระองค์นั้นคือให้ท่านดำเนินชีวิตในความรัก

7มีผู้ล่อลวงหลายคนเข้าไปในโลก คนเหล่านี้ไม่ยอมรับว่าพระเยซูคริสต์ทรงมาบังเกิดเป็นมนุษย์ คนเช่นนี้เป็นผู้ล่อลวงและเป็นปฏิปักษ์ของพระคริสต์ 8จงระวังไว้เถิดเพื่อท่านจะไม่สูญเสียสิ่งที่ท่านได้ทำไว้และเพื่อท่านจะได้รับรางวัลเต็มที่ 9ผู้ใดวิ่งล้ำหน้าไปและไม่ทำตามคำสั่งสอนของพระคริสต์ต่อไปก็ไม่มีพระเจ้า ส่วนผู้ที่ทำตามคำสั่งสอนต่อไปก็มีทั้งพระบิดาและพระบุตร 10ถ้าผู้ใดมาหาท่านโดยไม่นำคำสั่งสอนนี้มาด้วยก็อย่ารับเขาเข้าบ้านหรือต้อนรับเขา 11ผู้ที่ต้อนรับเขาก็ร่วมในกิจการชั่วของเขา

12ข้าพเจ้ามีหลายเรื่องจะเขียนถึงท่านแต่ไม่อยากใช้กระดาษและหมึก ข้าพเจ้าหวังจะมาพบปะพูดคุยกับท่านเองเพื่อความชื่นชมยินดีของเราจะเต็มบริบูรณ์

13พระเจ้าได้ทรงเลือกสรรน้องสาวของท่านไว้ บุตรทั้งหลายของนางฝากความคิดถึงมายังท่าน