1 ዜና መዋዕል 26 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 26:1-32

የቤተ መቅደሱ በር ጠባቂዎች

1የቤተ መቅደሱ በር ጠባቂዎች አመዳደብ፤

ከቆሬያውያን ወገን፤

ከአሳፍ ወንዶች ልጆች አንዱ የሆነው የቆሬ ወንድ ልጅ ሜሱላም። 2ሜሱላም ወንዶች ልጆች ነበሩት፤

የመጀመሪያው ዘካሪያስ፣

ሁለተኛው ይዲኤል፣

ሦስተኛው ዮዛባት፣

አራተኛው የትኒኤል፣

3አምስተኛው ኤላም፣

ስድስተኛው ይሆሐናን፣

ሰባተኛው ኤሊሆዔናይ።

4ዖቤድኤዶምም እንደዚሁ ወንዶች ልጆች ነበሩት፤

የመጀመሪያው ሸማያ፣

ሁለተኛው ዮዛባት፣

ሦስተኛው ኢዮአስ፣

አራተኛው ሣካር፣

አምስተኛው ናትናኤል፣

5ስድስተኛው ዓሚኤል፣

ሰባተኛው ይሳኮር፣

ስምንተኛው ፒላቲ፤

እግዚአብሔር ዖቤድኤዶምን ባርኮታልና።

6እንዲሁም ልጁ ሸማያ ወንዶች ልጆች ነበሩት፤ እነርሱም በቂ ችሎታ ስለ ነበራቸው የአባታቸው ቤት መሪዎች ሆነው ነበር። 7የሸማያ ወንዶች ልጆች፤

ዖትኒ፣ ራፋኤል፣ ዖቤድ፣ ኤልዛባድ፤

ዘመዶቹ ኤሊሁና ሰማክያም እንደዚሁ በቂ ችሎታ ነበራቸው።

8እነዚህ ሁሉ የዖቤድኤዶም ዘሮች ሲሆኑ፣ እነርሱም ሆኑ ወንዶች ልጆቻቸውና ቤተ ዘመዶቻቸው ሥራውን ለመሥራት በቂ ችሎታ ነበራቸው። የዖቤድኤዶም ዘሮች በአጠቃላይ ስድሳ ሁለት ነበሩ።

9ሜሱላም በቂ ችሎታ ያላቸው ወንዶች ልጆችና ቤተ ዘመዶች ነበሩት፤ ቍጥራቸውም በአጠቃላይ ዐሥራ ስምንት ነበረ።

10ከሜራሪ ወገን የሆነው ሖሳ ወንዶች ልጆች ነበሩት፤

የመጀመሪያው ሽምሪ ነበረ፤ የበኵር ልጅ ባይሆንም እንኳ፣ አባቱ ቀዳሚ አድርጎት ነበር።

11ሁለተኛው ኬልቅያስ፣ ሦስተኛው ጥበልያ፣ አራተኛው ዘካርያስ።

የሖሳ ወንዶች ልጆችና ቤተ ዘመዶቹ በአጠቃላይ ዐሥራ ሦስት ነበሩ።

12የቤተ መቅደሱም ጠባቂዎች በአለቆቻቸው ሥር ተመድበው ልክ እንደ ቤተ ዘመዶቻቸው ሁሉ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ሥራ ለማከናወን ምድብ ተራ ነበራቸው። 13ለእያንዳንዱም በር ወጣት ሽማግሌ ሳይባል ለሁሉም እኩል ዕጣ ተጣለ።

14የምሥራቁ በር ዕጣ ለሴሌምያ ወጣ።

ከዚያም ምክር ዐዋቂ ለሆነው ለልጁ ለዘካርያስ ዕጣ ጣሉ፤ እርሱም የሰሜኑ በር ደረሰው።

15የደቡቡ በር ዕጣ ለዖቤድኤዶም ሲወጣ፣ የግምጃ ቤቱ ዕጣ ደግሞ ለልጆቹ ወጣ።

16የምዕራቡ በርና በላይኛው መንገድ ላይ የሚገኘው የሸሌኬት በር ዕጣዎች ለሰፊንና ለሖሳ ወጣ።

በአንዱ ዘብ ጥበቃ ትይዩ ሌላ ዘብ ጥበቃ ነበረ፤

17በየቀኑም በምሥራቅ በኩል ስድስት፣

በሰሜን በኩል አራት፣

በደቡብ በኩል አራት፣

በዕቃ ቤቱ በኩል በአንድ ጊዜ ሁለት ሌዋውያን ይጠብቁ ነበር።

18በምዕራቡ በኩል የሚገኘውን አደባባይ ደግሞ በመንገዱ ላይ አራት፣ በአደባባዩ ላይ ደግሞ ሁለት ሆነው ይጠብቁ ነበር።

19እንግዲህ የቆሬና የሜራሪ ዘሮች የሆኑት በር ጠባቂዎች ድልድል ይህ ነበር።

የግምጃ ቤት ኀላፊዎችና ሌሎች ሹማምት

20ከሌዋውያን መካከል አኪያ የእግዚአብሔር ቤት ግምጃ ቤትና የተቀደሱት ዕቃዎች የሚቀመጡበት ግምጃ ቤት ኀላፊ ነበረ።

21የለአዳን ዘሮች፣ በለአዳን በኩል ጌድሶናውያን የሆኑትና ለጌድሶናዊው ለለአዳን ቤተ ሰቦች አለቆች የሆኑት የለአዳን ዘሮች እነዚህ ነበሩ፤ ይሒኤሊ፣ 22የይሒኤሊ ወንዶች ልጆች፣ ዜቶምና ወንድሙ ኢዩኤል። እነዚህም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ግምጃ ቤት ኀላፊዎች ነበሩ።

23ከእንበረማውያን፣ ከይስዓራውያን፣ ከኬብሮናውያን፣ ከዑዝኤላውያን፤

24የሙሴ ልጅ የጌርሳም ዘር የሆነው ሱባኤል የግምጃ ቤቱ የበላይ ኀላፊ ነበረ። 25በአልዓዛር በኩል የሚዛመዱት፤ ልጁ ረዓብያ፣ ልጁ የሻያ፣ ልጁ ኢዮራም፣ ልጁ ዝክሪ፣ ልጁ ሰሎሚት።

26ሰሎሚትና የሥጋ ዘመዶቹ ንጉሥ ዳዊት፣ የቤተ ሰቡ ኀላፊዎች፣ የሻለቆችና የመቶ አለቆች እንዲሁም ሌሎች የሰራዊቱ አዛዦች ቀድሰው ላቀረቧቸው ንዋያተ ቅድሳት ኀላፊዎች ነበሩ። 27በጦርነት ከተገኘውም ምርኮ ከፊሉን ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ማደሻ እንዲሆን ቀደሱት። 28ባለ ራእዩ ሳሙኤል፣ የቂስ ልጅ ሳኦል፣ የኔር ልጅ አበኔር፣ የጽሩያ ልጅ ኢዮአብ የቀደሱትን ሁሉና እንዲሁም ሌሎቹን ንዋያተ ቅድሳት ሰሎሚናትና ቤተ ዘመዶቹ ይጠብቁ ነበር።

29ከይስዓራውያን፤

ከናንያና ወንዶች ልጆቹ ከቤተ መቅደሱ ውጭ ባለው ሥራ በእስራኤል ላይ ሹማምትና ዳኞች ሆነው ተመደቡ።

30ከኬብሮናውያን፤

ለሐሻብያ፣ ጠንካራና ጐበዝ የሆኑ አንድ ሺሕ ሰባት መቶ ሰዎች ከዮርዳኖስ በስተ ምዕራብ በሚገኘው የእስራኤል ምድር ላለው የእግዚአብሔር ሥራና ለንጉሡም አገልግሎት ኀላፊዎች ሆነው ተመደቡ። 31በኬብሮናውያን በኩል በቤተ ሰቦቻቸው የትውልድ መዝገብ መሠረት ይሪያ አለቃቸው ነበረ።

በዳዊት ዘመነ መንግሥት በአርባኛው ዓመት መዛግብቱ ተመርምረው ስለ ነበር፣ በገለዓድ ውስጥ ኢያዜር በተባለ ቦታ ከኬብሮናውያን መካከል ጠንካራ ሰዎች ሊገኙ ችለዋል። 32ይሪያም ጠንካሮችና የቤተ ሰባቸው አለቆች የሆኑ ሁለት ሺሕ ሰባት መቶ ሥጋ ዘመዶች ነበሩት። ንጉሥ ዳዊትም እነዚህን የእግዚአብሔር ለሆነውና የንጉሡም በሆነው ጕዳይ ላይ ሮቤልን፣ ጋድንና የምናሴን ነገድ እኩሌታ ኀላፊ አድርጎ ሾማቸው።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

歷代志上 26:1-32

聖殿的守衛

1以下是殿門守衛的班次:

可拉亞薩的後代有可利的兒子米施利米雅2米施利米雅的長子是撒迦利亞,次子是耶疊,三子是西巴第雅,四子是耶提聶3五子是以攔,六子是約哈難,七子是以利約乃4俄別·以東的長子是示瑪雅,次子是約薩拔,三子是約亞,四子是沙甲,五子是拿坦業5六子是亞米利,七子是以薩迦,八子是毗烏利太。上帝特別賜福俄別·以東6他兒子示瑪雅有幾個兒子都很能幹,在各自的家族中做首領。 7他們是俄得尼利法益俄備得以利薩巴。他們的親族以利戶西瑪迦也很能幹。 8這些都是俄別·以東的子孫,他們和他們的兒子及親族共有六十二人,都是能幹稱職的人。 9米施利米雅的兒子及親族共十八人,都很能幹。 10米拉利的後代何薩的長子是申利,他本來不是長子,是被他父親立為長子的。 11次子是希勒迦,三子是底巴利雅,四子是撒迦利亞何薩的兒子及親族共十三人。

12這些按族長分成小組的殿門守衛在耶和華的殿裡按班次供職,與他們的親族一樣。 13他們無論大小,都按照族系抽籤,以決定看守哪個門。 14示利米雅抽中東門,他兒子撒迦利亞是個精明的謀士,抽中北門。 15俄別·以東抽中南門,他兒子抽中庫房。 16書聘何薩抽中西門和上行之路的沙利基門,兩班相對而立。 17每天有六個利未人守東門,四人守北門,四人守南門,守庫房的二人一組。 18守衛西面街道的有四人,守衛走廊的有二人。 19以上是可拉的子孫和米拉利的子孫守門的班次。

聖殿裡的其他職務

20利未亞希雅負責掌管上帝殿裡的庫房和放奉獻之物的庫房。 21革順拉但的子孫中做族長的有耶希伊利22耶希伊利的兩個兒子西坦約珥負責管理耶和華殿裡的庫房。 23暗蘭族、以斯哈族、希伯崙族、烏歇族也各有其職。 24摩西的孫子——革舜的兒子細布業是庫房的主管。 25細布業的親族有以利以謝以利以謝的兒子是利哈比雅利哈比雅的兒子是耶篩亞耶篩亞的兒子是約蘭約蘭的兒子是細基利細基利的兒子是示羅密26示羅密及其親族負責管理庫房中的奉獻之物,這些物品是大衛王、眾族長、千夫長、百夫長和將領獻給上帝的聖物。 27他們把戰爭中擄掠的財物獻出來,以備建造耶和華的殿。 28撒母耳先見、基士的兒子掃羅尼珥的兒子押尼珥洗魯雅的兒子約押及其他人奉獻的聖物都由示羅密及其親族管理。

29以斯哈族的基拿尼雅及其眾子做官長和士師,為以色列管理聖殿以外的事務。 30希伯崙族的哈沙比雅及其親族一千七百人都很能幹,他們在以色列約旦河以西辦理耶和華和王的事務。 31按家譜記載,希伯崙宗族的族長是耶利雅大衛執政第四十年,經過調查,在基列雅謝希伯崙族中找到一些能幹的人。 32耶利雅的親族有兩千七百人,都是能幹的族長。大衛王派他們在呂便支派、迦得支派和瑪拿西半個支派中辦理一切有關上帝和王的事務。