የሰራዊቱ ዋና ዋና ክፍሎች
1የእስራኤል የቤተ ሰብ አለቆች፣ የሻለቆች፣ የመቶ አለቆች እንዲሁም ዓመቱን ሙሉ በየወሩ የሚመደቡትን ዋና ዋና ክፍሎች በተመለከተ ንጉሡን ያገለገሉ አለቆቻቸው ዝርዝር ይህ ነው። እያንዳንዱ ዋና ክፍል ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረው።
2በመጀመሪያው ወር፣ የመጀመሪያው ዋና ክፍል የበላይ የዘብድኤል ልጅ ያሾብዓም ሲሆን፣ በሥሩ የሚታዘዙ ሃያ አራት ሺሕ ሰዎች ነበሩ። 3እርሱም የፋሬስ ዘር ሲሆን፣ በመጀመሪያው ወር የሰራዊቱ ሹማምት ሁሉ የበላይ ነበር።
4በሁለተኛው ወር፣ የክፍለ ጦሩ የበላይ አዛዥ አሆሃዊው ዱዲ ሲሆን፣ የዚሁ ክፍል መሪ ደግሞ ሚቅሎት ነው፤ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።
5በሦስተኛውም ወር፣ የሦስተኛው ክፍለ ጦር የበላይ አዛዥ የካህኑ የዮዳሄ ልጅ በናያስ ነበረ፤ ዋናው እርሱ ሲሆን፣ በሥሩ ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ። 6ይህም ከሠላሳዎቹ ይልቅ ኀያል ሲሆን፣ የሠላሳዎቹ የበላይ ነበረ፤ ልጁ ዓሚዛ ባድም የክፍሉ ሰራዊት አዛዥ ነበረ።
7በአራተኛው ወር፣ አራተኛው የበላይ አዛዥ የኢዮአብ ወንድም አሣሄል ሲሆን፣ በእግሩ የተተካውም ልጁ ዝባድያ ነው፤ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።
8በአምስተኛው ወር፣ አምስተኛው የበላይ አዛዥ ይዝራዊው ሸምሁት ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።
9በስድስተኛው ወር፣ ስድስተኛው የበላይ አዛዥ የቴቁሐዊው የዒስካ ልጅ ዒራስ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።
10በሰባተኛው ወር፣ ሰባተኛው የበላይ አዛዥ የኤፍሬም ወገን የሆነው ፍሎናዊው ሴሌስ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።
11በስምንተኛው ወር፣ ስምንተኛው የበላይ አዛዥ ከካዛራውያን ወገን የሆነው ኩሳታዊው ሲቦካይ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።
12በዘጠነኛው ወር፣ ዘጠነኛው የበላይ አዛዥ ከብንያም ወገን የሆነው ዓናቶታዊው አቢዔዜር ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።
13በዐሥረኛው ወር፣ ዐሥረኛው የበላይ አዛዥ ከከዛራውያን ወገን የሆነው ነጦፋዊው ኖኤሬ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።
14በዐሥራ አንደኛው ወር፣ ዐሥራ አንደኛው የበላይ አዛዥ ከኤፍሬም ወገን የሆነው ጲርዓቶናዊው በናያስ ሲሆን፣ በሥሩም ሃያ አራት ሺሕ ሰው ነበረ።
15በዐሥራ ሁለተኛው ወር፣ ዐሥራ ሁለተኛው የበላይ አዛዥ ከጎቶንያል ቤተ ሰብ የሆነው ነጦፋዊው ሔልዳይ ነበረ።
የየነገዱ የጦር ሹማምት
16የየነገዱ የእስራኤል የጦር ሹማምት፤
በሮቤል ነገድ ላይ የተሾመው፣ የዝክሪ ልጅ አልዓዛር፤
በስምዖን ነገድ ላይ የተሾመው፣ የመዓካ ልጅ ሰፋጥያስ።
17በሌዊ ነገድ ላይ የተሾመው፣ የቀሙኤል ልጅ ሐሸብያ፤
በአሮን ነገድ ላይ የተሾመው፣ ሳዶቅ።
18በይሁዳ ነገድ ላይ የተሾመው፣ የዳዊት ወንድም ኤሊሁ፤
በይሳኮር ነገድ ላይ የተሾመው፣ የሚካኤል ልጅ ዖምሪ።
19በዛብሎን ነገድ ላይ የተሾመው፣ የአብድዩ ልጅ ይሽማያ፤
በንፍታሌም ነገድ ላይ የተሾመው፣ የዓዝሪኤል ልጅ ለኢያሪሙት።
20በኤፍሬም ነገድ ላይ የተሾመው፣ የዓዛዝያ ልጅ ሆሴዕ፤
በምናሴ ነገድ እኩሌታ ላይ የተሾመው፣ የፈዳያ ልጅ ኢዩኤል።
21በገለዓድ ባለው የምናሴ ነገድ እኩሌታ ላይ የተሾመው፣ የዘካርያስ ልጅ አዶ፤ በብንያም ነገድ ላይ የተሾመው፣ የአበኔር ልጅ የዕሢኤል።
22በዳን ነገድ ላይ የተሾመው፣ የይሮሐም ልጅ ዓዛርኤል፤ እንግዲህ የእስራኤል ነገድ አለቆች እነዚህ ነበሩ።
23እግዚአብሔር እስራኤልን እንደ ሰማይ ከዋክብት እንደሚያበዛቸው ተስፋ ሰጥቶ ስለ ነበር፣ ዳዊት ዕድሜያቸው ሃያና ከዚያ በታች የሆነውን አልቈጠረም ነበር። 24የጽሩያ ልጅ ኢዮአብ መቍጠር ጀመረ፤ ሆኖም አልፈጸመውም፤ መቈጠራቸው በእስራኤል ላይ ቍጣ ስላመጣ፣ የተቈጠረውም በንጉሡ ዳዊት መዝገብ አልገባም።
ንጉሡ የሾማቸው የበላይ ተቈጣጣሪዎች
25የዓዲኤል ልጅ ዓዝሞት የቤተ መንግሥቱ ዕቃ ቤት ኀላፊ ነበረ፤
የዖዚያ ልጅ ዮናታን በየአውራጃው በየከተማው፣ በየመንደሩና በየቃፊር መጠበቂያው ላሉት ዕቃ ቤቶች ኀላፊ ነበረ።
26የክሉብ ልጅ ዔዝሪ ምድሪቱን ለሚያርሱት ገበሬዎች ኀላፊ ነበረ።
27ራማታዊው ሰሜኢ የወይን ተክል ቦታዎች ኀላፊ ነበረ፤ ሸፋማዊው ዘብዲ የወይን ጠጅ ዕቃ ቤት ኀላፊ ነበረ።
28ጌድራዊው በአልሐናን በምዕራባዊው ኰረብታዎች ግርጌ ለሚገኙት የወይንና የወርካ ዛፎች ጥበቃ ኀላፊ ነበረ።
29ሳሮናዊው ሰጥራይ በሳሮን ለሚሰማሩት የከብት መንጋዎች ኀላፊ ነበረ፤
የዓድላይ ልጅ ሻፋጥ በሸለቆው ውስጥ ላሉት የከብት መንጋዎች ኀላፊ ነበረ።
30እስማኤላዊው ኡቢያስ የግመሎች ኀላፊ ነበረ።
ሜሮኖታዊው ዬሕድያ የአህዮች ኀላፊ ነበረ።
31አጋራዊው ያዚዝ የበግና የፍየል መንጋዎች ኀላፊ ነበረ።
እነዚህ ሁሉ የንጉሥ ዳዊት ንብረት ኀላፊዎች ነበሩ።
32አስተዋይ የሆነው የዳዊት አጎት ዮናታን አማካሪና ጸሓፊ ነበረ፤ የሐክሞኒም ልጅ ይሒኤል ደግሞ የንጉሡ ልጆች ሞግዚት ነበረ።
33አኪጦፌል የንጉሡ አማካሪ ሲሆን፣ አርካዊው ኩሲ ደግሞ የንጉሡ ወዳጅ ነበረ።
34የበናያስ ልጅ ዮዳሄና አብያታር በአኪጦፌል እግር ተተኩ።
ኢዮአብም የንጉሡ የክብር ዘብ አዛዥ ሆነ።
以色列的軍隊
1以色列人的族長、千夫長、百夫長及其他官長都分定班次,每班兩萬四千人,每年按月輪流服侍王。
2撒巴第業的兒子雅朔班負責第一班,在一月當值,他班內有兩萬四千人。 3他是法勒斯的子孫,統管一月當值的所有將領。 4亞哈希人朵代負責二月的班次,他的副官是密基羅,他班內有兩萬四千人。 5祭司耶何耶大的兒子比拿雅負責第三班,在三月當值,他班內有兩萬四千人。 6比拿雅是當時的三十位勇士之一,也是三十位勇士之首。他兒子暗米薩拔在他班內做統領。 7約押的兄弟亞撒黑負責第四班,在四月當值,他班內有兩萬四千人,他兒子西巴第雅後來接替了他。 8伊斯拉人珊合負責第五班,在五月當值,他班內有兩萬四千人。 9提哥亞人益吉的兒子以拉負責第六班,在六月當值,他班內有兩萬四千人。 10以法蓮的子孫比倫人希利斯負責第七班,在七月當值,他班內有兩萬四千人。 11謝拉族的戶沙人西比該負責第八班,在八月當值,他班內有兩萬四千人。 12便雅憫的子孫亞拿突人亞比以謝負責第九班,在九月當值,他班內有兩萬四千人。 13謝拉族的尼陀法人瑪哈萊負責第十班,在十月當值,他班內有兩萬四千人。 14以法蓮的子孫比拉頓人比拿雅負責第十一班,在十一月當值,他班內有兩萬四千人。 15俄陀聶族的尼陀法人黑玳負責第十二班,在十二月當值,他班內有兩萬四千人。
以色列各支派的官長
16以下是以色列各支派的首領:呂便支派的首領是細基利的兒子以利以謝;西緬支派的首領是瑪迦的兒子示法提雅; 17利未支派的首領是基姆利的兒子哈沙比雅;亞倫子孫的首領是撒督; 18猶大支派的首領是大衛的哥哥以利戶;以薩迦支派的首領是米迦勒的兒子暗利; 19西布倫支派的首領是俄巴第雅的兒子伊施瑪雅;拿弗他利支派的首領是亞斯列的兒子耶利摩; 20以法蓮支派的首領是阿撒細雅的兒子何細亞;瑪拿西半個支派的首領是毗大雅的兒子約珥; 21基列的瑪拿西另半個支派的首領是撒迦利亞的兒子易多;便雅憫支派的首領是押尼珥的兒子雅西業; 22但支派的首領是耶羅罕的兒子亞薩列。以上這些人是以色列各支派的首領。 23大衛沒有統計二十歲以下的以色列人,因為耶和華曾經應許要使以色列的人數像天上的星那樣多。 24洗魯雅的兒子約押開始統計人數,但沒有完成,因為耶和華因此事而向以色列人發烈怒,因此統計的數目沒有收錄在大衛王記上。
王室產業的主管
25亞疊的兒子押斯馬威管理王室的庫房。烏西雅的兒子約拿單管理城邑、村莊和堡壘的庫房。 26基綠的兒子以斯利管理耕田種地的人。 27拉瑪人示每管理葡萄園。實弗米人撒巴底管理葡萄園的酒窖。 28基第利人巴勒·哈南管理丘陵的橄欖樹和無花果樹。約阿施管理油倉。 29沙崙人施提萊管理沙崙的牛群。亞第萊的兒子沙法管理山谷中的牛群。 30以實瑪利人阿比勒管理駱駝群。米崙人耶希底亞管理驢群。 31夏甲人雅悉管理羊群。以上這些人都是替大衛王管理產業的。
32大衛的叔叔約拿單很精明,任謀士和書記。哈摩尼的兒子耶歇做眾王子的老師。 33亞希多弗也是王的謀士。亞基人戶篩是王的朋友。 34後來,比拿雅的兒子耶何耶大和亞比亞他接替亞希多弗做謀士。約押在王的軍隊中做元帥。