1 ዜና መዋዕል 22 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 22:1-19

1ከዚያም ዳዊት፣ “ከእንግዲህ የእግዚአብሔር አምላክ ቤት በዚህ ይሆናል፤ እንዲሁም ስለ እስራኤል የሚቃጠል መሥዋዕት የሚቀርብበት መሠዊያ በዚሁ ይቆማል” አለ።

ቤተ መቅደሱን ለመሥራት የተደረገ ዝግጅት

2ስለዚህ ዳዊት በእስራኤል የሚኖሩ መጻተኞች እንዲሰበሰቡ አዘዘ፤ ከመካከላቸውም የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ የሚሠራበትን ጥርብ ድንጋይ እንዲያዘጋጁ ጠራቢዎችን መደበ። 3ለቅጥር በሮቹ ምስማርና ማጠፊያ የሚሆን ብዙ ብረትና ከብዛቱ የተነሣ ሊመዘን የማይቻል ናስ አዘጋጀ። 4እንዲሁም ሲዶናውያንና ጢሮሳውያን በብዛት አምጥተውለት ስለ ነበር፣ ስፍር ቍጥር የሌለው የዝግባ ዕንጨት አሰናዳ።

5ዳዊትም፣ “ልጄ ሰሎሞን ወጣት ነው፤ ልምዱም የለውም፤ ለእግዚአብሔር የሚሠራው ቤተ መቅደስ ደግሞ እጅግ የሚያምር፣ በአሕዛብም ሁሉ ዘንድ ዝናው የተሰማና እጅግ የተዋበ መሆን አለበት፤ ስለዚህ ሁሉንም እኔ አዘጋጃለሁ” አለ። እንዳለውም ዳዊት ከመሞቱ በፊት በብዛት አዘጋጀ።

6ከዚያም ልጁን ሰሎሞንን ጠርቶ ለእስራኤል አምላክ ለእግዚአብሔር ቤት እንዲሠራ አዘዘው።

7ዳዊትም ሰሎሞንን እንዲህ አለው፤ “ልጄ ሆይ፤ ለአምላኬ ለእግዚአብሔር ስም ቤት ለመሥራት በልቤ ዐስብ ነበር፤ 8ነገር ግን ከእግዚአብሔር እንዲህ የሚል ቃል መጣልኝ፤ ‘አንተ ብዙ ደም አፍስሰሃል፤ ብዙ ጦርነትም አድርገሃል፤ በፊቴ በምድር ላይ ብዙ ደም ያፈሰስህ ስለሆነ፣ አንተ ለስሜ ቤት አትሠራልኝም፤ 9ነገር ግን የሰላምና የዕረፍት ሰው የሆነ ልጅ ትወልዳለህ፤ በየአቅጣጫው ካሉ ጠላቶቹ አሳርፈዋለሁ፤ ስሙም ሰሎሞን ይባላል። በዘመኑም ለእስራኤል ሰላምንና ጸጥታን እሰጣለሁ። 10ለስሜ ቤት የሚሠራልኝ እርሱ ነው። እርሱ ልጅ ይሆነኛል፤ እኔም አባት እሆነዋለሁ። ዙፋኑንም በእስራኤል ላይ ለዘላለም አጸናለሁ።’

11“አሁንም ልጄ ሆይ፤ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ይሁን፤ እንድትፈጽመው በተናገረውም መሠረት፣ ተሳክቶልህ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ቤት ለመሥራት ያብቃህ። 12በእስራኤል ላይ አለቃ ባደረገህ ጊዜ፣ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ትፈጽም ዘንድ እግዚአብሔር ጥበብንና ማስተዋልን ይስጥህ። 13እግዚአብሔር በሙሴ አማካይነት ለእስራኤል የሰጠውን ሕጉንና ሥርዐቱን ተጠንቅቀህ ብትጠብቅ ይሳካልሃል፤ አይዞህ ጠንክር፤ በርታ፤ ተስፋም አትቍረጥ።

14ለእግዚአብሔር ቤት እንዲሆንም አንድ ሺሕ መክሊት22፥14 3,450 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው ወርቅ፣ አንድ ሚሊዮን መክሊት22፥14 34,500 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው ብር፣ ከብዛቱ የተነሣ ሊመዘን የማይቻል ናስና ብረት ለማዘጋጀት በተቻለኝ ሁሉ ጥሬአለሁ፤ በተረፈ አንተ ጨምርበት። 15ድንጋይ ጠራቢዎች፣ ግንበኞች፣ ዐናጢዎች የሆኑ ብዙ ሠራተኞች፣ እንዲሁም በልዩ ልዩ ሙያ የተጠበቡ ሰዎች አሉህ፤ 16እነዚህም ቍጥራቸው እጅግ የበዛ የወርቅ፣ የብር፣ የናስና የብረት ሠራተኞች ናቸው። በል ሥራህን ጀምር፤ እግዚአብሔርም ከአንተ ጋር ይሁን።”

17ከዚያም ዳዊት የእስራኤል መሪዎች ሁሉ ልጁን ሰሎሞንን እንዲረዱት አዘዘ፤ 18እንዲህም አለ፤ “እግዚአብሔር አምላካችሁ እስካሁን ከእናንተ ጋር አይደለምን? በየአቅጣጫውስ ዕረፍትን ሰጥቷችሁ የለምን? የምድሪቱን ነዋሪዎች በእጄ አሳልፎ ሰጥቶኛል፤ ምድሪቱም ለእግዚአብሔርና ለሕዝቡ ተገዝታለች። 19አሁንም እግዚአብሔር አምላካችሁን ለመፈለግ ልባችሁንና ነፍሳችሁን ሰብስቡ። የእግዚአብሔርን የኪዳኑን ታቦትና ንዋያተ ቅድሳቱን ለእግዚአብሔር ስም ወደሚሠራው ቤተ መቅደስ አምጥታችሁ የአምላክን የእግዚአብሔርን መቅደስ ሥሩ።”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

歷代志上 22:1-19

1大衛說:「耶和華上帝的殿和以色列人獻燔祭的壇要在這裡。」

大衛籌備建殿

2大衛下令召集住在以色列的外族人,派他們採鑿建上帝殿用的石頭。 3大衛預備了大量的鐵,用來做門扇的釘子和鉤子,又預備了不計其數的銅。 4他還預備了無數的香柏木,都是西頓人和泰爾人給他運來的。

5大衛說:「為耶和華建造的殿宇必須宏偉輝煌,聞名於世,而我的兒子所羅門年紀還輕、閱歷尚淺,所以我要為這殿預備材料。」因此,大衛在去世前為建殿預備了許多材料。

6大衛召來兒子所羅門,囑咐他要為以色列的上帝耶和華建造殿宇。 7他對所羅門說:「兒啊,我本想為我的上帝耶和華的名建造一座殿宇。 8但耶和華對我說,『你殺了許多人,打了很多仗,在我眼前使許多人血灑大地,因此你不可為我的名建造殿宇。 9你將生一個兒子,我必使他安享太平,不受四圍的仇敵侵擾。他的名字要叫所羅門,他執政期間,我必使以色列太平安寧。 10他將為我的名建造殿宇,他要做我的兒子,我要做他的父親,我要使他的王朝在以色列永遠長存。』

11「兒啊,願耶和華與你同在,使你亨通,照你的上帝耶和華的吩咐去建造祂的殿。 12願耶和華賜你聰明和智慧,以便你照祂的律法治理以色列13你若謹遵耶和華藉摩西吩咐以色列的律例和典章,就必亨通。你要剛強勇敢,不可驚慌害怕。 14看啊,我歷盡艱辛,為耶和華的殿預備了三千四百五十噸金子、三萬四千五百噸銀子和不計其數的銅和鐵。我還預備了木料和石頭。你還要多加預備。 15你有許多工匠,如鑿石匠、砌石匠、木匠等各種能工巧匠, 16還有不計其數的金匠、銀匠、銅匠和鐵匠。現在動工吧,願耶和華與你同在。」

17大衛又吩咐以色列的眾首領幫助他兒子所羅門18他說:「你們的上帝耶和華與你們同在,使你們四境平安。祂將這地方的居民交在我手中,使這地方被祂和祂的子民治理。 19現在,你們要全心全意地尋求你們的上帝耶和華,去建造耶和華上帝的聖所,好將祂的約櫃和聖潔器皿都放在裡面。」