1 ዜና መዋዕል 23 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

1 ዜና መዋዕል 23:1-32

ሌዋውያን

1ዳዊት በሸመገለና ዕድሜው በገፋ ጊዜ፣ ልጁን ሰሎሞንን በእስራኤል ላይ አነገሠው።

2እንዲሁም መላውን የእስራኤልን መሪዎች፣ ካህናቱንና ሌዋውያኑን ሁሉ በአንድነት ሰበሰበ። 3ዕድሜያቸው ሠላሳና ከዚያ በላይ የሆኑ ወንዶች ሁሉ ተቈጠሩ፤ ቍጥራቸውም በጠቅላላው ሠላሳ ስምንት ሺሕ ነበረ። 4ዳዊትም እንዲህ አለ፤ “ከእነዚህ መካከል ሃያ አራቱ ሺሕ የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ሥራ ይቈጣጠሩ፤ ስድስቱ ሺሕ ደግሞ ሹሞችና ዳኞች ይሁኑ፤ 5አራቱ ሺሕ የቅጥሩ በር ጠባቂዎች ይሁኑ፤ አራቱ ሺሕ ደግሞ ለዚሁ ብዬ ባዘጋጀሁት የዜማ መሣሪያ እግዚአብሔርን ያመስግኑ”።

6ዳዊትም ሌዋውያኑን በሌዊ ልጆች በጌድሶን፣ በቀዓትና በሜራሪ በየጐሣቸው መደባቸው።

ጌድሶናውያን

7ከጌድሶናውያን ወገን፤

ለአዳን፣ ሰሜኢ።

8የለአዳን ወንዶች ልጆች፤

የመጀመሪያው ይሒኤል፣ ዜቶም፣ ኢዮኤል፤ በአጠቃላይ ሦስት ናቸው።

9የሰሜኢ ወንዶች ልጆች፤

ሰሎሚት፣ ሐዝኤል፣ ሐራን፤ በአጠቃላይ ሦስት ናቸው።

እነዚህ የለአዳን ቤተ ሰብ አለቆች ናቸው።

10የሰሜኢ ወንዶች ልጆች፤

ኢኢት፣ ዚዛ፣ የዑስ፣ በሪዓ፤

እነዚህ አራቱ የሰሜኢ ልጆች ናቸው።

11የመጀመሪያው ኢኢት፣ ሁለተኛው ደግሞ ዚዛ23፥11 አንድ የዕብራይስጥ ቅጅ፣ የሰብዓ ሊቃናትና የቩልጌት ትርጕሞች (እንዲሁም ቍጥር 11 ይመ) ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ አብዛኞቹ የዕብራይስጥ ቅጆች ግን፣ ዚና ይላሉ። ነበረ፤ የዑስና በሪዓ ግን ብዙ ወንዶች ልጆች አልነበሯቸውም፤ ስለዚህ የተቈጠሩት በሥራ መደብ እንደ አንድ ቤተ ሰብ ሆነው ነው።

ቀዓታውያን

12የቀዓት ወንዶች ልጆች፤

እንበረም፣ ይስዓር፣ ኬብሮን፣ ዑዝኤል፤ በአጠቃላይ አራት ናቸው።

13የእንበረም ወንዶች ልጆች፤

አሮን፣ ሙሴ።

አሮን የተቀደሰ እንዲሆን ተለየ፤ እርሱና ዘሮቹ ለዘላለም ቅዱስ የሆኑትን ነገሮች እንዲቀድሱ፣ በእግዚአብሔር ፊት መሥዋዕት እንዲያቀርቡ፣ በፊቱ እንዲያገለግሉና በስሙም ለዘላለም እንዲባርኩ ተለዩ። 14የእግዚአብሔር ሰው የሙሴ ወንዶች ልጆችም እንደ ሌዊ ነገድ ሆነው ተቈጠሩ።

15የሙሴ ወንዶች ልጆች፤

ጌርሳም፣ አልዓዛር።

16የጌርሳም ዘሮች፤

ሱባኤል።

17የአልዓዛር ዘሮች፤

የመጀመሪያው ረዓብያ ነበረ።

አልዓዛር ሌሎች ወንዶች ልጆች አልነበሩትም፤ የረዓብያ ወንዶች ልጆች ግን እጅግ ብዙ ነበሩ።

18የይስዓር ወንዶች ልጆች፤

የመጀመሪያው ሰሎሚት ነበረ።

19የኬብሮን ወንዶች ልጆች፤

የመጀመሪያው ይሪያ፣ ሁለተኛው አማርያ፣ ሦስተኛው የሕዚኤል፣ አራተኛው ይቅምዓም ነበሩ።

20የዑዝኤል ወንዶች ልጆች፤

የመጀመሪያው ሚካ፣ ሁለተኛው ይሺያ ነበሩ።

ሜራሪያውያን

21የሜራሪ ወንዶች ልጆች፤

ሞሖሊ፣ ሙሲ።

የሞሖሊ ወንዶች ልጆች፤

አልዓዛርና ቂስ ነበሩ።

22አልዓዛር ወንድ ልጅ ሳይወልድ ሞተ፤ ልጆቹ ሴቶች ብቻ ነበሩ፤ እነርሱንም የአጎታቸው የቂስ ልጆች አገቧቸው።

23የሙሲ ወንዶች ልጆች፤

ሞሖሊ፣ ዔደር፣ ለኢያሪሙት በአጠቃላይ ሦስት ናቸው።

24እንግዲህ እነዚህ የቤተ ሰቡ አለቆች ሆነው እያንዳንዳቸው በየስማቸው ተመዝግበው የተቈጠሩት የሌዊ ዘሮች ናቸው፤ ዕድሜያቸውም ሃያና ከዚያ በላይ የሆናቸው በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ውስጥ የሚያገለግሉ ነበሩ። 25ዳዊት እንዲህ ብሎ ነበርና፣ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ለሕዝቡ ዕረፍት ሰጥቷል፤ በኢየሩሳሌምም ለዘላለም ለመኖር መጥቷል፤ 26ሌዋውያን ከእንግዲህ ወዲህ ድንኳኑን ወይም የመገልገያ ዕቃውን ሁሉ መሸከም የለባቸውም።” 27ዳዊት በሰጠው የመጨረሻ መመሪያ መሠረት የተቈጠሩት ሌዋውያን ዕድሜያቸው ሃያና ከዚያ በላይ ነበረ።

28የሌዋውያኑ ተግባር በእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አገልግሎት የአሮንን ዘሮች መርዳት፣ የቤተ መቅደሱን ቅጥር ግቢና ክፍሎች መንከባከብ፣ የተቀደሱ ዕቃዎችን ሁሉ ማንጻትና በእግዚአብሔር ቤት ያሉትን ሌሎች ተግባሮች ማከናወን ነበር። 29እንዲሁም መባ ሆኖ የሚቀርበውን ገጸ ኅብስት፣ የእህል ቍርባኑን ዱቄት፣ ያለ እርሾ የሚጋገረውን ቂጣ የሚጋግሩ፣ የሚያቦኩና የሚሰፈረውንም ሆነ የሚለካውን ሁሉ በኀላፊነት የሚቈጣጠሩ እነርሱ ነበሩ። 30በየዕለቱም እግዚአብሔርን ለማመስገንና ለመወደስ ጧት ጧት ይቆሙ ነበር፤ ይህንም ማታ ማታ 31እንዲሁም በየሰንበቱ፣ በወር መባቻ በዓልና በተደነገጉት በዓላት ሁሉ፣ የሚቃጠል መሥዋዕት ለእግዚአብሔር በሚቀርብበት ጊዜ ይፈጽሙ ነበር፤ በተወሰነላቸው ቍጥርና በተሰጠውም መመሪያ መሠረት፣ ዘወትር በእግዚአብሔር ፊት ያገለግሉ ነበር።

32ስለዚህ ሌዋውያኑ ለመገናኛው ድንኳንና ለመቅደሱ እንዲሁም በወንድሞቻቸው በአሮን ዘሮች ሥር ሆነው ለእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ያለባቸውን ኀላፊነት ያከናውኑ ነበር።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

歷代志上 23:1-32

利未人的職務

1大衛年紀老邁,壽數將盡,就立他兒子所羅門以色列王。 2他召集了以色列的眾首領、祭司和利未人。 3凡三十歲以上的利未人都在統計之列,共有三萬八千男子, 4其中有兩萬四千人在耶和華的殿裡司職,六千人做官長和審判官, 5四千人守門,四千人用大衛提供的樂器頌讚耶和華。 6大衛利未革順哥轄米拉利的子孫分成班次。

7革順的兒子有拉但示每8拉但有長子耶歇,還有細坦約珥,共三個兒子, 9都是拉但族的族長。示每的兒子有示羅密哈薛哈蘭三人。 10示每的兒子還有雅哈細拿耶烏施比利亞四人。 11雅哈是長子,細拿是次子。耶烏施比利亞的子孫不多,所以合為一族。

12哥轄暗蘭以斯哈希伯崙烏薛四個兒子。 13暗蘭的兒子是亞倫摩西亞倫和他的子孫永遠被分別出來事奉耶和華,向祂獻至聖之物,在祂面前燒香,奉祂的名祝福,直到永遠。 14上帝的僕人摩西的子孫歸在利未支派的名下。 15摩西的兒子是革舜以利以謝16革舜的長子是細布業17以利以謝只有一個兒子利哈比雅,但利哈比雅子孫眾多。 18以斯哈的長子是示羅密19希伯崙的長子是耶利雅,次子是亞瑪利亞,三子是雅哈悉,四子是耶加緬20烏薛的長子是米迦,次子是耶西雅

21米拉利的兒子是抹利姆示抹利的兒子是以利亞撒基士22以利亞撒終生沒有兒子,只有女兒,同族人基士的兒子娶了她們為妻。 23姆示的三個兒子是末力以得耶利摩24以上是利未各宗族的子孫,他們登記在各自族長的名下,凡二十歲以上的男子都在耶和華的殿裡任職。 25大衛說:「以色列的上帝耶和華已使祂的子民安享太平,祂永遠住在耶路撒冷26利未人再不用抬聖幕和其中的器皿了。」 27按照大衛臨終時的囑咐,二十歲以上的利未人都已被統計。 28他們的任務是幫助亞倫的子孫在耶和華的殿裡司職,管理殿的院子和廂房,負責潔淨聖物等事務。 29他們還負責供餅、做素祭的細麵粉、無酵薄餅的調和、烤製、分量和尺寸。 30他們每天早晚要肅立、頌讚耶和華, 31每逢安息日、朔日23·31 朔日」即每月初一。或其他節期,他們要按照規定的數目將燔祭獻給耶和華, 32並負責看守會幕和聖所,幫助他們的親族——亞倫的子孫在耶和華的殿裡供職。