1 ነገሥት 5 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 5:1-18

ቤተ መቅደሱን ለመሥራት የተደረገ ዝግጅት

5፥1-16 ተጓ ምብ – 2ዜና 2፥1-18

1የጢሮስ ንጉሥ ኪራም በዘመኑ ሁሉ ለዳዊት ወዳጅ ስለ ነበር፣ ሰሎሞን በአባቱ እግር ለመተካት መቀባቱን በሰማ ጊዜ፣ መልእክተኞቹን ወደ ሰሎሞን ላከ። 2ሰሎሞንም እንዲህ የሚል መልእክት ወደ ኪራም መልሶ ላከ፤

3“አባቴ ዳዊት በዙሪያው ሁሉ ከገጠመው ጦርነት የተነሣ፣ እግዚአብሔር ጠላቶቹን ከእግሩ በታች እስኪጥልለት ድረስ ለአምላኩ ለእግዚአብሔር ስም ቤተ መቅደስ መሥራት እንዳልቻለ ታውቃለህ። 4አሁን ግን አምላኬ እግዚአብሔር በዙሪያዬ ሁሉ ሰላም ሰጥቶኛል፤ ጠላትም የለብኝም። 5እነሆ፣ እግዚአብሔር ለአባቴ ለዳዊት፣ ‘ለስሜ ቤተ መቅደስ የሚሠራልኝ ከአንተ ቀጥሎ በዙፋንህ የማስቀምጠው ልጅህ ነው’ ብሎ እንደ ነገረው፣ ለአምላኬ ለእግዚአብሔር ስም ቤተ መቅደስ ለመሥራት ዐስቤአለሁ።

6“ስለዚህ የሊባኖስ ዝግባ እንዲቈረጥልኝ ትእዛዝ ስጥ፤ ሰዎቼ ከሰዎችህ ጋር አብረው ይሠራሉ፤ የሰዎችህንም ደመወዝ አንተ በወሰንኸው እከፍልሃለሁ፤ ከሰዎቼ መካከል እንደ ሲዶናውያን ዕንጨት በመቍረጥ እስከዚህ የሠለጠነ ሰው አለመኖሩን ራስህም ታውቃለህና።”

7ኪራም የሰሎሞን መልእክት በደረሰው ጊዜ እጅግ ደስ ስላለው፣ “ይህን ታላቅ ሕዝብ እንዲመራ ለዳዊት ጥበበኛ ልጅ ሰጥቶታልና ዛሬ ምስጋና ለእግዚአብሔር ይግባው” አለ።

8ስለዚህ ኪራም፣ ለሰሎሞን እንዲህ ሲል ላከበት፤

“የላክኸው መልእክት ደርሶኛል፤ የዝግባውንና የጥዱን ግንድ በማቅረብ ረገድ የምትፈልገውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ፤ 9ሰዎቼ ግንዱን ከሊባኖስ እስከ ባሕሩ ድረስ ጐትተው ያወርዳሉ፤ እኔም ግንዱ ሁሉ ታስሮ አንተ እስከ ወሰንኸው ስፍራ በባሕር ተንሳፍፎ እንዲደርስ አደርጋለሁ፤ እዚያም እኔ እፈታዋለሁ፤ አንተም ትወስደዋለህ፤ አንተም ለቤተ ሰቤ ቀለብ በመስጠት ፍላጎቴን ታሟላለህ።”

10በዚህ ሁኔታ ኪራም ለሰሎሞን የሚያስፈልገውን የዝግባና የጥድ ግንድ በሙሉ ያቀርብለት ጀመር፤ 11ሰሎሞን ደግሞ ለኪራም ቤተ ሰው ቀለብ እንዲሆን ሃያ ሺሕ የቆሮስ መስፈሪያ5፥11 4400000 ኪሎ ሊትር ያህል ነው። ስንዴ፣ ሃያ ሺሕ ኮር5፥11 ዕብራይስጡና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ሃያ ኮር ይላሉ (2ዜና 2፥10 ይመ) ንጹሕ5፥11 440 ኪሎ ሊትር ያህል ነው። የወይራ ዘይት ሰጠው፤ ይህን ባለማቋረጥ በየዓመቱ ለኪራም ይሰጥ ነበር። 12እግዚአብሔርም በገባለት ተስፋ መሠረት ለሰሎሞን ጥበብን ሰጠው፤ በኪራምና በሰሎሞን መካከልም መልካም ግንኙነት ነበር፤ ሁለቱም ቃል ኪዳን አደረጉ።

13ንጉሥ ሰሎሞን ከመላው እስራኤል የጕልበት ሠራተኞችን መለመለ፤ ቍጥራቸውም ሠላሳ ሺሕ ነበር። 14እነዚህንም አንድ ወር በሊባኖስ እንዲሠሩ፣ ሁለት ወር በቤታቸው እንዲያርፉ በማድረግ፣ ዐሥር ዐሥር ሺዉን ወር ተራ አግብቶ ላካቸው። የጕልበት ሠራተኞቹም አለቃ አዶኒራም ነበር። 15ሰሎሞንም በኰረብታማው አገር ሰባ ሺሕ ተሸካሚዎችና ሰማንያ ሺሕ ድንጋይ ጠራቢዎች ነበሩት፤ 16እንዲሁም ሥራውን የሚቈጣጠሩ ሦስት ሺሕ ሦስት መቶ5፥16 ዕብራይስጡና አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ሦስት ሺሕ ስድስት መቶ ይላሉ። ኀላፊዎች ነበሩ። 17እነርሱም በንጉሡ ትእዛዝ ለቤተ መቅደሱ መሠረት የሚሆን ታላላቅና ምርጥ ድንጋይ ፈልፍለው በማውጣት የተጠረበ ድንጋይ አዘጋጁ። 18የሰሎሞንና የኪራም የእጅ ባለሙያዎች እንዲሁም የጌባል ሰዎች5፥18 ይኸውም ቢብሎስ ነው። ለቤተ መቅደሱ የሚያስፈልገውን ዕንጨትና ድንጋይ ፈልጠው አዘጋጁ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

列王紀上 5:1-18

預備建造聖殿

1泰爾希蘭素來與大衛修好,他聽說以色列人膏立了所羅門繼承大衛的王位,就遣使者來見所羅門2所羅門也派人去見希蘭,說: 3「你知道,我父大衛因周圍戰事連連,未能為他的上帝耶和華建殿,要等到耶和華使仇敵伏在他腳下後再建。 4現在我的上帝耶和華使我四境太平,內外無憂, 5我想為我的上帝耶和華建殿,因為耶和華曾對我父大衛說,『我必使你的兒子繼承你的王位,他必為我的名建殿。』 6請你命人為我砍伐黎巴嫩的香柏木。我會派人幫助你的人,並按你的要求付你的人工錢。因為你知道,我們沒有人像西頓人那樣善於砍伐樹木。」

7希蘭聽了所羅門的話後,非常高興,說:「今天當讚美耶和華!祂賜給大衛一個有智慧的兒子治理這偉大的民族。」 8他派人回覆所羅門說:「我已收到你派人帶來的口信。我一定會照你的心願提供香柏木和松木。 9我的工人會將這些木料從黎巴嫩紮成木筏,經海道運到你指定的地點。木筏拆散以後,你就可以點收了。你也要成全我的心願,供應我家食糧。」 10於是,希蘭供應所羅門需用的香柏木和松木, 11所羅門每年供應希蘭四百四十萬升麥子和四千四百升橄欖油。 12耶和華照著應許賜給所羅門智慧。他跟希蘭修好,締結盟約。

13所羅門王從以色列徵集了三萬勞工, 14派他們每月輪班到黎巴嫩工作,每班一萬人,在黎巴嫩一個月,在家兩個月。亞多尼蘭做他們的總管。 15所羅門又徵用了七萬名搬運工,八萬名在山上鑿石的匠人。 16此外,他還派了三千三百名監工,監督工人做工。 17他們按照王的命令在山上鑿出珍貴的巨石,用來作殿的根基。 18於是,所羅門希蘭的工匠及迦巴勒人鑿好石頭,備好木料,準備建殿。