2 ሳሙኤል 1 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

2 ሳሙኤል 1:1-27

ዳዊት የሳኦልን ሞት ሰማ

1፥4-12 ተጓ ምብ – 1ሳሙ 31፥1-131ዜና 10፥1-12

1ሳኦል ከሞተ በኋላ፣ ዳዊት አማሌቃውያንን ድል አድርጎ በመመለስ፣ በጺቅላግ ሁለት ቀን ቈየ። 2በሦስተኛውም ቀን የተቀደደ ልብስ የለበሰ፣ በራሱም ላይ ትቢያ የነሰነሰ አንድ ሰው ከሳኦል ሰፈር መጣ። ወደ ዳዊት እንደ ደረሰም፣ ወደ መሬት ለጥ ብሎ በአክብሮት እጅ ነሣ።

3ዳዊትም፣ “ከወዴት መጣህ?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፣ “ከእስራኤላውያን ሰፈር ሸሽቼ መምጣቴ ነው” በማለት መለሰለት።

4ዳዊትም፣ “ምን ነገር ተፈጠረ?” ሲል ጠየቀው።

እርሱም፣ “ሰዎቹ ከጦርነቱ ሸሽተዋል፤ ብዙዎቹ ወድቀዋል፤ ሞተዋል፤ ሳኦልና ልጁ ዮናታንም ሞተዋል” አለ።

5ከዚያም ዳዊት ወሬውን የነገረውን ወጣት፣ “ሳኦልና ልጁ ዮናታን መሞታቸውን እንዴት ዐወቅህ?” ሲል ጠየቀው።

6ወሬ ነጋሪው ወጣትም እንዲህ አለ፤ “ድንገት ወደ ጊልቦዓ ተራራ ወጥቼ ነበር፤ እዚያም ሳኦል ጦሩን ተደግፎ ሳለ፣ ሠረገሎችና ፈረሰኞች ተከታትለው ደረሱበት። 7ወደ ኋላውም ዞር ሲል እኔን ስላየ ጠራኝ፤ እኔም፣ ‘ምን ልታዘዝ’ አልሁ።

8“እርሱም፣ ‘አንተ ማን ነህ?’ ሲል ጠየቀኝ፤

“እኔም ‘አማሌቃዊ ነኝ’ ብዬ መለስሁለት።

9“ከዚያም፣ ‘እኔ በሞት ጣር ውስጥ እገኛለሁ፤ ነፍሴ ግን አልወጣችም፤ እባክህ በላዬ ቆመህ ግደለኝ’ አለኝ።

10“መቼም ከወደቀ በኋላ እንደማይተርፍ ስላወቅሁ፣ በላዩ ቆሜ ገደልሁት፤ በራሱ ላይ የነበረውን ዘውድና የክንዱን አንባር ወስጄ እነሆ፤ ለጌታዬ አምጥቻለሁ።”

11ከዚያም ዳዊትና አብረውት የነበሩት ሰዎች ሁሉ ልብሳቸውን ቀደዱ። 12ለሳኦልና ለልጁ ለዮናታን፣ ለእግዚአብሔር ሰራዊትና ለእስራኤል ቤት ዐዘኑ፤ አለቀሱ፤ እስከ ማታም ድረስ ጾሙ፤ የወደቁት በሰይፍ ነበርና።

13ዳዊትም ወሬውን ያመጣለትን ወጣት፣ “ከየት ነው የመጣኸው?” ብሎ ጠየቀው።

እርሱም፣ “እኔ የአንድ መጻተኛ አማሌቃዊ ልጅ ነኝ” ብሎ መለሰ።

14ዳዊትም፣ “ታዲያ እግዚአብሔር የቀባውን ለማጥፋት እጅህን ስታነሣ እንዴት አልፈራህም?” ሲል ጠየቀው።

15ዳዊትም ከጕልማሶቹ አንዱን ጠርቶ፣ “በል ቅረብና ውደቅበት” አለው። እርሱም መታው፤ ሞተም። 16ዳዊትም፣ “ ‘እግዚአብሔር የቀባውን ገድያለሁ’ ስትል የገዛ አፍህ መስክሮብሃልና፣ ደምህ በራስህ ላይ ይሁን” አለው።

ዳዊት ለሳኦልና ለዮናታን የተቀኘው የሐዘን እንጕርጕሮ

17ዳዊትም በሳኦልና በልጁ በዮናታን ሞት ምክንያት ይህን የሐዘን እንጕርጕሮ እየተቀኘ አለቀሰ፤ 18እንዲሁም የቀስት እንጕርጕሮ የተባለውን ለይሁዳ ሕዝብ እንዲያስተምሩ አዘዘ፤ ይህም በያሻር መጽሐፍ ተጽፏል።

19“እስራኤል ሆይ፤ ክብርህ በኰረብቶችህ ላይ ተወግቶ ሞቷል፤

ኀያላኑ እንዴት እንደዚህ ይውደቁ!

20“ይህን በጌት አትናገሩ፤

በአስቀሎናም መንገዶች አታውጁት፤

የፍልስጥኤም ቈነጃጅት አይደሰቱ፤

ያልተገረዙት ሴቶች ልጆች እልል አይበሉ።

21“እናንተ የጊልቦዓ ተራሮች ሆይ፤

ጠል አያረስርሳችሁ፤

ዝናብም አይውረድባችሁ፤

የቍርባን እህል የሚያበቅሉም ዕርሻዎች አይኑራቸው፤

በዚያ የኀያሉ ሰው ጋሻ ረክሷልና፤ የሳኦል ጋሻ ከእንግዲህ በዘይት አይወለወልም።

22“ከሞቱት ሰዎች ደም፣

ከኀያላኑም ሥብ፣

የዮናታን ቀስት ተመልሳ አልመጣችም፤

የሳኦልም ሰይፍ በከንቱ አልተመለሰችም።

23ሳኦልና ዮናታን በሕይወት እያሉ፣

የሚዋደዱና የሚስማሙ ነበሩ፤

ሲሞቱም አልተለያዩም፤

ከንስርም ይልቅ ፈጣኖች፣

ከአንበሳም ይልቅ ብርቱዎች ነበሩ።

24“እናንት የእስራኤል ቈነጃጅት ሆይ፤

ሐምራዊ ቀሚስና ቀጭን ፈትል ላለበሳችሁ፣

ልብሶቻችሁንም በወርቀ ዘቦ ላስጌጠላችሁ፣

ለሳኦል አልቅሱለት።

25“ኀያላን እንዴት እንዲህ በጦርነት ወደቁ!

ዮናታን በኰረብቶችህ ላይ ተወግቶ ሞቷል።

26ወንድሜ ዮናታን ሆይ፤ እኔ ስለ አንተ ዐዘንሁ፤

አንተ ለእኔ እጅግ ውድ ነበርህ፤

ፍቅርህ ለእኔ ድንቅ ነበረ፤

ከሴት ፍቅርም ይልቅ ግሩም ነበር።

27“ኀያላኑ እንዴት ወደቁ!

የጦር መሣሪያዎቹስ እንዴት ከንቱ ይሁኑ!”

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

撒母耳記下 1:1-27

大衛得知掃羅的死訊

1大衛戰勝了亞瑪力人之後便回到洗革拉,在那裡住了兩天。那時掃羅已經死了。 2第三天,有一個衣服撕裂、頭蒙灰塵的人從掃羅軍營中跑到大衛面前,俯伏下拜。 3大衛問他:「你從哪裡來?」那人答道:「我是從以色列軍營逃出來的。」 4大衛說:「請告訴我那邊的情況。」他說:「以色列軍潰逃,傷亡慘重,掃羅和他兒子約拿單都死了!」 5大衛又問報信的青年:「你怎麼知道掃羅和他兒子約拿單死了?」 6青年說:「我偶然到基利波山,看見掃羅在那裡扶槍而立,敵人的戰車騎兵緊緊追來。 7他回頭看到我,便呼喚我。我說,『我在這裡。』 8他問我是什麼人。我告訴他我是亞瑪力人。 9掃羅說他痛苦難當,卻又死不掉,要我殺了他。 10我知道他身受重傷,必死無疑,就把他殺了,並取下他頭上的王冠和臂上的鐲子帶來獻給我主。」

11大衛就撕裂衣服,他的隨從也撕裂衣服。 12他們因掃羅、他的兒子約拿單和耶和華的子民——以色列同胞陣亡而悲哀痛哭,禁食直到黃昏。 13大衛又問報信的青年:「你是哪裡的人?」他答道:「我是寄居在以色列亞瑪力人。」 14大衛說:「你怎麼敢下手殺耶和華所膏立的王? 15-16你是咎由自取!因為你親口承認自己殺了耶和華所膏立的王。」大衛隨即命令一個年輕的隨從殺死他,隨從便殺死了他。

大衛的哀歌

17大衛作了一首輓歌哀悼掃羅和他兒子約拿單18並吩咐人教導猶大人唱這首弓歌。這首歌記在《雅煞珥書》上,歌詞說:

19以色列啊,

你榮耀的王伏屍山上,

偉大的勇士竟然倒下!

20不要在迦特宣告,

不要在亞實基倫的街上傳揚,

免得非利士的婦女幸災樂禍,

免得未受割禮之人的女子歡喜雀躍。

21基利波山啊,願你沒有雨露,

你的田地不長獻祭用的五穀,

因為在那裡勇士的盾牌污跡斑斑,

掃羅的盾牌沒有抹油。

22約拿單的弓射敵無數,

掃羅的劍不殺強敵不收回。

23掃羅約拿單深受愛戴,

生死不分離。

他們比鷹更敏捷,

比獅子還強壯。

24以色列的女子啊,

掃羅哀哭吧!

他曾使你們衣服華美,

穿金戴銀。

25「勇士竟戰死沙場!

約拿單竟伏屍山上!

26我的兄弟約拿單啊,

我為你悲傷,

你對我情深義重,

你對我的愛勝過女人的戀情。

27「偉大的勇士竟然倒下!

兵器竟然長埋!」