1 ነገሥት 5 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 5:1-18

ቤተ መቅደሱን ለመሥራት የተደረገ ዝግጅት

5፥1-16 ተጓ ምብ – 2ዜና 2፥1-18

1የጢሮስ ንጉሥ ኪራም በዘመኑ ሁሉ ለዳዊት ወዳጅ ስለ ነበር፣ ሰሎሞን በአባቱ እግር ለመተካት መቀባቱን በሰማ ጊዜ፣ መልእክተኞቹን ወደ ሰሎሞን ላከ። 2ሰሎሞንም እንዲህ የሚል መልእክት ወደ ኪራም መልሶ ላከ፤

3“አባቴ ዳዊት በዙሪያው ሁሉ ከገጠመው ጦርነት የተነሣ፣ እግዚአብሔር ጠላቶቹን ከእግሩ በታች እስኪጥልለት ድረስ ለአምላኩ ለእግዚአብሔር ስም ቤተ መቅደስ መሥራት እንዳልቻለ ታውቃለህ። 4አሁን ግን አምላኬ እግዚአብሔር በዙሪያዬ ሁሉ ሰላም ሰጥቶኛል፤ ጠላትም የለብኝም። 5እነሆ፣ እግዚአብሔር ለአባቴ ለዳዊት፣ ‘ለስሜ ቤተ መቅደስ የሚሠራልኝ ከአንተ ቀጥሎ በዙፋንህ የማስቀምጠው ልጅህ ነው’ ብሎ እንደ ነገረው፣ ለአምላኬ ለእግዚአብሔር ስም ቤተ መቅደስ ለመሥራት ዐስቤአለሁ።

6“ስለዚህ የሊባኖስ ዝግባ እንዲቈረጥልኝ ትእዛዝ ስጥ፤ ሰዎቼ ከሰዎችህ ጋር አብረው ይሠራሉ፤ የሰዎችህንም ደመወዝ አንተ በወሰንኸው እከፍልሃለሁ፤ ከሰዎቼ መካከል እንደ ሲዶናውያን ዕንጨት በመቍረጥ እስከዚህ የሠለጠነ ሰው አለመኖሩን ራስህም ታውቃለህና።”

7ኪራም የሰሎሞን መልእክት በደረሰው ጊዜ እጅግ ደስ ስላለው፣ “ይህን ታላቅ ሕዝብ እንዲመራ ለዳዊት ጥበበኛ ልጅ ሰጥቶታልና ዛሬ ምስጋና ለእግዚአብሔር ይግባው” አለ።

8ስለዚህ ኪራም፣ ለሰሎሞን እንዲህ ሲል ላከበት፤

“የላክኸው መልእክት ደርሶኛል፤ የዝግባውንና የጥዱን ግንድ በማቅረብ ረገድ የምትፈልገውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ፤ 9ሰዎቼ ግንዱን ከሊባኖስ እስከ ባሕሩ ድረስ ጐትተው ያወርዳሉ፤ እኔም ግንዱ ሁሉ ታስሮ አንተ እስከ ወሰንኸው ስፍራ በባሕር ተንሳፍፎ እንዲደርስ አደርጋለሁ፤ እዚያም እኔ እፈታዋለሁ፤ አንተም ትወስደዋለህ፤ አንተም ለቤተ ሰቤ ቀለብ በመስጠት ፍላጎቴን ታሟላለህ።”

10በዚህ ሁኔታ ኪራም ለሰሎሞን የሚያስፈልገውን የዝግባና የጥድ ግንድ በሙሉ ያቀርብለት ጀመር፤ 11ሰሎሞን ደግሞ ለኪራም ቤተ ሰው ቀለብ እንዲሆን ሃያ ሺሕ የቆሮስ መስፈሪያ5፥11 4400000 ኪሎ ሊትር ያህል ነው። ስንዴ፣ ሃያ ሺሕ ኮር5፥11 ዕብራይስጡና የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ሃያ ኮር ይላሉ (2ዜና 2፥10 ይመ) ንጹሕ5፥11 440 ኪሎ ሊትር ያህል ነው። የወይራ ዘይት ሰጠው፤ ይህን ባለማቋረጥ በየዓመቱ ለኪራም ይሰጥ ነበር። 12እግዚአብሔርም በገባለት ተስፋ መሠረት ለሰሎሞን ጥበብን ሰጠው፤ በኪራምና በሰሎሞን መካከልም መልካም ግንኙነት ነበር፤ ሁለቱም ቃል ኪዳን አደረጉ።

13ንጉሥ ሰሎሞን ከመላው እስራኤል የጕልበት ሠራተኞችን መለመለ፤ ቍጥራቸውም ሠላሳ ሺሕ ነበር። 14እነዚህንም አንድ ወር በሊባኖስ እንዲሠሩ፣ ሁለት ወር በቤታቸው እንዲያርፉ በማድረግ፣ ዐሥር ዐሥር ሺዉን ወር ተራ አግብቶ ላካቸው። የጕልበት ሠራተኞቹም አለቃ አዶኒራም ነበር። 15ሰሎሞንም በኰረብታማው አገር ሰባ ሺሕ ተሸካሚዎችና ሰማንያ ሺሕ ድንጋይ ጠራቢዎች ነበሩት፤ 16እንዲሁም ሥራውን የሚቈጣጠሩ ሦስት ሺሕ ሦስት መቶ5፥16 ዕብራይስጡና አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም ሦስት ሺሕ ስድስት መቶ ይላሉ። ኀላፊዎች ነበሩ። 17እነርሱም በንጉሡ ትእዛዝ ለቤተ መቅደሱ መሠረት የሚሆን ታላላቅና ምርጥ ድንጋይ ፈልፍለው በማውጣት የተጠረበ ድንጋይ አዘጋጁ። 18የሰሎሞንና የኪራም የእጅ ባለሙያዎች እንዲሁም የጌባል ሰዎች5፥18 ይኸውም ቢብሎስ ነው። ለቤተ መቅደሱ የሚያስፈልገውን ዕንጨትና ድንጋይ ፈልጠው አዘጋጁ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

列王纪上 5:1-18

预备建造圣殿

1泰尔希兰素来与大卫修好,他听说以色列人膏立了所罗门继承大卫的王位,就遣使者来见所罗门2所罗门也派人去见希兰,说: 3“你知道,我父大卫因周围战事连连,未能为他的上帝耶和华建殿,要等到耶和华使仇敌伏在他脚下后再建。 4现在我的上帝耶和华使我四境太平,内外无忧, 5我想为我的上帝耶和华建殿,因为耶和华曾对我父大卫说,‘我必使你的儿子继承你的王位,他必为我的名建殿。’ 6请你命人为我砍伐黎巴嫩的香柏木。我会派人帮助你的人,并按你的要求付你的人工钱。因为你知道,我们没有人像西顿人那样善于砍伐树木。”

7希兰听了所罗门的话后,非常高兴,说:“今天当赞美耶和华!祂赐给大卫一个有智慧的儿子治理这伟大的民族。” 8他派人回复所罗门说:“我已收到你派人带来的口信。我一定会照你的心愿提供香柏木和松木。 9我的工人会将这些木料从黎巴嫩扎成木筏,经海道运到你指定的地点。木筏拆散以后,你就可以点收了。你也要成全我的心愿,供应我家食粮。” 10于是,希兰供应所罗门需用的香柏木和松木, 11所罗门每年供应希兰四百四十万升麦子和四千四百升橄榄油。 12耶和华照着应许赐给所罗门智慧。他跟希兰修好,缔结盟约。

13所罗门王从以色列征集了三万劳工, 14派他们每月轮班到黎巴嫩工作,每班一万人,在黎巴嫩一个月,在家两个月。亚多尼兰做他们的总管。 15所罗门又征用了七万名搬运工,八万名在山上凿石的匠人。 16此外,他还派了三千三百名监工,监督工人做工。 17他们按照王的命令在山上凿出珍贵的巨石,用来作殿的根基。 18于是,所罗门希兰的工匠及迦巴勒人凿好石头,备好木料,准备建殿。