1 ነገሥት 4 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

1 ነገሥት 4:1-34

የሰሎሞን ሹማምት

1ንጉሥ ሰሎሞን በእስራኤል ሁሉ ላይ ነገሠ፤

2ዋና ዋናዎቹ ሹማምቱም እነዚህ ነበሩ፤

የሳዶቅ ልጅ ዓዛርያስ፣ ካህን፤

3የሺሻ ልጆች ኤሊሖሬፍና አኪያ፣ ጸሓፊዎች፤

የአሒሉድ ልጅ ኢዮሣፍጥ፣ ታሪክ ጸሓፊ፤

4የዮዳሄ ልጅ በናያስ፣ የሰራዊቱ ዋና አዛዥ፤

ሳዶቅና አብያታር፣ ካህናት፤

5የናታን ልጅ ዓዛርያስ፣ የአውራጃ ገዦች የበላይ ኀላፊ፤

የናታን ልጅ ዛቡድ፣ ካህንና የንጉሡ የቅርብ አማካሪ፤

6አሒሳር፣ የቤተ መንግሥቱ አዛዥ፤

የዓብዳ ልጅ አዶኒራም የግዳጅ ሥራ ተቈጣጣሪ።

7እንዲሁም ሰሎሞን ለንጉሡና ለንጉሡ ቤት የሚሆነውን ቀለብ ከመላው እስራኤል የሚሰበስቡ ዐሥራ ሁለት የአውራጃ ገዦች ነበሩት፤ እነዚህም እያንዳንዳቸው በዓመት ውስጥ የወር ቀለብ የሚያቀርቡ ነበሩ።

8ስማቸውም እንደሚከተለው ነው፤

ቤንሑር፣ በኰረብታማው በኤፍሬም ምድር፤

9ቤንጼቄር፣ በማቃጽ፣ በሻዓልቢም፣ በቤትሳሜስ፣ በኤሎንቤትሐናን፤

10ቤንሔሴድ፣ በአሩቦት ውስጥ የሚገኙት ሰኰትና የኦፌር አገር በሙሉ የእርሱ ነበር፤

11ቤን አሚናዳብ፤ በናፎት ዶር፣ እርሱም የሰሎሞንን ልጅ ጣፈትን አግብቶ የነበረ ነው፤4፥11 ወይም በናፎት ቁመት ተብሎ ሊተረጐም ይችላል።

12የአሒሉድ ልጅ በዓና፣ በታዕናክና በመጊዶ እንዲሁም ከጻርታን ቀጥሎ ቍልቍል እስከ ኢይዝራኤል ባለው በቤትሳን ሁሉ፣ ከዚያም ዮቅምዓምን ተሻግሮ እስከ አቤልምሖላና ድረስ፣

13ቤንጌበር፣ በገለዓድ ራሞት ከተማ እዚያው ገለዓድ ውስጥ የምናሴ ልጅ የኢያዕር መንደሮች፣ በባሳንም የአርጎብ አውራጃ እንዲሁም በሮቻቸው የናስ መወርወሪያ በሆኑ ስድሳ ባለ ቅጥር ታላላቅ ከተሞች፤

14የዒዶ ልጅ አሒናዳብ፤ በማሃናይም፣

15አኪማአስ በንፍታሌም፣ እርሱም የሰሎሞንን ልጅ ባስማትን አግብቶ የነበረ ነው፤

16የኩሲ ልጅ በዓና፤ በአሴርና በበዓሎት፣

17የፋሩዋ ልጅ ኢዮሣፍጥ በይሳኮር፣

18የኤላ ልጅ ሳሚ በብንያም፣

19የኡሪ ልጅ ጌበር፤ በአሞራውያን ንጉሥ በሴዎን ምድር፣ በባሳን ንጉሥ በዐግ አገር፣ እርሱም የአውራጃው ብቸኛ ገዥ ነበር።

ለሰሎሞን በየቀኑ የሚገባለት ቀለብ

20የይሁዳና የእስራኤል ሕዝቦች ብዛታቸው እንደ ባሕር ዳር አሸዋ ሆነ፤ ይበሉ፣ ይጠጡና ይደሰቱም ነበር። 21ሰሎሞንም ከወንዙ4፥21 በዚህና በ24 ላይ የተጠቀሰው የኤፍራጥስ ወንዝ ነው። አንሥቶ እስከ ፍልስጥኤማውያን ምድር፣ ከዚያም እስከ ግብፅ ዳርቻ ያሉትን መንግሥታት ሁሉ ገዛ፤ እነዚህም አገሮች ግብር አመጡለት፤ በሕይወት ዘመኑም ሁሉ ተገዙለት።

22ለሰሎሞን በየቀኑ የሚገባለትም ቀለብ ይህ ነበር፤ ሠላሳ ኮር4፥22 5500 ኪሎ ግራም ያህል ነው። ማለፊያ ዱቄት፣ ስድሳ ኮር4፥22 11000 ኪሎ ግራም ያህል ነው። መናኛ ዱቄት፣ 23ዐሥር ቅልብ ሰንጋዎች፣ ሃያ ግጦሽ መሬት ላይ የሚውሉ በሬዎች፣ መቶ በግና ፍየል እንዲሁም ዋሊያ፣ ሚዳቋ፣ የበረሓ ፍየልና ምርጥ አዕዋፍ። 24ከወንዙ በስተ ምዕራብ፣ ከቲፍሳ እስከ ጋዛ ያሉትን መንግሥታት ስለ ገዛ፣ በሁሉም አቅጣጫ ሰላም ሆኖለት ነበር። 25በሰሎሞን ዘመን ሁሉ ከዳን አንሥቶ እስከ ቤርሳቤህ ያለው ይሁዳና እስራኤል፣ እያንዳንዱ ሰው ከወይኑና ከበለሱ ጥላ ሥር በሰላም ለመኖር በቃ።

26ሰሎሞን ሠረገላ የሚጐትቱ ፈረሶች የሚያድሩበት አራት ሺሕ ጋጣና ዐሥራ ሁለት ሺሕ ፈረሶች4፥26 ዕብራይስጡና አንዳንድ የሰብዓ ሊቃናት ትርጕሞች አርባ ይላሉ። ነበሩት4፥26 ወይም ሠረገለኞች ተብሎ መተርጐም ይችላል።

27የየአውራጃው ሹማምትም በየወር ተራቸው ንጉሡን ሰሎሞንንና ወደ ንጉሡ ማእድ የሚቀርቡትን ሁሉ ምንም ሳያጓድሉ ይቀልቡ ነበር፤ 28እንዲሁም ለሠረገላ ፈረሶችና ለፈጣን ፈረሶች የተመደበውን ገብስና ጭድ ከተፈለገው ቦታ ድረስ ያመጡ ነበር።

የሰሎሞን ጥበብ

29አምላክ ለሰሎሞን ጥበብንና እጅግ ታላቅ ማስተዋልን እንዲሁም በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ የልብ ስፋትን ሰጠው። 30የሰሎሞን ጥበብ ከምሥራቅ ሰዎች ሁሉ ጥበብ በጣም የላቀ ከግብፅም ጥበብ ሁሉ የበለጠ ነበር፤ 31እርሱም ከማንም ሰው ይልቅ ጥበበኛ ነበር፣ ከኢይዝራኤላዊው ከኤታን፣ ከማሖል ልጆች ከሄማንና ከከልቀድ ደግሞም ከደራል ይልቅ ጥበበኛ ነበር፤ ዝናውም በዙሪያው ባሉት አሕዛብ ሁሉ ተሰማ። 32እርሱም ሦስት ሺሕ ምሳሌዎችን ተናገረ፤ የመሓልዩም ቍጥር ሺሕ አምስት ነበር። 33ከሊባኖስ ዝግባ አንሥቶ በቅጥር ግንብ ላይ እስከሚበቅለው ሂሶጵ ስለ ዕፀዋት ተናግሯል፤ እንዲሁም ስለ እንስሳት፣ ስለ ወፎች፣ በሆዳቸው ስለሚሳቡ እንስሳትና ስለ ዓሦችም ተናግሯል፤ 34ጥበቡን ከሰሙት ከዓለም ነገሥታት ሁሉ የተላኩ፣ የየአገሩ ሰዎች ሁሉ የሰሎሞንን ጥበብ ለማድመጥ መጡ።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

列王纪上 4:1-34

所罗门的臣仆

1所罗门统治以色列2以下是他的众臣仆:撒督的儿子亚撒利雅做祭司; 3示沙的儿子以利何烈亚希亚做书记;亚希律的儿子约沙法做史官; 4耶何耶大的儿子比拿雅做元帅;撒督亚比亚他做祭司长; 5拿单的儿子亚撒利雅掌管吏部;拿单的儿子撒布得祭司做所罗门王的顾问; 6亚希煞总管宫廷事务;亚比大的儿子亚多尼兰总管做劳役的。

7所罗门以色列全国设立了十二个地方官,负责供给王及王室的需用,每年每人负责一个月。 8这十二个地方官是:便·户珥,负责以法莲山区; 9便·底甲,负责玛迦斯沙宾伯·示麦以伦·伯·哈南10便·希悉,负责亚鲁泊,包括梭哥希弗全境; 11所罗门女儿她法的丈夫便·亚比拿达,负责多珥高原; 12亚希律的儿子巴拿,负责他纳米吉多,靠近撒拉他拿耶斯列下边的伯·善全境,以及从伯·善亚伯·米何拉,远至约念13便·基别,负责基列拉末玛拿西子孙雅珥基列的城邑,以及巴珊亚珥歌伯地区有城墙和铜闩的大城六十座; 14易多的儿子亚希拿达,负责玛哈念15所罗门的另一个女儿巴实抹的丈夫亚希玛斯,负责拿弗他利16户筛的儿子巴拿,负责亚设亚禄17帕路亚的儿子约沙法,负责以萨迦18以拉的儿子示每,负责便雅悯19乌利的儿子基别,独自负责从前属亚摩利西宏巴珊基列地区。

所罗门的财富和智慧

20犹大人和以色列人多如海沙,丰衣足食,生活幸福。 21所罗门统管列国,从幼发拉底河至非利士,直到埃及边界。所罗门在世的日子,列国都年年进贡称臣。

22王室每天用三千公斤细面粉、六千公斤粗面粉、 23十头肥牛、二十头草场的牛、一百只羊,此外还有鹿、羚羊、狍子及肥禽。 24所罗门统治幼发拉底河西面所有的国家,从提弗萨直到迦萨,四境安宁。 25所罗门在世的时候,从别示巴犹大人和以色列人都在自己的葡萄树和无花果树下安居。

26所罗门有四万匹拉战车的马,一万二千名骑兵。 27十二个地方官按月供给所罗门王及王室的需用,使他们一无所缺。 28他们也各按其份提供喂马用的大麦和干草。

29上帝赐予所罗门无比的智慧、悟性和渊博的学识。 30他的智慧高过东方人和埃及人的一切智慧, 31无人能比,胜过以斯拉以探玛曷的儿子希幔甲各达大的智慧。他名扬四周列国。 32所罗门写下箴言三千句,作诗歌一千零五首。 33他对飞禽走兽、草木鱼虫,从黎巴嫩的香柏树到长在墙上的牛膝草,都无所不知。 34天下列王风闻所罗门的智慧,都纷纷遣使来求教。