1 ተሰሎንቄ 1 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

1 ተሰሎንቄ 1:1-10

1ከጳውሎስ፣ ከሲላስና1፥1 ግሪኩ ሲልዋኑስ ይላል። ከጢሞቴዎስ፤

በእግዚአብሔር አብና በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ለሆኑት ለተሰሎንቄ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን፤

ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን1፥1 አንዳንድ ቅጆች ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ የሚለው የላቸውም።

ስለ ተሰሎንቄ ሰዎች እምነት የቀረበ ምስጋና

2በጸሎታችን እያስታወስናችሁ ሁልጊዜ እግዚአብሔርን ስለ ሁላችሁ እናመሰግናለን። 3ከእምነት የሆነውን ሥራችሁን፣ ከፍቅር የመነጨውን ድካማችሁንና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ባላችሁ ተስፋ የተገኘውን ጽናታችሁን በአምላካችንና በአባታችን ፊት ዘወትር እናስባለን።

4በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ፤ እርሱ እንደ መረጣችሁ እናውቃለን፤ 5ምክንያቱም ወንጌላችን ወደ እናንተ የመጣው በኀይልና በመንፈስ ቅዱስ፣ በብዙም መረዳት እንጂ በቃል ብቻ አይደለም። ደግሞ ስለ እናንተ ስንል በመካከላችሁ እንዴት እንደ ኖርን ታውቃላችሁ። 6እናንተ እኛንና ጌታን መስላችኋል፤ ምንም እንኳ ብርቱ መከራ ቢደርስባችሁም፣ ቃሉን በመንፈስ ቅዱስ ደስታ ተቀብላችኋል። 7ከዚህም የተነሣ በመቄዶንያና በአካይያ ለሚገኙ ምእመናን መልካም ምሳሌ ሆናችኋል። 8የጌታ ቃል ከእናንተ ወጥቶ በመቄዶንያና በአካይያ መሰማቱ ብቻ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ያላችሁ እምነት በሁሉ ቦታ ታውቋል፤ ስለዚህ እኛ በዚህ ጕዳይ ላይ ምንም መናገር አያስፈልገንም፤ 9በእንዴት ያለ አቀባበል እንደ ተቀበላችሁንና ሕያውና እውነተኛ የሆነውን አምላክ ለማገልገል ከጣዖታት ወደ እግዚአብሔር እንዴት እንደ ተመለሳችሁ እነርሱ ራሳቸው ይናገራሉ፤ 10ደግሞም ከሙታን ያስነሣውንና ከሰማይ የሚመጣውን ልጁን፣ ከሚመጣውም ቍጣ የሚያድነንን ኢየሱስን እንዴት እንደምትጠባበቁ ይናገራሉ።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרת פולוס הראשונה אל-התסלוניקים 1:1-10

1אל קהילת תסלוניקי, ששייכת לאלוהים אבינו ולישוע המשיח אדוננו.

מאת פולוס, סילוונוס וטימותיוס.

שלום וברכה מאת האלוהים אבינו וישוע המשיח אדוננו.

2בכל פעם שאנו מתפללים בעדכם אנו מודים לאלוהים על כולכם, 3ומזכירים לפניו תמיד את מעשיכם הטובים, את אמונתכם החזקה, את אהבתכם ואת ציפייתכם הסבלנית לשובו של ישוע המשיח אדוננו.

4אחים יקרים ואהובי האדון, אנחנו יודעים שאלוהים בחר בכם, 5שהרי כאשר בישרנו לכם את בשורת האלוהים לא המילים שלנו שכנעו אתכם, אלא רוח הקודש הוא ששכנע אתכם ועזר לכם להאמין בבשורה בהתלהבות ובדבקות. גם אורח חיינו שימש הוכחה חותכת לאמיתות הבשורה שבישרנו לכם. 6וכך הלכתם בעקבותינו כשם שאנו הלכנו בעקבות האדון. למרות שאמונתכם בבשורה הביאה עליכם צרות וסבל מאויביכם, מילא אתכם רוח הקודש שמחה, 7ותוך זמן קצר הפכתם בעצמכם לדוגמה ועשיתם שם בין כל המאמינים ביוון. 8בינתיים פרסמתם את דבר־אלוהים בכל מקום, ואנו שומעים על אמונתכם הנפלאה באלוהים בכל מקום שאנו הולכים. לנו לא נותר מה לספר! 9אנשים מספרים לנו על קבלת־הפנים החמה שערכתם לנו, וכיצד עזבתם את האלילים והאמנתם באלוהים החי והאמיתי. 10הם גם סיפרו לנו על ציפייתכם לשובו של בן־האלוהים מהשמים, הלא הוא ישוע המשיח שקם לתחייה והושיענו מזעם אלוהים על החטא.