2 ተሰሎንቄ 1 – NASV & HHH

New Amharic Standard Version

2 ተሰሎንቄ 1:1-12

1ጳውሎስ፣ ሲላስና1፥1 ግሪኩ ሲልዋኑስ ይላል። ጢሞቴዎስ፤

በእግዚአብሔር በአባታችን በጌታም በኢየሱስ ክርስቶስ ለሆኑት፣ ለተሰሎንቄ ሰዎች ቤተ ክርስቲያን፤

2ከእግዚአብሔር አብ፣ ከጌታ ከኢየሱስ ክርስቶስም ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።

የምስጋናና የልመና ጸሎት

3ወንድሞች ሆይ፤ እምነታችሁ በየጊዜው እያደገ በመሄዱና የእርስ በርስ ፍቅራችሁም እየጨመረ በመምጣቱ፣ ስለ እናንተ እግዚአብሔርን ሁልጊዜ በሚገባ ማመስገን አለብን። 4ስለዚህ በደረሰባችሁ ስደትና መከራ ሁሉ በመጽናታችሁ፣ እኛ ራሳችን ስለ ትዕግሥታችሁና ስለ እምነታችሁ በእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ እንመካለን።

5ይህ ሁሉ የእግዚአብሔር ፍርድ ቅን መሆኑን የሚያመለክት ነው፤ ከዚህም የተነሣ መከራን ለምትቀበሉለት ለእግዚአብሔር መንግሥት የበቃችሁ ሆናችሁ ትቈጠራላችሁ። 6እግዚአብሔር ጻድቅ በመሆኑ መከራን ለሚያመጡባችሁ መከራን ይከፍላቸዋል፤ 7መከራን ለተቀበላችሁት ለእናንተም ሆነ ለእኛ ደግሞ ዕረፍት ይሰጠናል። ይህም የሚሆነው ጌታ ኢየሱስ በሚንበለበል እሳት ከኀያላን መላእክት ጋር ከሰማይ በሚገለጥበት ጊዜ ነው። 8በዚያ ጊዜ እግዚአብሔርን የማያውቁትንና ለጌታችንም ለኢየሱስ ወንጌል የማይታዘዙትን ይበቀላል። 9እነርሱም ከጌታ ፊትና ከኀይሉ ክብር ተወግደው በዘላለም ጥፋት ይቀጣሉ፤ 10የሚቀጡትም በቅዱሳኑ ዘንድ ሊከብርና በሚያምኑበትም ሁሉ ሊገረም በሚመጣበት በዚያን ቀን ይሆናል፤ እናንተም ከሚያምኑት መካከል ናችሁ፤ ምስክርነታችንን ተቀብላችኋልና።

11ይህን እያሰብን አምላካችን ለጥሪው የበቃችሁ አድርጎ እንዲቈጥራችሁ፣ መልካም ለማድረግ ያላችሁን ምኞትና ከእምነት የሆነውን ሥራችሁን ሁሉ በኀይሉ እንዲፈጽምላችሁ ዘወትር ስለ እናንተ እንጸልያለን። 12ደግሞም እንደ አምላካችንና1፥12 ወይም እንደ አምላካችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ መጠን የጌታችን የኢየሱስ ስም በእናንተ ዘንድ እንዲከብርና እናንተም በእርሱ እንድትከብሩ ይህን እንጸልያለን።

Habrit Hakhadasha/Haderekh

אגרת פולוס השנייה אל-התסלוניקים 1:1-12

1אל קהילת תסלוניקי השייכת לאלוהים אבינו ולישוע המשיח אדוננו.

מאת פולוס, סילוונוס וטימותיוס.

2שלום וברכה מאת האלוהים אבינו וישוע המשיח אדוננו.

3אחים יקרים, אנו מרגישים חובה נעימה להודות לאלוהים על שאמונתכם התחזקה מאוד, ועל שאהבתכם איש לרעהו גדלה כל־כך. 4אנחנו אף מתגאים בכם לפני הקהילות האחרות, כי הוכחתם מה חזק כוח־הסבל שלכם ומה איתנה אמונתכם באלוהים, למרות כל הרדיפות והצרות הבאות עליכם. 5אלוהים חפץ שתהיו ראויים למלכותו אשר למענה אתם סובלים, והוא יוכיח לכם שהוא שופט בצדק. 6כיצד הוא יוכיח לכם זאת? בהענישו את רודפיכם, 7ובהעניקו לכם, הנרדפים, רווחה והקלה יחד איתנו, כשישוע המשיח יופיע בשמים עם מלאכיו בלהבת־אש, 8כדי להעניש את אלה שסירבו להאמין באלוהים ובתוכניתו להושיעם באמצעות ישוע המשיח אדוננו. 9עונשם יהיה אבדון עולם – ניתוק מפני האדון ומהדרת כוחו, 10ביום שיבוא האדון להתכבד בקדושיו. אתם תהיו בין הקדושים האלה, כי האמנתם למה שסיפרנו לכם עליו.

11לפיכך אנו תמיד מתפללים שאלוהים יעשה אתכם ראויים לו, שימלא בגבורתו את כל משאלותיכם הטובות, ושיצליח את מעשיכם הנעשים מתוך אמונה בו, 12כדי ששם ישוע המשיח יהיה מפואר ומכובד באמצעותכם, וכדי שגם אתם תיקחו חלק בכבוד הזה, לפי מידת חסדו של אלוהינו ואדוננו ישוע המשיח.