1 ሳሙኤል 10 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

1 ሳሙኤል 10:1-27

1ከዚያም ሳሙኤል የዘይቱን ብርሌ ወስዶ፣ ዘይቱን በሳኦል ራስ ላይ ካፈሰሰ በኋላ እንዲህ ሲል ሳመው፤ “በርስቱ ላይ ገዥ ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር ቀብቶህ የለምን10፥1 የዕራይስጥ ቅጆች ከዚህ ጋር ይስማማሉ፤ የሰብዓ ሊቃናትና የቩልጌት ትርጕም ግን፣ የእግዚአብሔርን ሕዝብ ትገዛለህ ከከበቡት ጠላቶቹም እጅ ታድነዋለህ፤ እግዚአብሔር ለርስቱ ገዥ አድርጐ የሾመህ ምልክቱ ይህ ነው የሚለውን ይጨምራሉ።? 2ዛሬ ከእኔ ተለይተህ ስትሄድ፣ በብንያም ወሰን ላይ በምትገኘው ጼልጻህ በተባለች ስፍራ በራሔል መቃብር አጠገብ ሁለት ሰዎች ታገኛለህ። እነርሱም፣ ‘የምትፈልጋቸው አህዮች ተገኝተዋል፤ አሁን አባትህ ስለ አህዮቹ ማሰቡን ትቶ፣ “ስለ ልጄ ምን ባደርግ ይሻለኛል?” እያለ በመጨነቅ ላይ ነው’ ይሉሃል።

3“አንተም ጕዞህን በመቀጠል በታቦር እስካለው እስከ ትልቁ ዛፍ ድረስ ትሄዳለህ፤ እዚያም ሦስት ሰዎች፣ አንዱ ሦስት የፍየል ግልገል፣ ሌላው ሦስት ዳቦ፣ ሌላው ደግሞ የወይን ጠጅ የተሞላበት አቍማዳ ይዘው ወደ እግዚአብሔር ወደ ቤቴል ሲወጡ ያገኙሃል። 4እነርሱም ሰላም ይሉሃል፤ ሁለት ዳቦ ይሰጡሃል፤ አንተም ትቀበላቸዋለህ።

5“ከዚያ በኋላ የፍልስጥኤማውያን ጦር ወዳለበት ወደ እግዚአብሔር ተራራ ወደ ጊብዓ ትሄዳለህ። ወደ ከተማዪቱ እንደ ደረስህም የነቢያት ጉባኤ በመሰንቆ፣ በከበሮ፣ በእንቢልታና በበገና ታጅበው ትንቢት እየተናገሩ ከማምለኪያው ኰረብታ ላይ ሲወርዱ ታገኛቸዋለህ። 6የእግዚአብሔር መንፈስ በኀይል ይወርድብሃል፤ ከእነርሱ ጋር ትንቢት ትናገራለህ፤ እንደ ሌላ ሰውም ሆነህ ትለወጣለህ። 7እነዚህ ምልክቶች በተፈጸሙ ጊዜ እጅህ ማድረግ የምትችለውን ሁሉ አድርግ፤ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና።

8“ከፊቴ ቀድመህ ወደ ጌልገላ ውረድ፤ እኔም የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የኅብረት መሥዋዕቱን10፥8 በትውፊት የሰላም መሥዋዕት ይባላል። ለማቅረብ ወደ አንተ እመጣለሁ፤ ነገር ግን ወደ አንተ መጥቼ ምን ማድረግ እንዳለብህ እስክነግርህ ድረስ ሰባት ቀን መቈየት አለብህ።”

ሳኦል ነገሠ

9ሳኦል ከሳሙኤል ተለይቶ ለመሄድ ፊቱን በመለሰ ጊዜ፣ እግዚአብሔር የሳኦልን ልብ ለወጠው፤ ምልክቱም ሁሉ በዚያ ዕለት ተፈጸመ። 10ጊብዓ በደረሱ ጊዜ የነቢያቱ ጉባኤ አገኙት፤ የእግዚአብሔር መንፈስ በኀይል ወረደበት፤ ከእነርሱም ጋር ትንቢት ተናገረ። 11ቀድሞ የሚያውቁት ሁሉ ከነቢያቱ ጋር ትንቢት ሲናገር ባዩት ጊዜ፣ እርስ በርሳቸው፣ “የቂስን ልጅ ምን ነካው? ሳኦልም ከነቢያት ወገን ነውን?” ሲሉ ተጠያየቁ።

12በዚያ ነዋሪ የሆነ አንድ ሰው፣ “የእነርሱስ አባት ማን ነው?” ብሎ መለሰ። ስለዚህ፣ “ሳኦልም ከነቢያት ወገን ነውን?” የሚል ምሳሌያዊ አነጋገር ሆነ። 13ሳኦል ትንቢት መናገሩን ከፈጸመ በኋላ ወደ ማምለኪያው ኰረብታ ሄደ።

14በዚህ ጊዜ የሳኦል አጎት እርሱንና አገልጋዩን፣ “የት ነበራችሁ?” ሲል ጠየቃቸው።

እርሱም፣ “አህዮቹን ፍለጋ ሄደን ነበር፤ እንደማይገኙ በተረዳን ጊዜ ግን ወደ ሳሙኤል ሄድን” አለው።

15የሳኦል አጎትም፣ “እባክህ፣ ሳሙኤል ያለህን ንገረኝ” አለው።

16ሳኦልም መልሶ፣ “አህዮቹ መገኘታቸውን ገልጦ ነገረን” አለው። ይሁን እንጂ ስለ መንገሡ ሳሙኤል የነገረውን ለአጎቱ አልተናገረም።

17ሳሙኤል የእስራኤልን ሕዝብ ወደ ምጽጳ ወደ እግዚአብሔር ፊት ጠርቶ፣ 18እንዲህ አላቸው፤ “የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ ‘እስራኤልን ከግብፅ አወጣሁት፤ ከግብፃውያን እጅ ይጨቍኗችሁ ከነበሩት ከሌሎቹ መንግሥታት ሁሉ እጅ ታደግኋችሁ።’ 19ዛሬ ግን ከመከራችሁና ከጭንቃችሁ ሁሉ የሚያድናችሁን አምላካችሁን ንቃችሁ፤ ‘የለም፤ ንጉሥ አንግሥልን’ አላችሁ። ስለዚህ በየነገዳችሁና በየጐሣችሁ ሆናችሁ በእግዚአብሔር ፊት ቅረቡ።”

20ሳሙኤል የእስራኤልን ነገዶች ሁሉ ባቀረበ ጊዜ፣ የብንያም ነገድ ተመረጠ። 21ከዚያም የብንያምን ነገድ በየጐሣው ወደ ፊት አቀረበ፤ የማጥሪ ጐሣም ተመረጠ። በመጨረሻም የቂስ ልጅ ሳኦል ተመረጠ። እርሱ ግን ተፈልጎ አልተገኘም። 22ሰዎቹም፣ “ሰውየው መጥቷልን?” ሲሉ እግዚአብሔርን ጠየቁ።

እግዚአብሔርም፣ “አዎን፤ ነገር ግን በዕቃ መካከል ተሸሽጓል” አለ።

23እነርሱም ሮጠው ከተደበቀበት አመጡት፤ በሕዝቡ መካከል በቆመ ጊዜም ቁመቱ ከሌሎቹ ሁሉ ይልቅ ከትከሻው በላይ ዘለግ ያለ ነበር። 24ሳሙኤልም መላውን ሕዝብ፣ “እግዚአብሔር የመረጠውን ሰው አያችሁን? ከሕዝቡ ሁሉ የሚስተካከለው ማንም የለም” አለ።

ከዚያም ሕዝቡ፣ “ንጉሡ ለዘላለም ይኑር!” ብሎ ጮኸ።

25ሳሙኤልም ለንጉሥ የሚገባውን ወግና ሥርዐት ለሕዝቡ ገልጦ ካስረዳ በኋላ በመጽሐፍ ጽፎ በእግዚአብሔር ፊት አኖረው። ከዚህ በኋላ ሳሙኤል እያንዳንዱን ሰው ወደየቤቱ አሰናበተ።

26ሳኦልም ጊብዓ ወዳለው ቤቱ ሄደ፤ እግዚአብሔርም ልባቸውን የነካው ኀያላን ሰዎች አብረውት ሄዱ። 27አንዳንድ ምናምንቴ ሰዎች ግን፣ “እንዲህ ያለ ሰው እንዴት ሊያድነን ይችላል?” በማለት ናቁት፤ ስጦታም አላመጡለትም። ሳኦል ግን ዝም አለ።

Thai New Contemporary Bible

1ซามูเอล 10:1-27

1แล้วซามูเอลก็เทน้ำมันชโลมศีรษะของซาอูล จูบเขาและกล่าวว่า “องค์พระผู้เป็นเจ้าได้ทรงเจิมตั้งท่านให้เป็นผู้นำอิสราเอลประชากรของพระองค์ไม่ใช่หรือ?10:1 ฉบับ LXX. และ Vulg. ว่าเหนืออิสราเอลประชากรของพระองค์ไม่ใช่หรือ? ท่านจะครอบครองเหนือประชากรขององค์พระผู้เป็นเจ้า และช่วยพวกเขาให้รอดจากอำนาจของศัตรูที่อยู่แวดล้อม และนี่จะเป็นหมายสำคัญแก่ท่านว่าองค์พระผู้เป็นเจ้าได้เจิมตั้งท่านให้เป็นผู้นำเหนือกรรมสิทธิ์ของพระองค์ 2ในวันนี้เมื่อท่านจากเราไปแล้ว ท่านจะพบชายสองคนใกล้สุสานของราเชลที่เศลซาห์ชายแดนเบนยามิน เขาจะบอกท่านว่า ‘พบลาที่หายไปแล้ว และบิดาของท่านเลิกห่วงเรื่องลา แต่กังวลว่าท่านหายไปไหน เขาถามว่า “ข้าพเจ้าจะทำอย่างไรเกี่ยวกับลูกชายของข้าพเจ้า?” ’

3“แล้วท่านจะเดินทางต่อจากที่นั่นไปถึงต้นไม้ใหญ่แห่งทาโบร์ จะพบชายสามคนซึ่งกำลังจะไปเข้าเฝ้าพระเจ้าที่เบธเอล คนหนึ่งอุ้มลูกแพะสามตัว อีกคนหนึ่งถือขนมปังสามก้อน คนที่สามถือถุงหนังเหล้าองุ่นหนึ่งถุง 4เขาทั้งสามจะทักทายท่านและยื่นขนมปังให้ท่านสองก้อนซึ่งท่านจะรับไว้

5“หลังจากนั้นท่านจะไปถึงเมืองกิเบอาห์ของพระเจ้าซึ่งมีกองทหารรักษาการณ์ของพวกฟีลิสเตีย เมื่อท่านไปถึงจะพบขบวนผู้เผยพระวจนะลงมาจากสถานสูง เล่นพิณ รำมะนา เป่าขลุ่ย และดีดกระจับปี่ กล่าวคำทำนายมาตลอดทาง 6พระวิญญาณขององค์พระผู้เป็นเจ้าจะลงมาสวมทับท่านด้วยฤทธานุภาพ ท่านจะร่วมทำนายกับคนเหล่านั้น และท่านจะเปลี่ยนเป็นคนละคน 7เมื่อสำเร็จตามหมายสำคัญต่างๆ เหล่านี้แล้ว จงทำทุกสิ่งทุกอย่างที่เป็นภาระหน้าที่ของท่านเถิด เพราะพระเจ้าสถิตกับท่าน

8“จงล่วงหน้าไปที่กิลกาล คอยข้าพเจ้าอยู่เจ็ดวัน ข้าพเจ้าจะไปหาท่านแน่นอน เพื่อถวายเครื่องเผาบูชาและเครื่องสันติบูชา เมื่อข้าพเจ้าไปถึงที่นั่นแล้ว ข้าพเจ้าจะบอกท่านว่าท่านควรทำอะไรบ้าง”

ซาอูลขึ้นเป็นกษัตริย์

9ขณะที่ซาอูลหันหลังไปจากซามูเอล พระเจ้าทรงเปลี่ยนแปลงจิตใจของซาอูล และหมายสำคัญทั้งปวงก็เป็นจริงในวันนั้น 10เมื่อซาอูลกับคนรับใช้มาถึงกิเบอาห์ ก็พบขบวนผู้เผยพระวจนะ พระวิญญาณของพระเจ้าลงมาเหนือซาอูลด้วยฤทธานุภาพ และเขาก็ร่วมทำนาย 11เมื่อคนทั้งปวงที่เคยรู้จักซาอูลมาก่อน เห็นเขาทำนายร่วมกับบรรดาผู้เผยพระวจนะก็ถามกันว่า “เกิดอะไรขึ้นกับบุตรชายของคีช? ซาอูลเป็นผู้เผยพระวจนะกับเขาด้วยหรือ?”

12ชายคนหนึ่งซึ่งอาศัยอยู่ที่นั่นถามกลับว่า “แล้วคนเหล่านี้เป็นลูกของใคร?” เหตุการณ์นี้จึงเป็นที่มาของคำกล่าวที่ว่า “ซาอูลเป็นผู้เผยพระวจนะกับเขาด้วยหรือ?” 13เมื่อซาอูลกล่าวคำทำนายเสร็จแล้วก็ขึ้นไปยังสถานสูง

14ลุงของซาอูลถามเขาและคนรับใช้ของเขาว่า “เจ้าไปไหนมา?”

ซาอูลตอบว่า “พวกข้าพเจ้าไปตามหาลา แต่ไม่พบ จึงไปหาซามูเอล”

15ลุงของซาอูลกล่าวว่า “เล่าให้ฟังซิว่าซามูเอลพูดอะไรกับเจ้าบ้าง”

16ซาอูลตอบว่า “เขายืนยันว่าพบลาแล้ว” แต่ซาอูลไม่ได้บอกลุงว่าซามูเอลได้เจิมตั้งตนเป็นกษัตริย์

17ซามูเอลได้เรียกชุมนุมชาวอิสราเอลมาเข้าเฝ้าองค์พระผู้เป็นเจ้าที่มิสปาห์ 18และกล่าวกับพวกเขาว่า “พระยาห์เวห์พระเจ้าแห่งอิสราเอลตรัสว่า ‘เราได้นำอิสราเอลออกมาจากอียิปต์ และกอบกู้พวกเจ้าจากอำนาจของอียิปต์และอาณาจักรทั้งปวงที่กดขี่ข่มเหงเจ้า’ 19แต่บัดนี้ท่านทอดทิ้งพระเจ้าของท่าน ผู้ทรงช่วยท่านจากภัยพิบัติและความทุกข์ยากทั้งปวง และพวกท่านกล่าวว่า ‘ขอให้ตั้งกษัตริย์ปกครองเรา’ ฉะนั้นจงแสดงตัวต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าทีละเผ่าทีละตระกูล”

20เมื่อซามูเอลนำทุกเผ่าของอิสราเอลเข้ามาใกล้ ก็เลือกได้เผ่าเบนยามิน 21จากนั้นซามูเอลนำแต่ละตระกูลในเผ่าเบนยามินมา ก็เลือกได้ตระกูลมัตรี และในที่สุดเลือกได้ซาอูลบุตรของคีช แต่เมื่อเขามองหาซาอูลก็ไม่พบ 22คนเหล่านั้นจึงทูลถามองค์พระผู้เป็นเจ้าว่า “เขามาถึงที่นี่แล้วหรือยัง?”

องค์พระผู้เป็นเจ้าตรัสว่า “มาแล้ว เขาซ่อนตัวอยู่ในกองสัมภาระ”

23พวกเขาจึงวิ่งไปนำตัวเขาออกมา ขณะเขายืนอยู่ในหมู่ชนก็สูงกว่าคนอื่นๆ ทั้งหมดหนึ่งช่วงศีรษะ 24ซามูเอลกล่าวแก่ประชากรทั้งปวงว่า “ท่านเห็นคนที่องค์พระผู้เป็นเจ้าทรงเลือกสรรหรือไม่? ไม่มีผู้ใดเหมือนเขาอีกแล้วในหมู่ประชากร”

แล้วประชากรทั้งปวงโห่ร้องว่า “ขอกษัตริย์จงทรงพระเจริญ!”

25ซามูเอลชี้แจงแก่ประชากรเรื่องกฎระเบียบของการเป็นกษัตริย์ เขาบันทึกกฎเหล่านั้นลงในหนังสือม้วนและเก็บรักษาไว้ต่อหน้าองค์พระผู้เป็นเจ้าแล้วซามูเอลก็ให้คนทั้งหลายกลับบ้าน

26เมื่อซาอูลกลับไปยังบ้านของเขาที่กิเบอาห์ก็มีนักรบแกล้วกล้าที่พระเจ้าทรงดลใจไปกับเขาด้วย 27แต่มีอันธพาลบางคนพูดว่า “คนนี้จะมาช่วยพวกเราให้รอดได้อย่างไร?” เขาเหล่านี้ดูถูกซาอูลและไม่ยอมนำของกำนัลมาให้ แต่ซาอูลนิ่งเงียบ