ገላትያ 1 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ገላትያ 1:1-24

1ከሰዎች ወይም በሰው ከተላከው ሳይሆን፣ በኢየሱስ ክርስቶስና ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አብ ሐዋርያ ከሆነው ከጳውሎስ፤ 2አብረውኝም ካሉት ወንድሞች ሁሉ፤

በገላትያ ላሉት አብያተ ክርስቲያናት፤

3ከአባታችን ከእግዚአብሔር፣ ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን። 4እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ፣ ከዚህ ክፉ ዓለም ያድነን ዘንድ ስለ ኀጢአታችን ራሱን ሰጠ፤ 5ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ክብር ይሁን፤ አሜን።

ወንጌል አንዲት ናት

6በክርስቶስ ጸጋ የጠራችሁን እርሱን ትታችሁ፣ ወደ ተለየ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ መዞራችሁ ደንቆኛል፤ 7እንደ እውነቱ ከሆነ ሌላ ወንጌል የለም። የሚያደነጋግሯችሁና የክርስቶስን ወንጌል ለማጣመም ጥረት የሚያደርጉ አንዳንድ ሰዎች አሉ። 8ነገር ግን እኛም ብንሆን ወይም የሰማይ መልአክ፣ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የተለየ ወንጌል ቢሰብክላችሁ እርሱ ለዘላለም የተረገመ ይሁን። 9ቀደም ብለን እንዳልነው፣ አሁንም ደግሜ እላለሁ፤ ማንም ከተቀበላችሁት ሌላ የተለየ ወንጌል ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።

10አሁን እኔ ጐሽ ለመባል የምሻው በሰዎች ዘንድ ነው ወይስ በእግዚአብሔር ዘንድ? ወይስ ሰዎችን ደስ ለማሰኘት እየተጣጣርሁ ነው? ሰዎችን ደስ ለማሰኘት የምጥር ብሆን ኖሮ፣ የክርስቶስ አገልጋይ ባልሆንሁ ነበር።

ጳውሎስ በእግዚአብሔር መጠራቱ

11ወንድሞች ሆይ፤ የሰበክሁላችሁ ወንጌል ሰው ሠራሽ አለመሆኑን እንድታውቁ እፈልጋለሁ፤ 12ከማንም ሰው አልተቀበልሁትም፤ ከማንም አልተማርሁትም፤ ይልቁንስ በመገለጥ ከኢየሱስ ክርስቶስ ተቀበልሁት።

13ቀድሞ በአይሁድ ሃይማኖት እንዴት እንደ ኖርሁ፣ የእግዚአብሔርንም ቤተ ክርስቲያን እንዴት በእጅጉ እንዳሳደድሁ፣ ለማጥፋትም እንዴት እንደ ጣርሁ ሰምታችኋል። 14በእኔ ዕድሜ ዘመን ከነበሩት ከብዙዎቹ አይሁድ ይበልጥ በአይሁድ ሃይማኖት እልቅ ነበር፤ ስለ አባቶቼም ወግ እጅግ ቀናተኛ ነበርሁ። 15ነገር ግን፣ ከእናቴ ማሕፀን1፥15 ወይም ከመወለዴ ጀምሮ የለየኝና በጸጋው የጠራኝ እግዚአብሔር፣ 16በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ እንድሰብክ ልጁን በእኔ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፣ ከማንም ሥጋ ለባሽ ጋር አልተማከርሁም፤ 17ከእኔ በፊት ሐዋርያት ወደሆኑትም ወደ ኢየሩሳሌም አልወጣሁም፤ ነገር ግን ወዲያው ወደ ዐረብ አገር ሄድሁ፤ በኋላም ወደ ደማስቆ ተመለስሁ።

18ከዚያም ከሦስት ዓመት በኋላ፣ ጴጥሮስን1፥18 ግሪኩ ኬፋ ይለዋል። አገኘው ዘንድ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣሁ፤ ከእርሱም ጋር ዐሥራ አምስት ቀን ተቀመጥሁ። 19ነገር ግን ከጌታ ወንድም ከያዕቆብ በቀር፣ ከሐዋርያት ማንንም አላየሁም። 20በምጽፍላችሁ ነገር በእግዚአብሔር ፊት ሐሰት እንደማልናገር አስረግጬ እነግራችኋለሁ። 21ከዚያም በኋላ፣ ወደ ሶርያና ወደ ኪልቅያ አገር ሄድሁ። 22በክርስቶስ ያሉት የይሁዳ አብያተ ክርስቲያናትም ፊቴን አይተው አያውቁም ነበር፤ 23እነርሱ ግን፣ “ቀድሞ እኛን ሲያሳድድ የነበረ ሰው፣ ከዚህ በፊት ሊያጠፋው ይፈልግ የነበረውን እምነት አሁን እየሰበከ ነው” የሚለውን ወሬ ብቻ ሰምተው ነበር፤ 24በእኔም ምክንያት እግዚአብሔርን አመሰገኑ።

Thai New Contemporary Bible

กาลาเทีย 1:1-24

1จดหมายฉบับนี้จากข้าพเจ้าเปาโลผู้เป็นอัครทูต ข้าพเจ้าไม่ได้ถูกส่งมาจากมนุษย์หรือโดยมนุษย์ แต่โดยพระเยซูคริสต์และพระเจ้าพระบิดาผู้ทรงให้พระองค์เป็นขึ้นจากตาย 2และบรรดาพี่น้องที่อยู่กับข้าพเจ้า

ถึงคริสตจักรต่างๆ ในแคว้นกาลาเทีย

3ขอพระคุณและสันติสุขจากพระเจ้าพระบิดาของเราและจากองค์พระเยซูคริสต์เจ้ามีแก่ท่านทั้งหลาย 4พระเยซูทรงสละพระองค์เองเพื่อบาปของเราทั้งหลาย ทั้งนี้เพื่อช่วยเราจากยุคอันชั่วร้ายนี้ตามพระประสงค์ของพระเจ้าและพระบิดาของเรา 5ขอถวายพระเกียรติสิริแด่พระองค์สืบๆ ไปเป็นนิตย์ อาเมน

ไม่มีข่าวประเสริฐอื่น

6ข้าพเจ้าประหลาดใจที่ท่านทั้งหลายทิ้งพระองค์ผู้ทรงเรียกท่านโดยพระคุณของพระคริสต์ไปอย่างรวดเร็ว และหันไปหาข่าวประเสริฐอื่น 7ซึ่งไม่ใช่ข่าวประเสริฐเลย เห็นได้ชัดว่าบางคนกำลังทำให้ท่านสับสนวุ่นวายและพยายามบิดเบือนข่าวประเสริฐของพระคริสต์ 8ไม่ว่าเราหรือทูตสวรรค์ หากประกาศข่าวประเสริฐอื่นซึ่งต่างจากข่าวประเสริฐที่เราได้ประกาศแก่ท่าน ขอให้ผู้นั้นถูกสาปแช่งชั่วนิรันดร์! 9ดังที่เราได้บอกไว้แล้ว บัดนี้ข้าพเจ้าขอกล่าวย้ำอีกครั้งว่าหากใครประกาศข่าวประเสริฐอื่นแก่ท่านนอกเหนือจากที่ท่านได้รับไว้แล้ว ขอให้ผู้นั้นถูกสาปแช่งชั่วนิรันดร์!

10นี่ข้าพเจ้ากำลังมุ่งให้มนุษย์หรือพระเจ้ายอมรับกันแน่? หรือว่าข้าพเจ้ากำลังพยายามทำให้มนุษย์พอใจ? หากข้าพเจ้ากำลังพยายามทำให้มนุษย์พอใจ ข้าพเจ้าก็ไม่ใช่ผู้รับใช้ของพระคริสต์

พระเจ้าทรงเรียกเปาโล

11พี่น้องทั้งหลาย ข้าพเจ้าอยากให้ท่านทราบว่าข่าวประเสริฐที่ข้าพเจ้าประกาศนั้นไม่ใช่เรื่องที่มนุษย์แต่งขึ้น 12ข้าพเจ้าไม่ได้รับข่าวประเสริฐนี้จากมนุษย์คนใดหรือมีคนมาสอน แต่รับการทรงสำแดงจากพระเยซูคริสต์

13ในเมื่อท่านก็ทราบว่าเมื่อก่อนขณะยังถือศาสนายิวข้าพเจ้าใช้ชีวิตอย่างไร ข้าพเจ้าได้ข่มเหงคริสตจักรของพระเจ้าอย่างรุนแรงและพยายามจะทำลายให้สิ้น 14เมื่ออยู่ในศาสนายิวข้าพเจ้าก้าวหน้ากว่าพี่น้องยิวหลายคนในรุ่นเดียวกัน และหัวรุนแรงอย่างยิ่งในการยึดถือประเพณีตามบรรพบุรุษของข้าพเจ้า 15แต่เมื่อพระเจ้าทรงเลือกข้าพเจ้าไว้ตั้งแต่กำเนิด1:15 หรืออยู่ในครรภ์มารดา และทรงเรียกข้าพเจ้าโดยพระคุณของพระองค์ พระองค์พอพระทัย 16ที่จะสำแดงพระบุตรของพระองค์ในข้าพเจ้า เพื่อให้ข้าพเจ้าประกาศพระบุตรนั้นท่ามกลางชาวต่างชาติ ข้าพเจ้าก็ไม่ได้ปรึกษามนุษย์คนใด 17ทั้งไม่ได้ขึ้นไปยังกรุงเยรูซาเล็มเพื่อพบบรรดาคนที่เป็นอัครทูตก่อนข้าพเจ้า แต่ข้าพเจ้าตรงไปยังประเทศอาระเบียทันที และภายหลังได้กลับมายังเมืองดามัสกัส

18สามปีต่อมาข้าพเจ้าขึ้นไปกรุงเยรูซาเล็มเพื่อทำความรู้จักกับเปโตร1:18 ภาษากรีกว่าเคฟาส และพักอยู่กับเขาสิบห้าวัน 19ข้าพเจ้าไม่ได้พบอัครทูตคนอื่นๆ เลยนอกจากยากอบน้องขององค์พระผู้เป็นเจ้า 20ข้าพเจ้าขอยืนยันต่อหน้าพระเจ้าว่าที่เขียนมานี้ไม่ได้โกหก 21หลังจากนั้นข้าพเจ้าไปยังเขตแดนซีเรียและซิลีเซีย 22คริสตจักรต่างๆ ในพระคริสต์ที่แคว้นยูเดียไม่รู้จักข้าพเจ้าเป็นการส่วนตัว 23พวกเขาเพียงแต่ได้ข่าวว่า “คนที่แต่ก่อนเคยข่มเหงเราเดี๋ยวนี้ประกาศความเชื่อซึ่งครั้งหนึ่งเขาเคยพยายามทำลาย” 24และพวกเขาสรรเสริญพระเจ้าเนื่องด้วยข้าพเจ้า