ገላትያ 2 – NASV & TNCV

New Amharic Standard Version

ገላትያ 2:1-21

ጳውሎስን ሐዋርያት ተቀበሉት

1ከዐሥራ አራት ዓመት በኋላም፣ ዳግመኛ ወደ ኢየሩሳሌም ወጣሁ፤ በዚህ ጊዜ ከበርናባስ ጋር ነበርሁ፤ ቲቶንም ይዤው ሄጄ ነበር። 2ካገኘሁትም መገለጥ የተነሣ ወደዚያ ሄድሁ፤ በአሕዛብ መካከል የምሰብከውን ወንጌል ለእነርሱም ገለጥሁላቸው። ይሁን እንጂ፣ ምናልባት በከንቱ እየሮጥሁ ወይም ሮጬ እንዳይሆን በመሥጋት፣ ዋነኞች ለሚመስሉት ብቻ በግል ይህን አስታወቅኋቸው። 3ከእኔ ጋር የነበረው ቲቶ እንኳ የግሪክ ሰው ቢሆንም፣ እንዲገረዝ አልተገደደም ነበር። 4ይህ ጕዳይ የተነሣው አንዳንድ ሐሰተኞች ወንድሞች በክርስቶስ ኢየሱስ ያገኘነውን ነጻነት ሊሰልሉና ባሪያዎች ሊያደርጉን ወደ እኛ ሾልከው በመግባታቸው ነው።

5ለእነዚህ ሰዎች ለአንድ አፍታ እንኳ አልተገዛንላቸውም፤ ይኸውም፣ የወንጌል እውነት ከእናንተ ጋር ጸንቶ እንዲኖር ነው።

6ዋነኛ መስለው ስለሚታዩት ሰዎች ማንነት እኔን አይገደኝም፤ እግዚአብሔር የሰውን ፊት አይቶ አያደላም፤ እነዚህም ሰዎች ለመልእክቴ የጨመሩልኝ ነገር የለም። 7ነገር ግን ጴጥሮስ ለተገረዙት2፥7 ወይም ለአይሁድ ወንጌልን እንዲሰብክ ዐደራ እንደ ተሰጠው፣ እኔም ላልተገረዙት2፥7 ወይም ለአረማዊያን እንዲሁም 8 እና 9 ይመ ወንጌልን እንድሰብክ ዐደራ እንደ ተሰጠኝ ተገነዘቡ፤ 8ጴጥሮስን ለአይሁድ ሐዋርያ እንዲሆን የሠራ እግዚአብሔር፣ በእኔ የአሕዛብ ሐዋርያዊ አገልግሎትም ሠርቷል። 9እንደ አዕማድ የሚቈጠሩት ያዕቆብ፣ ጴጥሮስና2፥9 ግሪኩ ኬፋ ይላል፤ እንዲሁም 11 እና 14 ይመ ዮሐንስም የተሰጠኝን ጸጋ ባስተዋሉ ጊዜ፣ ለእኔና ለበርናባስ የትብብር ቀኝ እጃቸውን ሰጡን፤ ከዚያም እኛ ወደ አሕዛብ፣ እነርሱ ደግሞ ወደ አይሁድ እንድንሄድ ተስማሙ። 10አጥብቀው ዐደራ ያሉን ድኾችን ማሰባችንን እንዳናቋርጥ ብቻ ነው፤ እኔም ይህንኑ ለማድረግ ጓጕቼ ነበር።

ጳውሎስ ጴጥሮስን ተቃወመው

11ጴጥሮስ ወደ አንጾኪያ በመጣ ጊዜ በግልጥ ስቶ ስለ ነበር፣ ፊት ለፊት ተቃወምሁት። 12አንዳንድ ሰዎች ከያዕቆብ ዘንድ ከመምጣታቸው በፊት፣ ከአሕዛብ ጋር ይበላ ነበር፤ እነርሱ በመጡ ጊዜ ግን፣ የተገረዙትን ወገኖች ፈርቶ ከአሕዛብ ራሱን በመለየት ገሸሽ ማለት ጀመረ፤ 13በርናባስም እንኳ በእነርሱ ግብዝነት እስኪወሰድ ድረስ፣ ሌሎቹም አይሁድ በግብዝነቱ ተባበሩት።

14ተግባራቸው እንደ ወንጌል እውነት አለመሆኑን በተረዳሁ ጊዜ፣ በሁሉም ፊት ጴጥሮስን እንዲህ አልሁት፤ “አንተ አይሁዳዊ ነህ፤ ሆኖም በአሕዛብ ሥርዐት እንጂ በአይሁድ ሥርዐት አትኖርም፤ ታዲያ አሕዛብ የአይሁድን ሥርዐት እንዲከተሉ እንዴት ታስገድዳቸዋለህ?

15“እኛ በትውልዳችን አይሁድ እንጂ፣ ‘ኀጢአተኞች አሕዛብ’ ያልሆንን፣ 16ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን እንጂ፣ ሕግን በመጠበቅ እንደማይጸድቅ እናውቃለን። ስለዚህ ሕግን በመጠበቅ ሳይሆን፣ በክርስቶስ በማመን እንጸድቅ ዘንድ እኛም ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነናል፤ ሕግን በመጠበቅ ማንም አይጸድቅምና።

17“በክርስቶስ ለመጽደቅ ስንፈልግ፣ እኛ ራሳችን ኀጢአተኞች መሆናችን ግልጽ ነው፤ ታዲያ ክርስቶስ ኀጢአት እንዲስፋፋ ያደርጋልን? ፈጽሞ አይደለም! 18ያፈረስሁትን መልሼ የምገነባ ከሆነማ፣ ሕግ ተላላፊ መሆኔን አረጋግጣለሁ። 19ለእግዚአብሔር እኖር ዘንድ በሕግ በኩል ለሕግ ሞቻለሁና። 20ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ፤ ከእንግዲህ እኔ አልኖርም፤ ነገር ግን ክርስቶስ በውስጤ ይኖራል። አሁንም በሥጋ የምኖረው ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን አሳልፎ በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለኝ እምነት ነው። 21የእግዚአብሔርን ጸጋ አላቃልልም፤ ጽድቅ በሕግ በኩል የሚገኝ ከሆነማ፣ ክርስቶስ እንዲያው በከንቱ ሞተ ማለት ነዋ!”2፥21 አንዳንድ ተርጓሚዎች ትምህርተ ጥቅሱን ከ14 በኋላ ያደርጋሉ።

Thai New Contemporary Bible

กาลาเทีย 2:1-21

เหล่าอัครทูตยอมรับเปาโล

1สิบสี่ปีต่อมาข้าพเจ้าไปที่กรุงเยรูซาเล็มอีกพร้อมกับบารนาบัส ข้าพเจ้าพาทิตัสไปด้วย 2ข้าพเจ้าไปตามการทรงสำแดง และได้ชี้แจงข่าวประเสริฐที่ข้าพเจ้าประกาศแก่คนต่างชาติให้พวกเขาฟัง แต่ข้าพเจ้าก็ได้ชี้แจงเป็นการส่วนตัวให้บรรดาผู้ที่ดูเหมือนว่าเป็นผู้นำฟัง เนื่องจากเกรงว่าที่ข้าพเจ้ากำลังวิ่งแข่งหรือได้วิ่งแข่งไปแล้วจะเปล่าประโยชน์ 3แต่กระนั้นทิตัสซึ่งอยู่กับข้าพเจ้า แม้เขาจะเป็นกรีกก็ไม่ถูกบังคับให้เข้าสุหนัต 4เรื่องนี้ลุกลามขึ้นมาเพราะพี่น้องจอมปลอมบางคนที่แทรกซึมเข้ามาในหมู่เรา เพื่อสืบดูเสรีภาพที่เรามีในพระเยซูคริสต์และเพื่อจะทำให้เราเป็นทาส 5แต่เราไม่อ่อนข้อให้เขาแม้สักขณะหนึ่ง เพื่อความจริงของข่าวประเสริฐจะได้คงอยู่กับท่าน

6สำหรับบรรดาผู้ที่ดูเหมือนว่าเป็นคนสำคัญ ซึ่งเขาจะเป็นอย่างไรนั้นไม่มีความหมายอะไรสำหรับข้าพเจ้า พระเจ้าไม่ได้ทรงพิจารณาที่รูปลักษณ์ภายนอก พวกเขาไม่ได้เพิ่มเติมอะไรแก่ถ้อยคำที่ข้าพเจ้าได้กล่าวไว้เลย 7ตรงกันข้ามเขาเห็นว่าข้าพเจ้าได้รับมอบหมายภารกิจในการประกาศข่าวประเสริฐแก่คนต่างชาติ2:7 ภาษากรีกว่าคนที่ไม่ได้เข้าสุหนัตเช่นเดียวกับที่เปโตรประกาศแก่คนยิว2:7 ภาษากรีกว่าคนที่เข้าสุหนัตแล้วเช่นเดียวกับข้อ 8 และ 9 8เพราะพระเจ้าผู้ทรงดำเนินการในพันธกิจของเปโตรผู้เป็นอัครทูตไปยังคนยิวก็ทรงดำเนินการในพันธกิจของข้าพเจ้าผู้เป็นอัครทูตไปยังคนต่างชาติด้วย 9เมื่อยากอบ เปโตร2:9 ภาษากรีกว่าเคฟาสเช่นเดียวกับข้อ 11 และ 14และยอห์นซึ่งได้ชื่อว่าเป็นเสาหลักเห็นถึงพระคุณที่ทรงมีต่อข้าพเจ้า ก็จับมือขวาของข้าพเจ้ากับบารนาบัสเพื่อแสดงว่าเราร่วมงานกัน เขาเหล่านี้เห็นด้วยว่าเราควรไปยังคนต่างชาติ ส่วนพวกเขาไปหาคนยิว 10เขาทั้งสามขอแต่เพียงให้เราคิดถึงคนจนเสมอ ซึ่งเป็นสิ่งที่ข้าพเจ้ากระตือรือร้นที่จะทำอยู่แล้ว

เปาโลคัดค้านเปโตร

11เมื่อเปโตรมาที่อันทิโอก ข้าพเจ้าคัดค้านเขาซึ่งๆ หน้าเนื่องจากเขาได้ทำผิดอย่างชัดเจน 12คือก่อนที่คนของยากอบบางคนจะมาถึง เปโตรเคยร่วมรับประทานอาหารกับคนต่างชาติเสมอ แต่เมื่อพวกนั้นมาถึง เขาก็ถอยห่างและปลีกตัวจากคนต่างชาติเพราะกลัวพวกที่เข้าสุหนัต 13ชาวยิวอื่นๆ พลอยหน้าซื่อใจคดไปกับเขาด้วย และด้วยความหน้าซื่อใจคดของพวกเขา แม้บารนาบัสเองก็ยังถูกชักจูงให้หลงทำตามด้วย

14เมื่อข้าพเจ้าเห็นพวกเขาทำตัวไม่สอดคล้องกับความจริงของข่าวประเสริฐ ข้าพเจ้าจึงพูดกับเปโตรต่อหน้าพวกเขาทั้งปวงว่า “ท่านเป็นยิวยังใช้ชีวิตเหมือนคนต่างชาติ ไม่เหมือนชาวยิว แล้วทำไมจึงบังคับคนต่างชาติให้ถือธรรมเนียมยิวเล่า?

15“เราซึ่งเป็นคนยิวโดยกำเนิด ไม่ใช่ ‘คนบาปต่างชาติ’ 16ยังรู้ว่าไม่มีใครถูกนับเป็นผู้ชอบธรรมได้โดยการถือรักษาบทบัญญัติ แต่เป็นได้โดยความเชื่อในพระเยซูคริสต์ ฉะนั้นเราเองจึงเชื่อในพระเยซูคริสต์เพื่อจะได้ถูกนับเป็นผู้ชอบธรรมโดยความเชื่อในพระคริสต์ ไม่ใช่โดยการทำตามบทบัญญัติ เพราะว่าไม่มีใครถูกนับเป็นผู้ชอบธรรมได้โดยการทำตามบทบัญญัติเลย

17“ถ้าขณะที่เรามุ่งจะให้พระเจ้าทรงนับเราเป็นผู้ชอบธรรมในพระคริสต์ ก็ปรากฏชัดว่าเราเองเป็นคนบาป นั่นหมายความว่าพระคริสต์ส่งเสริมบาปหรือ? ไม่ใช่อย่างนั้นแน่นอน! 18หากข้าพเจ้าสร้างสิ่งที่ข้าพเจ้าได้ทำลายลงแล้วขึ้นใหม่ ก็แสดงว่าข้าพเจ้าเป็นคนละเมิดบทบัญญัติ 19เพราะโดยทางบทบัญญัติข้าพเจ้าได้ตายต่อบทบัญญัติแล้ว เพื่อว่าจะได้มีชีวิตอยู่เพื่อพระเจ้า 20ข้าพเจ้าถูกตรึงไว้กับพระคริสต์แล้ว ข้าพเจ้าจึงไม่มีชีวิตอยู่ต่อไป พระคริสต์ต่างหากทรงมีชีวิตอยู่ในข้าพเจ้า ชีวิตที่ข้าพเจ้าดำเนินอยู่ในกายนี้ ข้าพเจ้าดำเนินด้วยความเชื่อในพระบุตรของพระเจ้าผู้ทรงรักข้าพเจ้าและประทานพระองค์เองเพื่อข้าพเจ้า 21ข้าพเจ้าไม่ได้ปัดพระคุณของพระเจ้าทิ้ง เพราะถ้าความชอบธรรมสามารถได้มาโดยทางบทบัญญัติ พระคริสต์ก็วายพระชนม์โดยเปล่าประโยชน์!”2:21 ผู้แปลบางคนปิดเครื่องหมายคำพูดหลังข้อ 14