ዳንኤል 8 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ዳንኤል 8:1-27

ዳንኤል በራእዩ ያየው አውራ በግና ፍየል

1ንጉሥ ቤልሻዛር በነገሠ በሦስተኛው ዓመት፣ አስቀድሞ ከተገለጠልኝ ራእይ በኋላ እኔ ዳንኤል ሌላ ራእይ አየሁ። 2በራእዩም፣ በኤላም አውራጃ በሱሳ ግንብ ራሴን አየሁት፤ በራእዩም በኡባል ወንዝ አጠገብ ነበርሁ። 3ዐይኔን አንሥቼ ስመለከት እነሆ፤ ሁለት ቀንዶች ያሉት አውራ በግ በወንዙ አጠገብ ቆሞ አየሁ፤ ቀንዶቹም ረዣዥሞች ነበሩ፤ ከቀንዶቹም አንዱ ከሌላው ይረዝማል፤ የበቀለው ግን ዘግይቶ ነበር። 4አውራ በጉም ወደ ምዕራብ፣ ወደ ሰሜንና ወደ ደቡብ በቀንዱ ሲጐሽም አየሁ። ምንም ዐይነት እንስሳ ሊቋቋመው አልቻለም፤ ከእጁም ሊያድን የሚችል አልነበረም፤ የፈለገውን ሁሉ አደረገ፤ ታላቅም ሆነ።

5ስለዚህም ነገር እያሰብሁ ሳለሁ፣ በዐይኖቹ መካከል ትልቅ ቀንድ ያለው አውራ ፍየል፣ መሬት ሳይነካ ምድርን ሁሉ እያቋረጠ በድንገት ከምዕራብ መጣ። 6በወንዙ አጠገብ ቆሞ ወዳየሁት፣ ሁለት ቀንድ ወዳለው አውራ በግ ተንደርድሮ መጣበት፤ በታላቅ ቍጣም መታው፤ 7እየወጋውና ሁለቱን ቀንዶቹን እየሰበረ፣ በጭካኔ አውራውን በግ ሲጐዳ አየሁ፤ አውራ በጉም ለመቋቋም ጕልበት አልነበረውም። ፍየሉ በምድር ላይ ጥሎ ረገጠው፤ አውራ በጉንም ከፍየሉ እጅ ለማዳን የሚችል አልነበረም። 8ፍየሉም ታላቅ ሆነ፤ ነገር ግን በኀይሉ በበረታ ጊዜ፣ ትልቁ ቀንዱ ተሰበረ፤ በቦታውም ወደ አራቱ የሰማይ ነፋሳት የሚያመለክቱ አራት ታላላቅ ቀንዶች በቀሉ።

9ከእነዚህም ቀንዶች መካከል በአንዱ ላይ አንድ ሌላ ትንሽ ቀንድ በቀለ፤ ወደ ደቡብ፣ ወደ ምሥራቅና ወደ መልካሚቱ ምድር በኀይል አደገ። 10ወደ ሰማይ ሰራዊት እስኪደርስ ድረስ አደገ፤ ከከዋክብት ሰራዊትም የተወሰኑትን ወደ ምድር ጣለ፤ ረጋገጣቸውም። 11ከሰማይ ሰራዊት አለቃ ጋር እስኪተካከል ድረስ ራሱን ከፍ ከፍ አደረገ፤ የልዑሉንም የዘወትር መሥዋዕት ወሰደበት፤ የመቅደሱንም ስፍራ አረከሰ። 12ከዐመፅ የተነሣም የቅዱሳን ሰራዊት8፥12 ወይም ከዐመፅ…ሰራዊቱ ከዘወትሩ መሥዋዕት ጋር ለእርሱ ዐልፎ ተሰጠ፤ የሚያደርገው ሁሉ ተከናወነለት፤ እውነትም ወደ ምድር ተጣለች።

13ከቅዱሳኑም አንዱ ሲናገር ሰማሁ፤ ሌላውም ቅዱስ እንዲህ አለው፤ “ስለ ዘወትሩ መሥዋዕት፣ ለጥፋት ምክንያት ስለ ሆነው ዐመፅ፣ ከእግር በታች እንዲረገጡ ዐልፈው ስለሚሰጡት መቅደስና ሰራዊት የታየው ራእይ የሚፈጸመው መቼ ነው?”

14እርሱም፣ “እስከ ሁለት ሺሕ ሦስት መቶ ምሽቶችና ማለዳዎች ድረስ ይቈያል፤ ከዚያም መቅደሱ እንደ ገና ይነጻል” አለኝ።

የራእዩ ትርጓሜ

15እኔ ዳንኤል ራእዩን ስመለከትና ሳስተውል ሳለ፣ ሰውን የሚመስል ከፊት ለፊቴ ቆመ፤ 16ከኡባልም፣ “ገብርኤል ሆይ፤ ለዚህ ሰው የራእዩን ትርጕም ንገረው” ብሎ የሚጮኽ የሰው ድምፅ ሰማሁ።

17እኔ ወደ ቆምሁበት ስፍራ እየቀረበ ሲመጣ፣ ደንግጬ በግምባሬ ተደፋሁ፤ እርሱም፣ “የሰው ልጅ ሆይ፤ ራእዩ ስለ ዘመኑ ፍጻሜ እንደ ሆነ አስተውል” አለኝ።

18እየተናገረኝ ሳለ፣ በምድር ላይ በግንባሬ ተደፋሁ፤ በከባድ እንቅልፍም ተዋጥሁ፤ እርሱ ግን ዳሰሰኝና በእግሮቼ አቆመኝ።

19እርሱም እንዲህ አለኝ፤ “ራእዩ በመጨረሻው ዘመን8፥19 ወይም መጨረሻው በተወሰነው ጊዜ ስለሚሆን ሊሆን ያለውን የሚያመለክት ስለሆነ፣ በኋላ በቍጣው ዘመን ምን እንደሚሆን እነግርሃለሁ፤ 20ያየኸው ሁለት ቀንዶች የነበሩት አውራ በግ፣ የሜዶንና የፋርስን መንግሥታት ያመለክታል። 21ጠጕራሙ ፍየል የግሪክ ንጉሥ ሲሆን፣ በዐይኖቹም መካከል ያለው ትልቁ ቀንድ የመጀመሪያው ንጉሥ ነው። 22የተሰበረውን ቀንድ የተኩት አራቱ ቀንዶች፣ ከመንግሥቱ የሚወጡትን አራት መንግሥታት ያመለክታሉ፤ ነገር ግን በኀይል አይተካከሉትም።

23“በዘመነ መንግሥታቸው በስተ መጨረሻ፣ ዐመፀኞች ፍጹም እየከፉ በሚሄዱበት ጊዜ፣ አስፈሪ ፊት ያለው አታላይ ንጉሥ ይነሣል። 24እጅግ ብርቱ ይሆናል፤ ነገር ግን በገዛ ኀይሉ አይደለም። አሠቃቂ ጥፋት ይፈጽማል፤ የሚያደርገው ሁሉ ይከናወንለታል፤ ኀያላን ሰዎችንና ቅዱሳኑን ሕዝብ ያጠፋል። 25እያጭበረበረ ይበለጽጋል፤ ራሱንም ታላቅ አድርጎ ይቈጥራል። በሰላም ተደላድለን ተቀምጠናል ሲሉ፣ ብዙዎችን ያጠፋል፤ በልዑላን ልዑልም ላይ ይነሣል፤ ይሁን እንጂ እርሱም ይጠፋል፤ ነገር ግን በሰው ኀይል አይደለም።

26“የተሰጠህ የምሽቱና የማለዳው ራእይ እውነት ነው፤ ነገር ግን ከብዙ ዘመን በኋላ የሚሆነውን ስለሚያመለክት ራእዩን ዝጋው።”

27እኔ ዳንኤል ዐቅሜ ተሟጥጦ ነበር፤ ለብዙ ቀናት ታመምሁ፤ ተኛሁም። ከዚያም በኋላ ተነሥቼ ወደ ንጉሡ ሥራ ሄድሁ። ባየሁት ራእይ ተደናግጬ ነበር፤ ነገሩም አልገባኝም።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

但以理書 8:1-27

公綿羊和公山羊的異象

1在看見先前的異象之後,我但以理伯沙撒王執政第三年又看見一個異象。 2我在異象中看見自己在以攔省的書珊城,又看見自己站在烏萊河畔。 3我舉目觀看,見一隻長著長角的公綿羊站在河邊,其中一角比另一角長,較長的角是後長出來的。 4我看見這公綿羊向西方、北方和南方頂撞,沒有獸能抵擋牠,或逃脫牠的威力。牠隨心所欲,狂妄自大。

5我正沉思的時候,忽然從西面出現一隻公山羊,穿越大地,腳不沾地。牠雙眼之間有一個大角。 6這公山羊來到我之前看見的那隻站在河邊的雙角公綿羊那裡,憤怒地向牠頂去。 7我看見公山羊憤怒地頂向公綿羊,攻擊牠,折斷了牠的雙角。公綿羊無力抵擋,被撞倒在地,踐踏在腳下,無人能救牠脫離公山羊的威力。 8公山羊極其狂妄自大。但正值鼎盛之時,牠的大角突然折斷,在原處又長出四個奇特的角,朝著天的四方。 9其中一個角又長出一個小角,向南方、東方和佳美之地8·9 佳美之地」指以色列,下同11·1641擴張勢力。 10它逐漸強大,高及天軍,將一些天軍和星宿拋到地上,用腳踐踏。 11它狂妄自大,要與天軍的統帥比高,它廢除日常獻給祂的祭,毀壞祂的聖所。 12因為反叛的緣故,天軍和日常所獻的祭都交給了它。它將真理拋在地上,它所行的無不順利。

13接著,我聽見一位聖者在說話,另一位聖者問他:「異象中出現的有關日常所獻的祭,毀滅性的反叛和踐踏聖所及天軍的事要持續多久呢?」 14他對我說:「兩千三百個晝夜。之後,聖所才會潔淨。」

解釋異象

15但以理看見這異象,正想明白它的意思,忽然有一個外貌像人的站在我面前。 16我聽見有人聲從烏萊河兩岸之間呼喊:「加百列啊,要讓此人明白這異象。」 17於是,他朝我站的地方走來,當他走來的時候,我嚇得俯伏在地。他對我說:「人子啊,你要明白,這異象是關於末後的時期。」 18他和我說話的時候,我伏在地上昏睡過去,他便輕拍我,扶我起來, 19對我說:「我要告訴你將來上帝發烈怒時所發生的事,因為這異象是關於那定好的末後時期。 20你看見的那隻有兩角的公綿羊指瑪代波斯的諸王。 21公山羊指希臘王,在牠雙眼之間的大角指第一個王。 22大角折斷後,從原處長出四個角表示四個國必從這國興起,但都不及這國強大。 23在四國的末期,人們惡貫滿盈的時候,必有一個面貌兇惡、詭計多端的王興起。 24他勢力強大,卻不是靠自己的力量。他必帶來可怕的毀滅,而且凡事亨通,他必毀滅強者和聖民。 25他利用詭計和騙術得逞,心高氣傲,乘人不備突然毀滅許多人,甚至要攻擊萬君之君,然而他終必被擊垮,但並非被人的手擊垮。 26異象中所說的兩千三百個晝夜是真的。但你要保密,不可告訴別人,因為這指的是遙遠的將來。」

27但以理精疲力盡,病了幾天。後來我起來照常辦理王的事務,但我對這異象感到驚奇不已,不明白它的意思。