ሕዝቅኤል 1 – NASV & CCBT

New Amharic Standard Version

ሕዝቅኤል 1:1-28

ሕያዋኑ ፍጡራንና የእግዚአብሔር ክብር

1በሠላሳኛው ዓመት፣1፥1 ወይም ዓመቴ በአራተኛው ወር፣ በአምስተኛው ቀን፣ በኮቦር ወንዝ አጠገብ በምርኮኞች መካከል ሳለሁ፣ ሰማያት ተከፈቱ፤ እኔም የእግዚአብሔርን ራእይ አየሁ።

2ንጉሡ ዮአኪን በተማረከ በአምስተኛው ዓመት፣ በአምስተኛው ቀን፣ 3በባቢሎናውያን1፥3 ወይም በከለዳውያን ምድር በኮቦር ወንዝ አጠገብ፣ የእግዚአብሔር ቃል ወደ ቡዝ ልጅ፣1፥3 ወይም ወደ ካህኑ ቡዝ ልጅ ወደ ሕዝቅኤል ወደ ካህኑ ወደ ሕዝቅኤል መጣ፤ በዚያ የእግዚአብሔር እጅ በእርሱ ላይ ነበረች።

4እኔም አየሁ፤ ስመለከትም፣ እነሆ ዐውሎ ነፋስ ከሰሜን በኩል መጣ፤ ይኸውም በታላቅ ብርሃን የተከበበ፣ መብረቅን የሚረጭ ታላቅ ደመና ነበረ፤ የእሳቱም መኻል የጋለ ብረት ይመስል ነበር። 5በእሳቱም ውስጥ የአራት ሕያዋን ፍጡራን አምሳያ ነበረ፤ መልካቸውም የሰው ቅርጽ ይመስል ነበር። 6እያንዳንዳቸውም አራት አራት ፊትና አራት አራት ክንፍ ነበራቸው። 7እግራቸው ቀጥ ያለ ነበር፤ ኰቴያቸውም እንደ ጥጃ ኰቴ ያለ ሲሆን፣ እንደ ተወለወለ ናስም ያብለጨልጭ ነበር። 8በአራቱ ጐኖቻቸው ባሉት ክንፎቻቸው ሥር የሰው እጅ ነበራቸው። አራቱም ፊቶችና ክንፎች ነበሯቸው፤ 9ክንፎቻቸውም እርስ በርስ ይነካኩ ነበር። እያንዳንዱም ቀጥ ብሎ ይሄድ ነበር፤ ወደ ኋላቸውም ዞር ብለው አይመለከቱም ነበር።

10ፊታቸውም እንዲህ ነበር፤ አራቱም እያንዳንዳቸው የሰው ፊት ነበራቸው፤ በቀኝ በኩል የአንበሳ ፊት፣ በግራ በኩልም የበሬ ፊት ነበራቸው፤ እያንዳንዳቸውም ደግሞ የንስር ፊት ነበራቸው። 11እንግዲህ ፊታቸው ይህን ይመስል ነበር፤ ክንፋቸውም ወደ ላይ ተዘርግቶ ነበር፤ እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ክንፍ ነበራቸው፤ የእያንዳንዱም ክንፍ የሌላውን ክንፍ ይነካ ነበር፤ ሁለቱ ክንፎቻቸው ሰውነታቸውን ይሸፍኑ ነበር። 12እያንዳንዱ ቀጥ ብሎ ወደ ፊት ይሄድ ነበር፤ ወደ ኋላም ሳይዞር መንፈስ ወደሚሄድበት ሁሉ ይሄድ ነበር። 13የሕያዋን ፍጡራኑ መልክም እንደሚነድ የከሰል ፍምና የተቀጣጠለ ችቦ ይመስል ነበር፤ በፍጡራኑ መካከል እሳት ወዲያ ወዲህ ይንቀሳቀስ ነበር፤ ብርሃኑም ደማቅ ነበር፤ ከእሳቱም ውስጥ መብረቅ ይወጣ ነበር። 14ፍጡራኑም እንደ መብረቅ ብልጭታ ፍጥነት ወዲያ ወዲህ ይወረወሩ ነበር።

15ሕያዋን ፍጡራኑን ስመለከታቸው፣ አራት ፊቶች ባሉት በእያንዳንዱ ፍጡር አጠገብ አንዳንድ መንኰራኵር በምድር ላይ አየሁ። 16የመንኰራኵሮቹ መልክና አሠራር እንዲህ ነበር፤ እንደ ቢረሌ ያንጸባርቁ ነበር፤ የአራቱም ቅርጽ ተመሳሳይ ሆኖ፤ እያንዳንዱ መንኰራኵር በመንኰራኵር ውስጥ ተሰክቶ የተሠራ ይመስል ነበር። 17በሚሄዱበት ጊዜም፣ ፍጡራኑ ወደሚዞሩበት ወደ አራቱ አቅጣጫ ሁሉ መንቀሳቀስ ይችሉ ነበር፤ ፍጡራኑ በሚሄዱበትም ጊዜ መንኰራኵሮቹ ወዲያና ወዲህ1፥17 ወይም ወደ ሌላ አይሉም ነበር። 18የመንኰራኵሮቹ ክብ ጠርዝ ረዥምና አስፈሪ ነበር፤ የአራቱም መንኰራኵሮች ክብ ጠርዝ ዙሪያውን በዐይኖች የተሞላ ነበር።

19ሕያዋኑ ፍጡራን ሲንቀሳቀሱ፣ በአጠገባቸው ያሉ መንኰራኵሮችም ይንቀሳቀሱ ነበር፤ ሕያዋኑ ፍጡራን ከምድር ከፍ ከፍ ሲሉ፣ መንኰራኵሮቹም አብረዋቸው ከፍ ከፍ ይሉ ነበር። 20መንፈስ ወደሚሄድበት ሁሉ ይሄዳሉ፤ የሕያዋኑ ፍጡራን መንፈስ በውስጣቸው ስላለ መንኰራኵሮቹ አብረዋቸው ይነሣሉ፤ 21ፍጡራኑ ሲንቀሳቀሱ ይንቀሳቀሳሉ፤ ፍጡራኑ ቀጥ ብለው ሲቆሙ እነርሱም ይቆማሉ፤ ፍጡራኑ ከምድር ከፍ ከፍ ሲሉ፣ የሕያዋኑ ፍጡራን መንፈስ በውስጣቸው ስላለ መንኰራኵሮቹ አብረዋቸው ይነሣሉ።

22ከሕያዋኑ ፍጡራን ራስ በላይ የሚያስፈራና፤ እንደ በረዶ የሚያንጸባርቅ ጠፈር የሚመስል ነገር ነበር። 23ከጠፈሩም በታች የአንዱ ክንፍ ወደ ሌላው ተዘርግቶ ነበር፤ እያንዳንዱም ሰውነቱን የሚሸፍንበት ሁለት ክንፍ ነበረው። 24ፍጡራኑ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ የክንፎቻቸውን ድምፅ ሰማሁ፤ ድምፁም እንደሚጐርፍ ውሃ ጩኸት፣ ሁሉን እንደሚችል1፥24 በዕብራይስጡ ሻዳይ ይላል አምላክ ድምፅና እንደ ሰራዊት ውካታ ነበር። መንቀሳቀሳቸውን ሲያቆሙም ክንፎቻቸውን ዝቅ ያደርጉ ነበር።

25መንቀሳቀሳቸውን አቁመው ክንፎቻቸውን ዝቅ እንዳደረጉ፣ ከራሳቸው በላይ ካለው ጠፈር ድምፅ ተሰማ። 26ከራሳቸው በላይ ካለው ጠፈር ከፍ ብሎ የሰንፔር1፥26 ወይም ላፒስ ላዙሊ ዙፋን የሚመስል ነገር ነበር፤ በዙፋኑም ላይ የሰው መልክ የሚመስል ነበር። 27ወገቡ ከሚመስለው ጀምሮ ወደ ላይ በእሳት መካከል እንዳለ የጋለ ብረት፣ ከወገቡም በታች እሳት ይመስል እንደ ነበር አየሁ፤ ደማቅ ብርሃንም በዙሪያው ነበር። 28በዝናብ ቀን በደመና ውስጥ እንደሚታየው ቀስተ ደመና በዙሪያው ያለው ጸዳል እንዲሁ ነበር።

ይህም የእግዚአብሔር ክብር መልክ አምሳያ ነበረ። ባየሁትም ጊዜ በግንባሬ ተደፋሁ፤ የአንድ ተናጋሪን ድምፅ ሰማሁ።

Chinese Contemporary Bible (Traditional)

以西結書 1:1-28

以西結的異象

1第三十年四月五日,我正在迦巴魯河畔被擄的人當中,忽然天開了,我看見了上帝的異象。 2那是約雅斤王被擄第五年的四月五日, 3就在迦勒底人境內的迦巴魯河畔,耶和華的話特別傳給了布西的兒子以西結祭司,耶和華的能力1·3 能力」希伯來文是「手」。降在他身上。

4在異象中,我看見一陣狂風從北方颳來,隨後有一大朵雲閃耀著火光,四周環繞著燦爛的光芒,火的中心像發光的金屬。 5火中有四個像人形的活物, 6每個活物有四張不同的面孔和四個翅膀。 7他們的腿是直的,腳如同牛犢的蹄,都亮如磨光的銅。 8四面的翅膀下都有人的手,四個活物都有臉和翅膀, 9翅膀彼此相連。他們移動時不必轉身,各朝前面移動。 10四個活物的面孔是這樣的:正面是人的臉,右面是獅子的臉,左面是牛的臉,後面是鷹的臉。 11他們的翅膀向上展開,每個活物的一對翅膀與其他活物的翅膀相連,另外一對翅膀遮蔽身體。 12耶和華的靈往哪裡去,他們也往哪裡去,移動時不用轉身。 13四個活物的形像如燃燒的火炭,又像火把。活物之間有火上下移動,發出耀眼的閃電。 14這些活物像閃電一樣往來飛馳。

15當我觀看這些活物的時候,發現每個活物旁邊的地上都有一個輪子。 16四個輪子的形狀和結構都一樣,好像輪套輪,如同閃耀的綠寶石。 17他們可以向四面移動,移動時輪子不必轉向。 18輪圈高而可畏,周圍佈滿了眼睛。 19活物行走,輪子也在旁邊行走;活物上升,輪子也上升。 20靈往哪裡去,活物也往哪裡去,輪子也跟著往哪裡去,因為活物的靈在輪子裡。 21活物行走,輪子也行走;活物站立不動,輪子也站立不動;活物上升,輪子也跟著上升,因為活物的靈在輪子裡。

22活物的頭上好像鋪展著茫茫的穹蒼,如同頂著耀眼的水晶。 23穹蒼下四個活物伸展翅膀,彼此相對,各用兩個翅膀遮蔽身體。 24他們移動時,翅膀發出的響聲如洪濤之聲,既像全能者的聲音,又像軍隊的呐喊。活物站住的時候,便將翅膀垂下。 25他們站立垂下翅膀時,有聲音從他們頭頂的穹蒼之上傳來。

26在他們頭頂的穹蒼之上彷彿有藍寶石的寶座,有一位形狀像人的高高坐在寶座上。 27我看到祂的腰部以上好像燒紅發亮的金屬,好像有火四面環繞。腰部以下如同火焰。祂周圍有耀眼的光輝, 28彷彿雨天雲中的彩虹。

這是耶和華榮耀的形像。我一看見,便俯伏在地,隨後聽見有說話的聲音。