ዳንኤል 3 – NASV & CCB

New Amharic Standard Version

ዳንኤል 3:1-30

የወርቁ ምስልና የእቶን እሳት

1ንጉሡ ናቡከደነፆር ከፍታው ስድሳ ክንድ፣ ወርዱ ስድስት ክንድ የሆነ የወርቅ ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው። 2ከዚያም መኳንንትን፣ ሹማምትን፣ አገረ ገዦችን፣ አማካሪዎችን፣ የግምጃ ቤት ኀላፊዎችን፣ ዳኞችን፣ ሌሎች የሕግ ዐዋቂዎችንና በየአውራጃው ያሉትን ሹማምት ሁሉ ላቆመው ምስል ምረቃ በዓል እንዲመጡ ጠራ። 3መኳንንቱ፣ ሹማምቱ፣ አገረ ገዦቹ፣ አማካሪዎቹ፣ የግምጃ ቤት ኀላፊዎቹ፣ ዳኞቹ፣ ሌሎች የሕግ ዐዋቂዎችና በየአውራጃው ያሉ ሹማምት ሁሉ ንጉሥ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ በዓል ተሰበሰቡ፤ በምስሉም ፊት ቆሙ።

4ከዚያም ከፍ ባለ ድምፅ እንዲህ የሚል ዐዋጅ ታወጀ፤ “ሕዝቦች ሆይ፤ መንግሥታትና ልዩ ልዩ ቋንቋ የምትናገሩ ሰዎች ሁሉ፤ እንድታደርጉ የታዘዛችሁት ይህ ነው፤ 5የመለከትና የእንቢልታ፣ የመሰንቆና የክራር፣ የበገናና የዋሽንት እንዲሁም የዘፈን ሁሉ ድምፅ ስትሰሙ፣ ንጉሥ ናቡከደነፆር ላቆመው የወርቅ ምስል ተደፍታችሁ መስገድ አለባችሁ፤ 6ተደፍቶ የማይሰግድ ማንም ሰው ቢኖር፣ ወዲያውኑ በሚንበለበለው የእሳት እቶን ውስጥ ይጣላል።”

7ስለዚህ የመለከትና የእንቢልታ፣ የመሰንቆና የክራር፣ የበገናና የዋሽንት፣ የዘፈንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ ወዲያውኑ ሕዝቡ ሁሉ፣ መንግሥታትና ልዩ ልዩ ቋንቋ የሚናገሩ ሰዎች፣ ንጉሥ ናቡከደነፆር ላቆመው የወርቅ ምስል ተደፍተው ሰገዱ።

8በዚህ ጊዜ አንዳንድ ኮከብ ቈጣሪዎች3፥8 ወይም ከላዳውያን ወደ ፊት ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፤ 9ንጉሥ ናቡከደነፆርንም እንዲህ አሉት፤ “ንጉሥ ሆይ፤ ለዘላለም ንገሥ! 10ንጉሥ ሆይ፤ አንተ እንዲህ ብለህ ዐዋጅ አውጥተህ ነበር፤ የመለከትና የእንቢልታ፣ የመሰንቆና የክራር፣ የበገናና የዋሽንት፣ የዘፈንም ድምፅ የሰማ ሁሉ ለወርቁ ምስል ተደፍቶ መስገድ አለበት፤ 11ማንም ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ባይሰግድ በሚንበለበለው የእሳት እቶን ውስጥ ይጣላል። 12ነገር ግን ንጉሥ ሆይ፤ በባቢሎን አውራጃ አስተዳዳሪዎች አድርገህ የሾምሃቸው ሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብደናጎ የሚባሉት አንዳንድ አይሁድ ትእዛዝህን አይቀበሉም፤ አማልክትህን አያገለግሉም፤ አንተም ላቆምኸው የወርቅ ምስል አይሰግዱም።”

13ንጉሥ ናቡከደነፆር በታላቅ ቍጣ ሲድራቅን፣ ሚሳቅንና አብደናጎን አስጠራቸው፤ እነዚህንም ሰዎች በንጉሡ ፊት አቀረቧቸው፤ 14ናቡከደነፆርም እንዲህ አላቸው፤ “ሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብደናጎ ሆይ፤ እኔ ላቆምሁት ምስል አለመስገዳችሁ፣ አማልክቴንም አለማገልገላችሁ እውነት ነው? 15አሁንም ቢሆን የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዋሽንቱን፣ የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ ስትሰሙ፣ እኔ ላቆምሁት የወርቅ ምስል ተደፍታችሁ ለመስገድ ዝግጁ ከሆናችሁ መልካም! ባትሰግዱለት ግን ወዲያውኑ ወደሚንበለበለው የእቶን እሳት ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ታዲያ ከእጄ ሊያድናችሁ የሚችል አምላክ ማን ነው?”

16ሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብደናጎ ለንጉሡ እንዲህ ብለው መለሱ፤ “ናቡከደነፆር ሆይ፤ በዚህ ጕዳይ ላይ ስለ ራሳችን መልስ መስጠት አያስፈልገንም። 17ንጉሥ ሆይ፤ በሚንበለበለው የእቶን እሳት ውስጥ ብንጣል፣ የምናመልከው አምላክ ሊያድነን ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል። 18ነገር ግን ንጉሥ ሆይ፤ ባያድነንም እንኳ፤ አማልክትህን እንደማናገለግል፣ ላቆምኸውም የወርቅ ምስል እንደማንሰግድ ዕወቅ።”

19ከዚያም ናቡከደነፆር በሲድራቅ፣ በሚሳቅና በአብደናጎ እጅግ ተቈጣ፣ ፊቱም ተለወጠባቸው፤ የእቶኑ እሳትም ቀደም ሲል ከነበረው ሰባት ዕጥፍ ተደርጎ እንዲነድድ አዘዘ። 20ከሰራዊቱም ብርቱ የሆኑትን ጥቂት ወታደሮች፣ ሲድራቅን፣ ሚሳቅንና አብደናጎን አስረው ወደሚንበለበለው የእቶን እሳት ውስጥ እንዲጥሏቸው አዘዘ። 21እነርሱም መጐናጸፊያቸውን፣ ሱሪያቸውን፣ የራስ ጥምጥማቸውንና ሌሎች ልብሶቻቸውን እንደ ለበሱ ታስረው በሚንበለበለው የእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ። 22የንጉሡ ትእዛዝ አስቸኳይ ስለ ነበረና የእቶኑም እሳት እጅግ ስለ ነደደ፣ የእሳቱ ወላፈን ሲድራቅን፣ ሚሳቅንና አብደናጎን ወስደው የጣሏቸውን ወታደሮች ገደላቸው። 23ሦስቱ ሰዎች ግን ተጠፍረው እንደ ታሰሩ በሚንበለበለው የእቶን እሳት ውስጥ ወደቁ።

24ከዚህ በኋላ ንጉሥ ናቡከደነፆር በአድናቆት ከተቀመጠበት ዘልሎ በመነሣት አማካሪዎቹን “አስረን በእሳት ውስጥ የጣልናቸው ሰዎች ሦስት አልነበሩምን?” ሲል ጠየቀ።

እነርሱም፣ “ንጉሥ ሆይ፤ እውነት ነው” አሉ።

25እርሱም፣ “እነሆ፤ ያልታሰሩና ያልተጐዱ አራት ሰዎች በእሳቱ ውስጥ ሲመላለሱ አያለሁ፤ አራተኛውም የአማልክትን ልጅ ይመስላል” አላቸው።

26ናቡከደነፆርም ወደሚነድደው የእቶን እሳት በር ቀረብ ብሎ ከፍ ባለ ድምፅ፣ “እናንተ የልዑል አምላክ አገልጋዮች ሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብድናጎ፤ ኑ ውጡ! ወደዚህ ኑ!” አላቸው።

ስለዚህ ሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብድናጎ ከእሳቱ ወጡ፤ 27መኳንንቱ፣ ሹማምቱ፣ አገረ ገዦቹና የቤተ መንግሥት አማካሪዎችም በዙሪያቸው ተሰበሰቡ፤ እነርሱም እሳቱ ሰውነታቸውን እንዳልጐዳ፣ ከራሳቸውም ጠጕር አንዲቷ እንኳ እንዳልተቃጠለች አዩ፤ የመጐናጸፊያቸው መልክ አልተለወጠም፤ የእሳትም ሽታ በላያቸው አልነበረም።

28ከዚያም ናቡከደነፆር እንዲህ አለ፤ “መልአኩን ልኮ አገልጋዮቹን ያዳነ፣ የሲድራቅ፣ የሚሳቅና የአብደናጎ አምላክ ይባረክ፤ በእርሱ በመታመን የንጉሡን ትእዛዝ ጥሰው፣ ከአምላካቸው በቀር ሌላ አምላክ ለማገልገልም ሆነ ለእርሱ ለመስገድ ፈቃደኛ ባለመሆን ሕይወታቸውን አሳልፈው ሰጥተዋልና። 29ስለዚህ እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅ፣ በሚሳቅና በአብደናጎ አምላክ ላይ ማናቸውንም ቃል የሚናገሩ ሕዝቦችም ሆኑ ልዩ ልዩ ቋንቋ የሚናገሩ ሁሉ ይቈራረጣሉ፤ ቤቶቻቸውም የፍርስራሽ ክምር ይሆናሉ ብዬ አዝዣለሁ።”

30ከዚያም ንጉሡ ሲድራቅን፣ ሚሳቅንና አብደናጎን በባቢሎን አውራጃ ላይ ሾማቸው።

Chinese Contemporary Bible (Simplified)

但以理书 3:1-30

金像和火窑

1尼布甲尼撒王造了一尊高二十七米、宽二点七米的金像,立在巴比伦省的杜拉平原。 2他派人召集总督、行政官、省长、谋士、库房官、审判官、司法官及各省的所有官员,前来参加他所立之像的奉献礼。 3于是总督、行政官、省长、谋士、库房官、审判官、司法官及各省的官员齐来参加尼布甲尼撒王所立之像的奉献礼,站在那像面前。

4传令官大声宣布说:“各族、各邦、各语种的人啊,王有令, 5‘你们一听见角、笛、弦琴、竖琴、瑟、笙等各种乐器奏响,就要叩拜尼布甲尼撒王所立的金像。 6不叩拜的人必立刻被抛进烈焰熊熊的火窑。’” 7于是,各族、各邦、各语种的人一听见角、笛、弦琴、竖琴、瑟等各种乐器的声音,就都叩拜尼布甲尼撒王所立的金像。

8那时,有几个占星家前来控告犹大人。 9他们对尼布甲尼撒王说:“愿王万岁! 10王啊,你曾下令,角、笛、弦琴、竖琴、瑟、笙等各种乐器一奏响,每个人都要叩拜金像。 11不叩拜的人必被扔进烈焰熊熊的火窑。 12然而,王啊,有几个犹大人,就是王委派负责巴比伦省事务的沙得拉米煞亚伯尼歌,却不理会你的命令,不事奉你的神明,也不祭拜你立的金像。” 13尼布甲尼撒王勃然大怒,下令将沙得拉米煞亚伯尼歌带来。于是他们被带到王面前。 14尼布甲尼撒问他们:“沙得拉米煞亚伯尼歌啊,你们真的不事奉我的神明,不祭拜我立的金像吗? 15现在你们准备好,一听见角、笛、弦琴、竖琴、瑟、笙等各种乐器的声音,就要叩拜我造的像。不然,必立刻将你们扔进烈焰熊熊的火窑。那时什么神明能从我手中救你们呢?”

16沙得拉米煞亚伯尼歌答道:“尼布甲尼撒啊,我们无需为此事回答你。 17王啊,我们若真被扔进烈焰熊熊的火窑,我们所事奉的上帝必能救我们脱离火窑,祂必从你手中救我们。 18即或不然,王啊,你要明白,我们也不会事奉你的神明或祭拜你立的金像。”

19尼布甲尼撒怒气填胸,向沙得拉米煞亚伯尼歌大发雷霆,下令将火窑烧得比平时热七倍, 20又命令军中的勇士将沙得拉米煞亚伯尼歌绑起来,扔进烈焰熊熊的火窑。 21这三人穿着外袍、裤子等衣物,戴着头巾,被绑着扔进烈焰熊熊的火窑。 22因为王的命令紧急,窑烧得非常热,火焰烧死了那些抬沙得拉米煞亚伯尼歌的人。 23沙得拉米煞亚伯尼歌三人被绑着落入烈焰熊熊的火窑。

24这时,尼布甲尼撒王惊奇地跳起来,问谋士:“我们绑起来扔进火里的不是三个人吗?”他们答道:“王啊,是的。” 25王说:“看啊,我见有四个人在火中走来走去,没有被绑着,也没有被烧伤,第四个人的面貌好像神明的儿子。”

26于是,尼布甲尼撒走近火窑的门,喊道:“至高上帝的仆人沙得拉米煞亚伯尼歌啊,出来吧,到这里来吧。”沙得拉米煞亚伯尼歌便从火中出来。 27那些总督、行政官、省长和王的谋士上前围观,见火焰没有烧伤他们的身体,他们的头发没有烧焦,衣服没有烧坏,身上甚至没有火燎的气味。 28尼布甲尼撒说:“沙得拉米煞亚伯尼歌的上帝当受称颂!祂差遣天使拯救那些信靠祂的仆人。他们无视王命,宁肯死也不供奉、祭拜其他神明。 29现在我下令,不论何民、何邦、何族,若毁谤沙得拉米煞亚伯尼歌的上帝,必被碎尸万段,他们的家必沦为废墟,因为没有别的神明能这样施行拯救。” 30于是,王让沙得拉米煞亚伯尼歌巴比伦省身居高位。